• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የዳያስፖራ ትህነጎች ቀጣይ አጀንዳ

September 6, 2021 07:37 pm by Editor 2 Comments

የትግራይ ዲያስፖራ የሳይበር ቡድን (Diaspora Cyber Team) ትላንት (Sep 5) ስብሰባ ነበራቸው።የእኛ ሰዎችም የሳይበር ውይይታቸውን ሰብረው በመግባት ታድመው ወጥተዋል።

አጀንዳዎቹ:-

1- አለም አቀፍ ጫናዎችን በድጋሜ በአዲስ መልክ እንዴት እንፍጠር?

2- ትግራይ ውስጥ ቤተሰቦቻችን በርሃብ እያለቁ ነው። ለዚህስ መፍትሄው ምንድነው?

3- ህወሓት/የትግራይ መንግስት ምን ማድረግ አለበት? የሚሉ ናቸው።

የተስማሙባቸው ነጥቦች:-

1ኛ) ጦርነቱ ትግራይ መሬት ላይ በነበረበት ወቅት ተዘረፍን ፣ ሴቶች ተደፈሩ ፣ በጅምላ ተገደልን … ብለን የአለም አቀፍ መንግስታት ጫና እንዲፈጥሩ አድርገናል። አሁን ያንን መንገድ መከተል አዋጭ ስላልሆነ 5.2 ሚሊዮን ህዝብ በርሃብ እየተጎዳና እየሞተ እንደሆነ ፣ ወደ ትግራይ እየገባ ያለው የእርዳታ እህልም እጅግ አነስተኛ እንደሆነ ፣ አንድ ሰው የሚመግብ እህል ለአስር ሰው እየተከፋፈለ እንደሆነና እጅግ አስከፊ ርሃብ እንደተከሰተ አድርገን ለአለም እንጩህ። አጋሮቻችንንም በማንቃት ጫና እንፍጠር።

2ኛ) ይህን ከፈጠርን በሗላ የሱዳን መንግስት ጋር በመነጋገር እና የሱዳን መንግስትም ከድሮው በተሻለ  ተፅኖ እንዲፈጥር  በማድረግ እርዳታዎች  በሱዳን በኩል ሊገቡ የሚችሉበትን አማራጭ እስከቻልነው (to the maximum) መሞከር።

3ኛ). የሱዳን መንግስት አሁን ላይ በሚፈለገው መጠን ኢትዮጵያ ላይ ተፅኖ እየፈጠረ ስላልሆነ በተሻለ አግባብ የሚጠናከርበት ሁኔታ ላይ የህወሃት ወኪሎች በድጋሜ እንዲወያዩ ማድረግ።

4ኛ) ህወሓት ማርኮ ያስቀመጣቸው ወታደሮች ላይ እርምጃ ይውሰድ /በተጠና አግባብ/ then አሁን የትግራይ ሃይልን እያጠቃ ያለው መከላከያ ላይ  መሸማቀቅና ፍርሃት ይፈጠራል ብለዋል። 

በማጠቃለያቸውም:-

–  የፕሮፖጋንዳ ብልጫ በኢትዮጵያውያን የሳይበር ቡድን cyber team እየተወሰደብን ስለሆነ እሱን መቀልበስና አለም ፊቱን ወደ ትግራይ ጉዳይ በድጋሜ እንዲያዞር እናደርጋለን።

–  ዘመቻው የሚጀመርበት ጊዜና አጀንዳዎች በቅርብ ይፋ ይደረጋሉ።

–  ሃገር ቤት ካሉ አካላት ጋር በመነጋገር ተጨማሪ ሃሳቦች ይመጣሉ ብለዋል።

ትዝብት:-

– በአብዛኛው ተሰብሳቢ ቤተሰቦቻችን በርሃብ እያለቁ ነው፣ ሱዳን በሚገባ አልረዳችንም፣ ወጣቱ እና ህፃናቱ በጦርነት እያለቀ ነው፣ ህወሓት መፍትሄ ማምጣት አለበት … ወዘተ በማለት ሲያለቃቅሱ ነው የዋሉት። በብዙዎቹ ላይ ተስፋ መቁረጥ ይታያል። ብዙ ወቀሳዎች ነበሩበት!

– “ትግሉ ምድር ላይ ያለው ጦርነት ብቻ ስላይደለ የኢትዮጵያ Cyber team ልንበረታ ይገባል” ብለዋል ውይይቱን ሰብረው የታደሙ ኢትዮጵያውያን።

በመሆኑም እነዚህ ከላይ የተጠቀሱትን ሻጥሮች እና ሴራዎች ከወዲሁ ተደራጅቶ ማጋለጥ ከሁሉም ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የሚጠበቅ ብሔራዊ ግዴታ ይሆናል! ኢትዮጵያውያን በሳይበር ብልጫ እየወሰዱ መሆናቸው አበረታች ቢሆንም አሁንም የተቀናጀ የሳይበር ውጊያ እስከመጨረሻው ማካሄድ የግድ ነው!!!! እውነት ያሸንፋል! ኢትዮጵያ ታሸንፋለች! (Dejene Assefa)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, rapist tplf, tplf children soldiers, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Miherete Tibebe says

    September 7, 2021 04:04 am at 4:04 am

    ዘመናችንን በሽብርና ሽብርተኛ በመጨናነቅ ማሳለፍ የለብንም! የአለም ማህረስበ ተባብሮ ማስወገድ አለበት! መንግስታትም ይህን አይነት ቡድንን በድብቅ ከመገደፍ መታቀብ አለባቸው! የአሸባሪነት መነሻ ለግል ጥቅም መስገብገብና አላማ የሌለው ቡድን ስብስብ ስለሆነ ለዓለም ስልጣኔ ከፍተኛ እራስ ምታት ነው!

    Reply
  2. gihaile says

    September 7, 2021 10:35 am at 10:35 am

    ሕወኣት ምንጊዜም ቢሆን መሸነፍ ኣይችልም ያበቃለት ድርጅት ነው። ያልሞተው ኣሳቡ ነው። በሕዝቡ ውስጥ ያለው ሃሳብ የመገንጠል ሃሳብ በሶስት ተከፍሎኣል። ከኢትዮጵያን ጋር መኖር ከ51% በላይ ነው። በዚህ መካከል ትግራይ ነፃ ትውጣ የሚለው የጂንታው ቤተሰቦችና ጁንታው ያሰለጠናቸው ለስራው ይጠቅመኛል ያላቸው በውጭ የሚገኙ ምሁራን ናቸው። የሲ.ኣይ .ኤ ምልምሎቹ ጁንታዎች እጅግ ብዙ ስልጠና የወሰዱ በመሆኑ ብዙ ሙከራዎቻቸው ያልተሳኩ በመሆኑ በሞራል ውድቀት ውስጥ ናቸው። ክፋትንና ጥፋትና ዓላማው ኣድርጎ የተነሳ ማንኛዎም ሃይል ኣሸንፎ ኣያውቅም ማሸነፍም ኣይችልም። በኣሁኑ ሰዓት ኣሜሪካ፣እንጎሊዝ፣ግብፅ የጁንታው ደጋፊዎች በራሳቸው የውስጥና የውጭ ችግር ተውጠዋል። ግራ ተጋብተዋል የሕወኣቱ የምስራቅ ኣፍሪካ የምስጥር ኣማካሪ ኤርማን ኮሄንም ሚሹኑን ጨርሶ መፅሓፉን በመፃፍ ስራውን አጠናቆኣል ከእንግዲህ በኋላ የወደቀውንና የሞተውን ሕወኣት እንደገና ለማንሳት ኣይጥርም ሆሮማይ። ድል ለኢትዮጵያና ለትግራይ ሕዝብ። እንኳንም ለ2014 አዲሱ ኣመት በሰላም አደረሳችሁ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule