• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል?

January 13, 2021 04:10 am by Editor 2 Comments

ከህወሀት መደምሰስ በኋላ የብልጽግና ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል የሚለውን ጥያቄ ኢትዮጵያውያን መጠየቅ የጀመሩት የአገር መከላከያ ሰራዊት መቀሌን መቆጣጠሩን የሚያበስረው ዜና ከተሰማ ሰአት አንስቶ ነው።

ከዚህ የድል ዜና በኋላ ብዙዎች የዜጎች መፈናቀል እና የፖለቲካ ትኩሳት የሚፈጥራቸው አሰቃቂ ክስተቶችን ከመስማት እንገላገላለን በሚል ተስፋ አድርገው ነበር።

ለመሆኑ አገር እየመራ ያለው የቀድሞው ኢህአዴግ የአሁኑ ብልጽግና ፓርቲ ከህወሀት መደምሰስ በኋላ ፈተናዎቹ ምን ምን ሊሆኑ ይችላሉ በሚል ኢትዮ ኤፍ ኤም በፖለቲካ ነክ ጉዳዮች ላይ ትንታኔ በመስጠት ከሚታወቁት ዶክተር አለማየሁ አረዳ ጋር ቆይታ አደርጓል።

እንደ ዶ/ር አለማየሁ ገለጸ ህወሀት በአካል ቢወገድም የዘረጋው አጠቃላይ ስርአት፣አስተሳሰቡና የመንፈስ ልጆቹ የገዢው ፓርቲ ፈተና ይሆናሉ ብለዋል።

ይህ እንዳለ ሆኖ “ዋናው የብልፅግና ቀጣይ ፈተና ራሱ ብልፅግና ነው” ብለዋል ዶክተር አለማየሁ።

የተወሰነ መረጃ እንዳገኘሁት ከሆነ ይላሉ ዶ/ር አለማየሁ ብልፅግና ፓርቲ ጠቅላላ ጉባዔውን አድርጎ ፕሮግራሙንና መታዳደርያ ደንቡብ አላፀደቀም።

የኢህአዴግ የነበረው በሙሉ ተገልብጦ ብልፅግና እንዲባል፣ አባላቱም ልክ እንደ ጃኬት ተገልብጠው ነው የመጡት ሲሉ ተናግረዋል።

የሚቀጥለውን ምርጫ እንዳሉ እነሱ በፌደራልም፣ በክልልም ተመርጠው ፤ ስልጣን ለመያዝ ተዘጋጅተዋል፤ ሽንፈት የመቀበል ስነ ልቦናዊ ዝግጅቱም ያላቸው አይመስሉም ብለዋል።

እነዚህ የብልፅግና ካድሬዎች ምን ያህል የጠራ ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ አላቸው? ምን ያህልስ ለውጡን ተገንዝበውታል? ምን ያህልስ ለህዝቡ ተገቢ አመራር የመስጠት አቅም አላቸው?

የሚለው አጠራጣሪና ለፈተና ያልቀረበ ነው ያሉ ሲሆን አብዛኛውን ጊዜ ስለ በጋራ ስለ መኖር፣ ስለ አንድነት፣ ስለ ዴሞክራሲ፣ በጋራ ስለ መበልፀግ፣ የምንሰማው ከዶ/ር አብይ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ሌሎቹ ካድሬዎች ባሉበት ነው ያሉት የሚሉት ዶ/ር አለማየሁ፤ በየክልሎቹ ያሉት የብልፅግና ቅርንጫፎች እውነት ለሌሎች ፓርቲዎች ሰፊ የመጫወቻ ሜዳ ይለቃሉ? የሚለው በጣም አጠራጣሪ ነው ብለዋል።

ሌላው ይላሉ ዶ/ር አለማየሁ፤ ሌላው ትልቁ በጥበብ ሊፈታ የሚገባው ቀጣዩ የገዢው ፓርቲ ፈተና ፤ የእነ ወላቃይትና ራያ ጉዳይ ነው ብለዋል።

አካባቢዎቹ ነፃ ወጥተናል ሲሉ አውጀዋል፤ የህግ የበላይነትን ለማስከበር የተካሄደ ዘመቻ መሆኑ መዘንጋት የለበትም ይላሉ።

ምርጫው እየቀረበ ሲሄድ ጥያቄዎቹ እየከረሩ ሲሄዱ ለመንግስትም ለድንበር ኮሚሽኑም ትልቅ አጣቢቂኝ ነው የሚሆነው ብለዋል።

በቃ ህወሀት ተወግዷል በሚል ከትግራይ ክልል ነጥቆ አማራ ክልል ውስጥ ማስገባት በዛ በኩል የሚያስከፋው ህዝብ ስለሚኖር ፍትሀዊ አይደለም። በሌላ በኩል ህወሀት ለዘመናት በቅኝ እንደያዛቸው አድርጎ ሲያስተዳድራቸው የነበረው፣ የሰብአዊ መብት ጥሰት እስከ ዘር ማጥፋት ወንጀል ሲፈፀምባቸው የኖረውንና ማንነታችንን ተነጥቀናል፤ የሚሉትን ዜጎች በቃ እንደ ከዚህ ቀደሙ ቀጥሉ ማለትም ተገቢ አይደለም፣ህዝቡ ነቅቷል።

ከዚህ በመለስ ለትግራይ፣ከዚህ በመለስ ደግሞ ለማራ ብሎ ሸንሽኖ ማከፍፈልም አይሆንም፤ሲሉ ተናግረዋል።

እነዚህ አካባቢዎች ኢህአዴግ ስልጣን ከመያዙ በፊት የትኛው አስተዳደር ስር ነበሩ፣ የህዝቡስ ፍላጉትና ስነ ልቦና (Psychological makeup)፣ ኢህአዴግ ስልጣን ከያዘ በኋላ ለዲሞግራፊ ተብሎ ስለ ሰፈሩ ህዝቦች፤ የሚሉትና ሌሎችም ጉዳዮች ላይ የአማራ ክልልና የትግራይ ክልል ፌዴሬሽን ምክር ቤትም የሚመለከተው ሁሉ ቁጭ ብለው መነጋገር አለባቸው ያሉ ሲሆን እስከ ምርጫው ግን ግዛቶቹ በፌደራል መንግስት ስር ያሉ ልዩ አስተዳደሮች ተመስርቶላቸው ነው መቆየት ያለባቸው፣ የሽግግርና ፋታ መውሰጃ ጊዜ ያስፈልጋል ሲሉ አሳስበዋል ዶክተር አለማየሁ።

በቅድሚያ መተማመን መፈጠር አለበት ብለዋል።

ሌላው ሙሉ በሙሉ በኦነግ ሸኔ የሚላከከው፤ የመተከልና ሌሎች ኦሮሚያ ክልል ላይ በተለይ አማራ ላይ የሚፈፀሙ ማንነትን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች፤ ራሱ ብልፅግና በተለይ ፤ የኦሮሚያ ክንፍ ሊፈተሽባቸው የሚገቡ ወንጀሎች ናቸው ብለዋል።

ሸኔ ተደመሰሰ ሲባል ተማረከ ተብሎ የምንሰማው 7 ክላሽና 30 ኋላ ቀር መሳርያ ነው፤ ይሄ የሚያሳይህ ምን ያህል ደካማ ሀይል እንደሆነ ነው፤ መንግስት አቅቶት ሳይሆን ራሱ ገዢው ፓርቲ ውስጥ የሚገኙ ለኦነግ ሸኔ የሚያደሉ በልፅግና ውስጥ የሚገኙ ሰዎች በቁጥር ትንሽ ስላልሆኑ ነው ብለዋል።

የኦሮሚያ የፖለቲካ አሰላለፍ ጥናት ይፈልጋል ያሉት ዶክተር አለማየሁ ግብፅን የመሰሉ የውጪ ሀይሎችም፤ከፍተኛ ገንዘብ የሚያፈሱበት ነው ብለዋል።

ለዶ/ር አብይ መንግስት ትልቅ ራስ ምታት ቤንሻንጉል ነው የሚሉት ዶ/ር አለማየሁ አልጀዚራ ላይ አንድ የግብፅ ሰው ቤንሻንጉል የሚባል ቦታ አለ፣ በዛም መግባት እንችላለን ሲል እንደነበር አንስተዋል።

በመጨረሻም ፤ ዶ/ር አለማየሁ ፤ ብልፅግና ራሱን እንዲያጸዳ ያሳሰቡ ሲሆን ፤ ግልፅ አቋምና ፍኖተ ካርታ እንጂ ለሁሉ ነገር ግብረ ሀይል አያስፈልገውም ሲሉ ምክራቸውን አስተላልፈዋል።

በመጀመርያ ደረጃ ራሱ ብልፅግና ፓርቲ ኢህአዴግ ያለበሰውን ጥብቆ አውልቆ መለወጥ አለበት ይላሉ ዶ/ር አለማየሁ።

ከስር ያለው የፓርቲው መሰረት እላይ ባለው አመራር ዝም ብሎ የሚጎተት ይመስላኛል ብለዋል።

ምንድነው ግብረ ሀይል ማብዛት ሲሉ የሚጠይቁት ዶ/ር አለማየሁ ዋናው እና መሰረታዊ የሆነው የሀገራችንን ፖለቲካዊ ጥያቄ በዘላቂነት ለመፍታት ነው ገዢው ፓርቲ መሞከር ያለበት ብለዋል።

ዶ/ር አብይ የሚሰራውን አምስት በመቶ የሚሰራ ብልፅግና ውስጥ የለም ያ ሲሆን ፕሮግራሙና መተዳደርያ ደንቡ አለመፅደቁን የማያውቅ የማዕከላዊ ኮሚቴ እንዳለ አውቄያለሁ። ሌላ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ደግሞ ጸድቋል ይለኛል። ሁለቱም ደግሞ የኢህአዴግ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ነበሩ ሲሉ ትዝብታቸውን ገልፀዋል።

እነዚህ ምርጫ ሲመጣ እኛ እኮ ብልፅግና ነን ወደ የትም አንሄድም ነው የሚሉን ያሉ ሲሆን ብልፅግና ቀጣዩን ፈተናውን ለመሻገር በጠራ አስተሳሰብና በጠራ ፍኖተ ካርታ መንቀሳቀስ አለበት ሲሉ ምክራቸውን አስተላልፈዋል።

(ሔኖክ አስራት፤ ኤፍ ኤም 107.8)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics, Right Column

Reader Interactions

Comments

  1. Gashaw yismaw says

    March 15, 2021 09:03 am at 9:03 am

    በጥም ጥሩ አቅርቧል ሌላ ትንታኔዎችን እንጠብቃለን

    Reply
  2. wendwesen mekonen says

    May 15, 2021 01:30 pm at 1:30 pm

    I like this page

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule