• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሰማዕትነት ጥሪ ቤተመንግሥቱን ባቋራጭ መቆጣጠር

February 9, 2023 01:25 pm by Editor 1 Comment

ይህ ለውጥ እውን ከሆነ በኋላ ሕዝብን ስሜታዊ የሚያደረጉ ተግባራት ናቸው በቅስቀሳ መልኩ የሚሰራጩት። ሰው ይገደልና ይሰቀላል። ተሰቅሎ ሲወገር ፊልም ይቀረጻል። ወዲያው ለሕዝብ ላይቭ ይለቀቃል።

“እኔ ከእገሌ ብሔር አልተወለድኩም በል” እየተባለ ሰው በማንነቱ ሲገደል የሚያሳይ ፊልም በቅጽበት አየር ላይ እንዲውልና በብርሃን ፍጥነት እንዲሰራጭ ይደረጋል።

ንጹሐን እንዲታገቱ ይደረግና እገታው በሚፈለገው መንገድ ተቀነባብሮ በማኅበራዊ ሚዲያ እንዲጎን ይደረጋል።

ነፍሰጡር ስትሞት፣ ሕጻን እያየ አባት ሲገደል፣ ንብረት ሲቃጠልና ሌሎች በሟችና በሚወድመው ንብረት ሲዛበቱ የሚያሳይ ምስል በተቀናበረ ሁኔታ በማኅበራዊ ሚዲያዎች ይጦዛል። ይህ በትግራይ፣ በኦሮሚያ፣ በማራ፣ አፋር … ሆኗል። አሁን ደግሞ መልኩን ቀይሮ እየሆነ ነው። ሲሆን ንጹሐን ላይ የደረሰን ጉዳት ለፖለቲካ ገበያ ለማዋል ታስቦ ሲሆን፣ አንድም ሆነ ተብሎ ጉዳቱ እንዲደርስ ሤራ ይጠነሰሳል፤ ሤራውን ፈጻሚና አስፈጻሚ ይቀጠራሉ። በጀት መዳቢዎቹ ሚዲያዎችንም ያካትታሉ። በግብስብስ በተከፈቱ የቁጭ በሉ ስሞች ድራማው ይረጫል። ሕዝብ በሚያየው ተቃጥሎ ስሜት ውስጥ ይገባል። ስሜት ውስጥ የሚገቡ ማሰብ ያቆማሉ። ማሰብ ባቆሙት አማካይነት የሚፈለገው የወቅቱ አጀንዳ ይፈጸማል።

ዛሬ ቃላት ሳይመረጥ “ቤተመንግሥት ክበብ፣ ቤተመንግሥት ውረር፣ ቤተመንግሥት ገብተህ ንቀል” የሚባለው እምነት ላይ የተንጠለጠለ “የቅዱስ ሲኖዶስ የሰማዕትነት ጥሪ” አዝማቾቹ አባቶቹ ላይ “እንዳትወያዩ፣ እንዳትነጋገሩ” በሚል ጫና እያደረጉ እየቆሰቆሱት ነው።

በስመ ነጻ ሚዲያ የሚደረገው ይህ የዓመጽ ጥሪ ሁሉንም ዓይነት አማራጭ ተከትሎ በኪሣራ ሲቋጭ አስቀድሞ የሞከረው ሙስሊሞችን ነበር። የሙስሊሞች በር ሲዘጋ፣ መቶ ሃያ አምስት ሚሊዮን ሕዝብና በርካታ ዕምነት ባለበት አገር “አንድ እምነት፣ አንድ ቤተክርስቲያን፣ አንድ ጳጳስ፣…” በሚለው ለስምምነት የማይበጅ፣ ለዘመኑ የማይመጥን፣ ሌሎችን ቅር የሚያሰኝ ዘመቻ በታሪካዊቷ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ስም ተከፈተ። ይህ ዘመቻ የመጨረሻው ካርድ ባለው ከፍተኛ በጀት እየታገዘ ያገኝውን ሁሉ አዝማች፣ አጋፋሪ፣ አውራጅና ጫኝ፣ ተቆርቋሪና አልቃሽ … አድርጎ “ለጠቅላይ” እንጫወት እያለ ነው።

በቅዱስ ሲኖዶስ ውስጥ ካሉት አባቶች አንዳንዶቹ ለቅሰቀሳ በሚጋበዙባቸው ሚዲያዎች “አንወያይም አላልንም፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዲያወያዩን እንፈልጋለን፤ ጥላቻ ኃጢአት ነው። መስዋዕት ፍቅር ከሌለበት ዋጋ የለውም” ሲሉ የሰሙ፣ ሲኖዶሱ በተወሰኑ ክፍሎች ጫና ሥር ስለመውደቁ ማሳያ እንደሆነና አድሮ ሌላ ጣጣ እንደሚያመጣ ይገልጻሉ።

ሌሎች ደግሞ “እጅግ ያከረሩና የመንፈሳዊነት ጠረን የሌላቸው” መኖራቸውን ጠቅሰው ልዩነት መኖሩን ያመልክታሉ። እነዚህ ክፍሎች “አፈንጋጭ” ከሚባሉት ወገን ሆነው ያልተገባ ድርጊት እንዲፈጠር የሚሠሩ መኖራቸውን ያክላሉ። በፖለቲካው አመራር ውስጥም አብረዋቸው ያሉ መስለው ባለተገባ መንገድ ልዩነቱን የሚያከሩ ካድሬዎች ስለመኖራቸው አይጠራጠሩም።

የአዲስ አበባ አገረ ስብከት ከፍተኛ ግፍ ይፈጸምበት እንደነበረ “ሰው ይሸጥበታል” በሚል ሰሞኑንን የገለጹ፣ ጸቡ የሃብት ቅርምትና የሌብነትም እንደሆነ ሰሞኑን ቃለ ምልልስ ሰጥተው የተናገሩ አሁንም በሥራ ላይ ያሉ ምስክሮች ተሰምተዋል።

አዲስ አበባ አገር ስብከት ገቢው ከፍተኛ በመሆኑ፣ ውዝግብ፣ ሽኩቻ የሚበዛበት ሆኖ መቆየቱን የመሰከሩት እንደሚሉት ከሆነ በሲኖዶስ ውስጥ ከበድ ያለ ገቢ ባለበት አቅጣጫ ለመሰለፍ እጅ መንሻው ለጉድ ነው።

በዚህ ሁሉ የቅድስና ትብትብ ውስጥ ያለችውና የአምልኮ አጸዷ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ተቸርችሮ ጸዳሏን በሚገፏት የተከበበችው ቤተክርስቲያን ለዚህ ሁሉ የተዳረገችው በሯን ለመዝጋት የሚያስችል ጽዳት ያላቸው መሪዎች ስለሌሏት እንደሆነ በተደጋጋሚ ይገለጻል።

ከውስን ደጋግ አባቶች በስተቀር ጥቅም ላይ የተንጠለጠሉት ወገኖች ራሳቸውን ሳይሆን ቤተክርስቲያንንም ባልተገባ ስፍራ እንድትሆን አድርገዋታል። ነብሳቸውን ይማረውና አለቃ አያሌው “እንኳንም አይኔ አሳወርከኝ። አመስግንሃለሁ” ሲሉ በሕይወት ዘመናቸው ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ቤተክርስቲያን ንግሥ ላይ ሲያስተምሩ እያለቀሱ” እኔ በምሰማው ልፈነዳ ደርሻለሁ። እናንተ ከመስማትም አልፎ እያያችሁ እንዴት ቻላችሁት” ሲሉ ስለ መቆሸሽ አስተምረው እንደነበር የሚያስታውሱ፣ ሲኖዶስ ይህን አጋጣሚ ተጠቅሞ “ቤተመንግሥት ውረሩ፣ የሰማዕት ሞት ሙቱ” በሚል የስልጣን ጥማት ያሰከራቸው ክፍሎች ለሚያራግቡት እልቂት ጋባዥ ፉከራ ተላቀው ራሳቸው እንዲመለከቱ ይመክራሉ።

መንግሥትም ዕልህ መጋባቱን ትቶ በሆደ ሰፊነት ልቅ የሆኑትን በማረቅ ቤተክርስቲያኒቱ ባላት ደንብና መተዳደሪያ መሠረት ችግሯን እንድትፈታ ሚናውን እንዲጫወት በርካቶች እየጠየቁ ነው። የዓመጽ ጥሪውን ንቆ፣ ሰላም የሚሰፍንበትን መንገድ ባስቸኳይ በመፈለግ ዕልባት እንዲገኝ ሊፈጥን እንደሚገባው የሚያሳስቡ ወገኖች መንግሥት ውስጥ ያለው መዥጎርጎር ሊታረም እንደሚገባው አመልክተዋል።

ይህንን ልዩነትና ወይም አለመግባባት ተንተርሶ “አርቲስት ነን፣ ኮባ ለፍላፊ ነን፣ ማስታወቂያ ሠራተኛ ነን፣ የባንክ ካሸር ነን፣ የዩትዩብ ተከፋይ ነን …” እያሉ ከየሥርቻው እየተጠራሩ “ግፋ በለው” የሚሉ በማያተርፉበት ጨዋታ ዝም ብለው ነገር ማንቀርቀባቸው ጊዜው የመረጃ ዘመን ነውና የከፋ ነገር ቢከሰት አብረው ሲጠቀሱ ከመኖር የዘለለ ጥቅም አያስገኝላቸውምና ቢተውት የሚሉ አሉ።

“ተጸዕኖ ፈጣሪ ነን” ብለው ራሳቸውን የቆለሉ ጥቁር ለብሰው “ሐዋሪያዊ የፖለቲካ መመሪያ” ሲሰጡ “አብዛኛው” የሚባሉ አድፋጮች ለፈገግታ እንደሚጠቀሙባቸው፣ በተለይ ውጭ ያሉትን “ሻሸመኔ ናና ተሰዋ” ሲልም በማኅበራዊ ሚዲያ የተሳለቁባቸው ጥቂት አይደሉም። አንዳችም የማኅበረሰብ ሥራና ጥቅም ላይ ፈጠራቸውን ያላኖሩ፣ የማኖር ብቃትም የሌላቸው፣ አገር በተወረችበት ወቅት ቤት ዘግተው ሃድራ ሲያሞቁ የነበሩ፣ ዛሬ ወጥተው ምስኪን መእመናን ወደ እሳት ለመንዳት ሲነደፋደፉ ማየት እጅግ አሳዛኝ እንደሆነ የሚገልጹ “ኢትዮጵያ የተሠራችበትን ውቅሯን ለሚረዳና የክልሎችን ሕገ መንግሥታዊ አቅም የሚያውቁ በዚህ መልኩ መንግሥትን ለመናድ ማሰባቸው መጨረሻው ሃዘን እንደሚሆን ይወቁት” እያሉ ነው። (ፎቶ፤ በስሪ ላንካ የተደረገው የቤተ መንግሥት ወረራ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Politics Tagged With: Ethiopian Orthodox Church, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. afuye says

    February 13, 2023 10:02 am at 10:02 am

    As always your are biased and partial, I think the government has plenty platforms and I don’t think needs your help.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule