• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ

December 13, 2022 09:06 am by Editor Leave a Comment

ከ30 ሚሊየን ብር በላይ ለግል ጥቅማቸው አውለዋል የተባሉ የብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት የኮንስትራክሽን እና ሎጂስቲክስ ም/ዳይሬክተር የሆኑት ተስፋዬ ደሜን ጨምሮ በአራት የአገልግሎቱ ሰራተኞች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ።

በኢፌዲሪ ፍትሕ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጀነራል ዐቃቤ ሕግ በብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ስም 29 ሺሕ 200 ኩንታል ሲሚንቶ ከኹለት ፋብሪካዎች ገዝተው ለግለሰቦች በመሸጥ ከ30 ሚሊየን ብር በላይ ለግል ጥቅማቸው ባዋሉ የአገልግሎቱ የኮንስትራክሽን እና ሎጂስቲክስ ም/ዳይሬክተርን ጨምሮ በአራት ሰራተኞች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ መስርቶባቸዋል፡፡

የዐቃቤ ህግ የክስ መዝገብ እንደሚያስረዳው፤ ተከሳሾች በብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ውስጥ 1ኛ ተስፋዬ ደሜ በብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት የኮንስትራክሽን እና ሎጂስቲክስ ም/ዳይሬክተር፣ 2ኛ አሸናፊ ተስፋዬ የኮንስትራክሽን እና ሎጂስቲክስ ግዢ ዋና ክፍል ሃላፊ፣ 3ኛ ቱጅባ ቀልቤሳ እና 4ኛ ተከሳሽ ሙስጠፋ ሙሳ የግዢ ባለሙያ ናቸው፡፡

ግለሰቦቹ በተቆሙ ውስጥ ሲሰሩ ተገቢ ያልሆ ጥቅም ለማግኘት በማሰብ በ2013 እና 2014 በተለያዩ ወራት በብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ምንም አይንት ሲሚንቶ ግዢ ባልተፈፀመበት ሁኔታ በሥሙ ሲሚንቶ ከፋብሪካዎች በአነስተኛ ዋጋ በመግዛትና ገበያ ላይ በከፍተኛ ዋጋ በመሸጥ ህገ-ወጥ ጥቅም ለማግኘት በማሰብ፤ 1ኛ ተከሳሽ አገልግሎቱ የሲሚንቶ ግዢ ፍላጎት ሳይኖረው እንዳለው በማስመሰል ለአገልግሎቱ አስቸኳይ የግንባታ ሥራ የሚውል በድምሩ 29 ሺሕ 200 ኩንታል ሲሚንቶ ሽያጭ ከደርባና ዳንጎቴ ሲሚንቶ ፋብሪካዎች እንዲፈፀም በ3ኛ እና በ4ኛ ተከሳሽ ሥም ደብዳቤዎችን በመፃፍ፣ በተከሳሾች የግል አካውንት ገቢ በማድረግ፣ ወደ ፋብሪካችሁ ገቢ በሆነው ገንዘብ ለመስሪያ ቤታችን የሲሚንቶ ሽያጭ እንድትፈፀሙ በማለት ደብዳቤ በመፃፍ በመስሪያ ቤቱ ስም ግዢ እንዲፈፀም እና ሲሚንቶው ወደ መስሪያ ቤቱ ገቢ ሳይደረግ አየር ላይ ተሸጦ ለግል ጥቅሙ እንዲውል ያደረገ መሆኑ ተገልጿል።

በተመሳሳይ 2ኛ ተከሳሽም 1ኛ ተከሳሽ ያለምንም ግዢ ፍላጎት በተቋሙ ሥም ግዢ እንዲፈፀም የፃፋቸውን ደብዳቤዎች 3ኛ እና 4ኛ ተከሳሾች ለደርባ እና ዳንጎቴ ሲሚንቶ ፋብሪካዎች እንዲያደርሱ እና ተከሳሾች በግል አካውንታቸው ገቢ በሚያደርግላቸው ገንዘብ ከየፋብሪካዎቹ የሲሚንቶ ግዢ እንዲፈፅሙ በመንገርና ደብዳቤዎቹን በመስጠት በተቋሙ ስም የተገዛውን 29 ሺሕ 200 ኩንታል ሲሚንቶ በመሸጥ ለግል ጥቅማቸው እንዲውል ያደረገ መሆኑ ተገልጿል፡፡

3ኛ እና 4ኛ ተከሳሾች ደግሞ፤ ለደርባ እና ዳንጎቴ ሲሚንቶ ፋብሪካ በተቋሙ የሲሚንቶ ግዢ ፍላጎት ሳይኖር ለደርባ እና ዳንጎቴ ሲሚንቶ ፋብሪካ በ3ኛ ተከሳሽ ሥም 7 ሺሕ 200 ኩንታል፣ በ4ኛ ተከሳሽስም 22 ሺሕ ኩንታል ሲሚንቶ፣ በድምሩ 29 ሺሕ 200 ኩንታል ሲሚንቶ ግዢ እንዲፈፀም በተፃፈ የተቋሙ ደብዳቤ አማካኝነት በግል አካውንታቸው በሚገባ ከፍተኛ ገንዘብ ግዢ በመፈፀም ሲሚንቶው ወደ ተቋሙ ገቢ ሳይሆን አየር በአየር በመሸጥ ለግል ጥቅማቸው እንዲውል ያደረጉ መሆኑ በክሱ ተዘርዝሯል።

በአጠቃላይ ተከሳሾች በጥቅም በመመሳጠር ምንም አይነት የግዢ ፍላጎት ሳይኖር በአገልግሎቱ ሥም በፃፏቸው ደብዳቤዎች ከዳንጎቴ እና ደርባ ሲሚንቶ ፋብሪካዎች በድምሩ 29 ሺሕ 200 ኩንታል ሲሚንቶ በመግዛት ወደ ተቋሙ ገቢ ሳያደርጉ ገበያ ላይ በመሸጥ 30 ሚሊዮን 99 ሺሕ 360 ብር ጥቅም ያገኙ በመሆኑ፤ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈፀሙት በስልጣን አላግባብ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ተከሰዋል፡፡

ተከሳሾች የተከሰሱበት ክስ በችሎት ደርሷቸው ክሱ የተነበበላቸው ሲሆን ተከሳሾችም የክስ መቃወሚያ ካላቸው በጽሁፍ እንዲያቀርቡ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ወንጀል ችሎትም ለታሕሳስ 7 ቀን 2015 ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡

ይህ ዘገባ ተከሳሾች ላይ ክስ ስለመመስረቱ ለማሳወቅ የቀረበ ሲሆን፤ የተከሳሾችን ከፍርድ በፊት እንደ ንፁህ የመገመት ህገ-መንግስታዊ መብትን እንደሚያከብር ፍትሕ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ አመላክቷል። (አዲስ ማለዳ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: anti-corruption campaign, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule