• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል?

January 13, 2021 04:10 am by Editor 2 Comments

ከህወሀት መደምሰስ በኋላ የብልጽግና ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል የሚለውን ጥያቄ ኢትዮጵያውያን መጠየቅ የጀመሩት የአገር መከላከያ ሰራዊት መቀሌን መቆጣጠሩን የሚያበስረው ዜና ከተሰማ ሰአት አንስቶ ነው።

ከዚህ የድል ዜና በኋላ ብዙዎች የዜጎች መፈናቀል እና የፖለቲካ ትኩሳት የሚፈጥራቸው አሰቃቂ ክስተቶችን ከመስማት እንገላገላለን በሚል ተስፋ አድርገው ነበር።

ለመሆኑ አገር እየመራ ያለው የቀድሞው ኢህአዴግ የአሁኑ ብልጽግና ፓርቲ ከህወሀት መደምሰስ በኋላ ፈተናዎቹ ምን ምን ሊሆኑ ይችላሉ በሚል ኢትዮ ኤፍ ኤም በፖለቲካ ነክ ጉዳዮች ላይ ትንታኔ በመስጠት ከሚታወቁት ዶክተር አለማየሁ አረዳ ጋር ቆይታ አደርጓል።

እንደ ዶ/ር አለማየሁ ገለጸ ህወሀት በአካል ቢወገድም የዘረጋው አጠቃላይ ስርአት፣አስተሳሰቡና የመንፈስ ልጆቹ የገዢው ፓርቲ ፈተና ይሆናሉ ብለዋል።

ይህ እንዳለ ሆኖ “ዋናው የብልፅግና ቀጣይ ፈተና ራሱ ብልፅግና ነው” ብለዋል ዶክተር አለማየሁ።

የተወሰነ መረጃ እንዳገኘሁት ከሆነ ይላሉ ዶ/ር አለማየሁ ብልፅግና ፓርቲ ጠቅላላ ጉባዔውን አድርጎ ፕሮግራሙንና መታዳደርያ ደንቡብ አላፀደቀም።

የኢህአዴግ የነበረው በሙሉ ተገልብጦ ብልፅግና እንዲባል፣ አባላቱም ልክ እንደ ጃኬት ተገልብጠው ነው የመጡት ሲሉ ተናግረዋል።

የሚቀጥለውን ምርጫ እንዳሉ እነሱ በፌደራልም፣ በክልልም ተመርጠው ፤ ስልጣን ለመያዝ ተዘጋጅተዋል፤ ሽንፈት የመቀበል ስነ ልቦናዊ ዝግጅቱም ያላቸው አይመስሉም ብለዋል።

እነዚህ የብልፅግና ካድሬዎች ምን ያህል የጠራ ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ አላቸው? ምን ያህልስ ለውጡን ተገንዝበውታል? ምን ያህልስ ለህዝቡ ተገቢ አመራር የመስጠት አቅም አላቸው?

የሚለው አጠራጣሪና ለፈተና ያልቀረበ ነው ያሉ ሲሆን አብዛኛውን ጊዜ ስለ በጋራ ስለ መኖር፣ ስለ አንድነት፣ ስለ ዴሞክራሲ፣ በጋራ ስለ መበልፀግ፣ የምንሰማው ከዶ/ር አብይ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ሌሎቹ ካድሬዎች ባሉበት ነው ያሉት የሚሉት ዶ/ር አለማየሁ፤ በየክልሎቹ ያሉት የብልፅግና ቅርንጫፎች እውነት ለሌሎች ፓርቲዎች ሰፊ የመጫወቻ ሜዳ ይለቃሉ? የሚለው በጣም አጠራጣሪ ነው ብለዋል።

ሌላው ይላሉ ዶ/ር አለማየሁ፤ ሌላው ትልቁ በጥበብ ሊፈታ የሚገባው ቀጣዩ የገዢው ፓርቲ ፈተና ፤ የእነ ወላቃይትና ራያ ጉዳይ ነው ብለዋል።

አካባቢዎቹ ነፃ ወጥተናል ሲሉ አውጀዋል፤ የህግ የበላይነትን ለማስከበር የተካሄደ ዘመቻ መሆኑ መዘንጋት የለበትም ይላሉ።

ምርጫው እየቀረበ ሲሄድ ጥያቄዎቹ እየከረሩ ሲሄዱ ለመንግስትም ለድንበር ኮሚሽኑም ትልቅ አጣቢቂኝ ነው የሚሆነው ብለዋል።

በቃ ህወሀት ተወግዷል በሚል ከትግራይ ክልል ነጥቆ አማራ ክልል ውስጥ ማስገባት በዛ በኩል የሚያስከፋው ህዝብ ስለሚኖር ፍትሀዊ አይደለም። በሌላ በኩል ህወሀት ለዘመናት በቅኝ እንደያዛቸው አድርጎ ሲያስተዳድራቸው የነበረው፣ የሰብአዊ መብት ጥሰት እስከ ዘር ማጥፋት ወንጀል ሲፈፀምባቸው የኖረውንና ማንነታችንን ተነጥቀናል፤ የሚሉትን ዜጎች በቃ እንደ ከዚህ ቀደሙ ቀጥሉ ማለትም ተገቢ አይደለም፣ህዝቡ ነቅቷል።

ከዚህ በመለስ ለትግራይ፣ከዚህ በመለስ ደግሞ ለማራ ብሎ ሸንሽኖ ማከፍፈልም አይሆንም፤ሲሉ ተናግረዋል።

እነዚህ አካባቢዎች ኢህአዴግ ስልጣን ከመያዙ በፊት የትኛው አስተዳደር ስር ነበሩ፣ የህዝቡስ ፍላጉትና ስነ ልቦና (Psychological makeup)፣ ኢህአዴግ ስልጣን ከያዘ በኋላ ለዲሞግራፊ ተብሎ ስለ ሰፈሩ ህዝቦች፤ የሚሉትና ሌሎችም ጉዳዮች ላይ የአማራ ክልልና የትግራይ ክልል ፌዴሬሽን ምክር ቤትም የሚመለከተው ሁሉ ቁጭ ብለው መነጋገር አለባቸው ያሉ ሲሆን እስከ ምርጫው ግን ግዛቶቹ በፌደራል መንግስት ስር ያሉ ልዩ አስተዳደሮች ተመስርቶላቸው ነው መቆየት ያለባቸው፣ የሽግግርና ፋታ መውሰጃ ጊዜ ያስፈልጋል ሲሉ አሳስበዋል ዶክተር አለማየሁ።

በቅድሚያ መተማመን መፈጠር አለበት ብለዋል።

ሌላው ሙሉ በሙሉ በኦነግ ሸኔ የሚላከከው፤ የመተከልና ሌሎች ኦሮሚያ ክልል ላይ በተለይ አማራ ላይ የሚፈፀሙ ማንነትን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች፤ ራሱ ብልፅግና በተለይ ፤ የኦሮሚያ ክንፍ ሊፈተሽባቸው የሚገቡ ወንጀሎች ናቸው ብለዋል።

ሸኔ ተደመሰሰ ሲባል ተማረከ ተብሎ የምንሰማው 7 ክላሽና 30 ኋላ ቀር መሳርያ ነው፤ ይሄ የሚያሳይህ ምን ያህል ደካማ ሀይል እንደሆነ ነው፤ መንግስት አቅቶት ሳይሆን ራሱ ገዢው ፓርቲ ውስጥ የሚገኙ ለኦነግ ሸኔ የሚያደሉ በልፅግና ውስጥ የሚገኙ ሰዎች በቁጥር ትንሽ ስላልሆኑ ነው ብለዋል።

የኦሮሚያ የፖለቲካ አሰላለፍ ጥናት ይፈልጋል ያሉት ዶክተር አለማየሁ ግብፅን የመሰሉ የውጪ ሀይሎችም፤ከፍተኛ ገንዘብ የሚያፈሱበት ነው ብለዋል።

ለዶ/ር አብይ መንግስት ትልቅ ራስ ምታት ቤንሻንጉል ነው የሚሉት ዶ/ር አለማየሁ አልጀዚራ ላይ አንድ የግብፅ ሰው ቤንሻንጉል የሚባል ቦታ አለ፣ በዛም መግባት እንችላለን ሲል እንደነበር አንስተዋል።

በመጨረሻም ፤ ዶ/ር አለማየሁ ፤ ብልፅግና ራሱን እንዲያጸዳ ያሳሰቡ ሲሆን ፤ ግልፅ አቋምና ፍኖተ ካርታ እንጂ ለሁሉ ነገር ግብረ ሀይል አያስፈልገውም ሲሉ ምክራቸውን አስተላልፈዋል።

በመጀመርያ ደረጃ ራሱ ብልፅግና ፓርቲ ኢህአዴግ ያለበሰውን ጥብቆ አውልቆ መለወጥ አለበት ይላሉ ዶ/ር አለማየሁ።

ከስር ያለው የፓርቲው መሰረት እላይ ባለው አመራር ዝም ብሎ የሚጎተት ይመስላኛል ብለዋል።

ምንድነው ግብረ ሀይል ማብዛት ሲሉ የሚጠይቁት ዶ/ር አለማየሁ ዋናው እና መሰረታዊ የሆነው የሀገራችንን ፖለቲካዊ ጥያቄ በዘላቂነት ለመፍታት ነው ገዢው ፓርቲ መሞከር ያለበት ብለዋል።

ዶ/ር አብይ የሚሰራውን አምስት በመቶ የሚሰራ ብልፅግና ውስጥ የለም ያ ሲሆን ፕሮግራሙና መተዳደርያ ደንቡ አለመፅደቁን የማያውቅ የማዕከላዊ ኮሚቴ እንዳለ አውቄያለሁ። ሌላ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ደግሞ ጸድቋል ይለኛል። ሁለቱም ደግሞ የኢህአዴግ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ነበሩ ሲሉ ትዝብታቸውን ገልፀዋል።

እነዚህ ምርጫ ሲመጣ እኛ እኮ ብልፅግና ነን ወደ የትም አንሄድም ነው የሚሉን ያሉ ሲሆን ብልፅግና ቀጣዩን ፈተናውን ለመሻገር በጠራ አስተሳሰብና በጠራ ፍኖተ ካርታ መንቀሳቀስ አለበት ሲሉ ምክራቸውን አስተላልፈዋል።

(ሔኖክ አስራት፤ ኤፍ ኤም 107.8)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics, Right Column

Reader Interactions

Comments

  1. Gashaw yismaw says

    March 15, 2021 09:03 am at 9:03 am

    በጥም ጥሩ አቅርቧል ሌላ ትንታኔዎችን እንጠብቃለን

    Reply
  2. wendwesen mekonen says

    May 15, 2021 01:30 pm at 1:30 pm

    I like this page

    Reply

Leave a Reply to wendwesen mekonen Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሆሩ ጉዱሩ ወለጋ ዞን የጉደኔ ጫላ ሲበሬ ቀበሌ ነዋሪዎች በኦነግ ሸኔ ላይ ጀብዱ ፈፀሙ August 11, 2022 03:04 pm
  • በኢትዮጵያ ግብርና ላይ ግብጽ ለዓመታት የፈጸመችው ሤራ August 10, 2022 10:58 am
  • የስሪ ላንካው “FamilyCracy” – ከመዓቱ እስከ ተውኔቱ August 8, 2022 09:45 am
  • “አበበ እንጂ መቼ ሞተ!”          July 19, 2022 04:57 pm
  • ሸኔ አመራሮቹንና ጠንካራ ይዞታዎቹን እያጣ ነው July 19, 2022 01:55 am
  • የወልቃይት አማራ የተሰቃየባቸው የትህነግ 15 ድብቅ እስር ቤቶች! July 18, 2022 03:13 pm
  • ገቢ የማያስገኙ የዜና ርዕሶች July 17, 2022 05:36 pm
  • “ዛሬ ‘ኃያል ነን’ የሚሉ ሀገራት ኢትዮጵያ ላይ በሚዲያ /በመረጃ/፣ በዲፕሎማሲ፣ በሳይበር እና በተልእኮ የተቀነባበረ ‘ግራጫ ጦርነት’ እያካሄዱባት ነው” ጠ/ሚ ዐቢይ July 7, 2022 10:03 am
  • የኦሮሞ ልሂቃንና ፖለቲከኞች በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን “የዘር ማጥፋት” ወንጀል እንዲያወግዙት አብን ጠየቀ July 6, 2022 01:38 pm
  • “አማራን ኦሮሚያ ውስጥ የመግደል እና የመጨፍጨፍ እቅድ የኦነግ ሳይሆን የኦሮሚያ ብልጽግና ነው” አቶ ሃንጋሳ July 6, 2022 01:53 am
  • “በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” አይማን አብድልአዚዝ ግብጻዊው ፖለቲከኛ July 5, 2022 12:57 pm
  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule