• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የዳያስፖራ ትህነጎች ቀጣይ አጀንዳ

September 6, 2021 07:37 pm by Editor 2 Comments

የትግራይ ዲያስፖራ የሳይበር ቡድን (Diaspora Cyber Team) ትላንት (Sep 5) ስብሰባ ነበራቸው።የእኛ ሰዎችም የሳይበር ውይይታቸውን ሰብረው በመግባት ታድመው ወጥተዋል።

አጀንዳዎቹ:-

1- አለም አቀፍ ጫናዎችን በድጋሜ በአዲስ መልክ እንዴት እንፍጠር?

2- ትግራይ ውስጥ ቤተሰቦቻችን በርሃብ እያለቁ ነው። ለዚህስ መፍትሄው ምንድነው?

3- ህወሓት/የትግራይ መንግስት ምን ማድረግ አለበት? የሚሉ ናቸው።

የተስማሙባቸው ነጥቦች:-

1ኛ) ጦርነቱ ትግራይ መሬት ላይ በነበረበት ወቅት ተዘረፍን ፣ ሴቶች ተደፈሩ ፣ በጅምላ ተገደልን … ብለን የአለም አቀፍ መንግስታት ጫና እንዲፈጥሩ አድርገናል። አሁን ያንን መንገድ መከተል አዋጭ ስላልሆነ 5.2 ሚሊዮን ህዝብ በርሃብ እየተጎዳና እየሞተ እንደሆነ ፣ ወደ ትግራይ እየገባ ያለው የእርዳታ እህልም እጅግ አነስተኛ እንደሆነ ፣ አንድ ሰው የሚመግብ እህል ለአስር ሰው እየተከፋፈለ እንደሆነና እጅግ አስከፊ ርሃብ እንደተከሰተ አድርገን ለአለም እንጩህ። አጋሮቻችንንም በማንቃት ጫና እንፍጠር።

2ኛ) ይህን ከፈጠርን በሗላ የሱዳን መንግስት ጋር በመነጋገር እና የሱዳን መንግስትም ከድሮው በተሻለ  ተፅኖ እንዲፈጥር  በማድረግ እርዳታዎች  በሱዳን በኩል ሊገቡ የሚችሉበትን አማራጭ እስከቻልነው (to the maximum) መሞከር።

3ኛ). የሱዳን መንግስት አሁን ላይ በሚፈለገው መጠን ኢትዮጵያ ላይ ተፅኖ እየፈጠረ ስላልሆነ በተሻለ አግባብ የሚጠናከርበት ሁኔታ ላይ የህወሃት ወኪሎች በድጋሜ እንዲወያዩ ማድረግ።

4ኛ) ህወሓት ማርኮ ያስቀመጣቸው ወታደሮች ላይ እርምጃ ይውሰድ /በተጠና አግባብ/ then አሁን የትግራይ ሃይልን እያጠቃ ያለው መከላከያ ላይ  መሸማቀቅና ፍርሃት ይፈጠራል ብለዋል። 

በማጠቃለያቸውም:-

–  የፕሮፖጋንዳ ብልጫ በኢትዮጵያውያን የሳይበር ቡድን cyber team እየተወሰደብን ስለሆነ እሱን መቀልበስና አለም ፊቱን ወደ ትግራይ ጉዳይ በድጋሜ እንዲያዞር እናደርጋለን።

–  ዘመቻው የሚጀመርበት ጊዜና አጀንዳዎች በቅርብ ይፋ ይደረጋሉ።

–  ሃገር ቤት ካሉ አካላት ጋር በመነጋገር ተጨማሪ ሃሳቦች ይመጣሉ ብለዋል።

ትዝብት:-

– በአብዛኛው ተሰብሳቢ ቤተሰቦቻችን በርሃብ እያለቁ ነው፣ ሱዳን በሚገባ አልረዳችንም፣ ወጣቱ እና ህፃናቱ በጦርነት እያለቀ ነው፣ ህወሓት መፍትሄ ማምጣት አለበት … ወዘተ በማለት ሲያለቃቅሱ ነው የዋሉት። በብዙዎቹ ላይ ተስፋ መቁረጥ ይታያል። ብዙ ወቀሳዎች ነበሩበት!

– “ትግሉ ምድር ላይ ያለው ጦርነት ብቻ ስላይደለ የኢትዮጵያ Cyber team ልንበረታ ይገባል” ብለዋል ውይይቱን ሰብረው የታደሙ ኢትዮጵያውያን።

በመሆኑም እነዚህ ከላይ የተጠቀሱትን ሻጥሮች እና ሴራዎች ከወዲሁ ተደራጅቶ ማጋለጥ ከሁሉም ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የሚጠበቅ ብሔራዊ ግዴታ ይሆናል! ኢትዮጵያውያን በሳይበር ብልጫ እየወሰዱ መሆናቸው አበረታች ቢሆንም አሁንም የተቀናጀ የሳይበር ውጊያ እስከመጨረሻው ማካሄድ የግድ ነው!!!! እውነት ያሸንፋል! ኢትዮጵያ ታሸንፋለች! (Dejene Assefa)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, rapist tplf, tplf children soldiers, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Miherete Tibebe says

    September 7, 2021 04:04 am at 4:04 am

    ዘመናችንን በሽብርና ሽብርተኛ በመጨናነቅ ማሳለፍ የለብንም! የአለም ማህረስበ ተባብሮ ማስወገድ አለበት! መንግስታትም ይህን አይነት ቡድንን በድብቅ ከመገደፍ መታቀብ አለባቸው! የአሸባሪነት መነሻ ለግል ጥቅም መስገብገብና አላማ የሌለው ቡድን ስብስብ ስለሆነ ለዓለም ስልጣኔ ከፍተኛ እራስ ምታት ነው!

    Reply
  2. gihaile says

    September 7, 2021 10:35 am at 10:35 am

    ሕወኣት ምንጊዜም ቢሆን መሸነፍ ኣይችልም ያበቃለት ድርጅት ነው። ያልሞተው ኣሳቡ ነው። በሕዝቡ ውስጥ ያለው ሃሳብ የመገንጠል ሃሳብ በሶስት ተከፍሎኣል። ከኢትዮጵያን ጋር መኖር ከ51% በላይ ነው። በዚህ መካከል ትግራይ ነፃ ትውጣ የሚለው የጂንታው ቤተሰቦችና ጁንታው ያሰለጠናቸው ለስራው ይጠቅመኛል ያላቸው በውጭ የሚገኙ ምሁራን ናቸው። የሲ.ኣይ .ኤ ምልምሎቹ ጁንታዎች እጅግ ብዙ ስልጠና የወሰዱ በመሆኑ ብዙ ሙከራዎቻቸው ያልተሳኩ በመሆኑ በሞራል ውድቀት ውስጥ ናቸው። ክፋትንና ጥፋትና ዓላማው ኣድርጎ የተነሳ ማንኛዎም ሃይል ኣሸንፎ ኣያውቅም ማሸነፍም ኣይችልም። በኣሁኑ ሰዓት ኣሜሪካ፣እንጎሊዝ፣ግብፅ የጁንታው ደጋፊዎች በራሳቸው የውስጥና የውጭ ችግር ተውጠዋል። ግራ ተጋብተዋል የሕወኣቱ የምስራቅ ኣፍሪካ የምስጥር ኣማካሪ ኤርማን ኮሄንም ሚሹኑን ጨርሶ መፅሓፉን በመፃፍ ስራውን አጠናቆኣል ከእንግዲህ በኋላ የወደቀውንና የሞተውን ሕወኣት እንደገና ለማንሳት ኣይጥርም ሆሮማይ። ድል ለኢትዮጵያና ለትግራይ ሕዝብ። እንኳንም ለ2014 አዲሱ ኣመት በሰላም አደረሳችሁ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule