• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ገንዘብና ሥውር እጆች ተዋናይ የሆኑበት የጋምቤላ የርዕሰ መስተዳድር ምደባ

November 2, 2018 07:24 pm by Editor 3 Comments

ተጠናቀቀ በተባለው የጋምቤላ ክልል ግምገማ የክልሉን ርዕሰ መስተዳድርና ምክትል ለመሾም የገንዘብ ኃይል ከፍተኛ ተጽዕኖ እያደረገ መሆኑ ተሰማ። ግምገማውን እንዲመሩ የተመደቡት ግለሰቦች የክልሉን ርዕሰ መስተዳድር ምደባ በተመለከተ ከሌሎች ጋር በመሆን በገንዘብ ኃይል የሚፈልጉትን ለመሾም ጥረት እያደረጉ መሆናቸው እየተነገረ ነው።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የጋምቤላ ክልል ነዋሪዎች “ጋትሉዋክና ተባባሪዎቻቸው በሙሉ ለፍርድ መቅረብ አለባቸው” ማለታቸውን ጠቅሶ በክልሉ የተንሰራፋውን ግፍና ሙስና (ሌብነት) በተመለከተ ሰፋ ያለ ዘገባ ካወጣ በኋላ የክልሉን ርዕሰ መስተዳድር ለመሾም በታቀደው ድብቅ አጀንዳ ላይ ችግር መፈጠሩ ተሰምቷል።

ለአሥር ቀናት የተካሄደውን ግምገማ የመሩትን በተመለከተ ጎልጉል ዘገባውን ሲያቀርብ “ግምገማውን እንዲመሩ ከፌዴራል መንግሥት የተወከሉት ፈቃዱ ተሰማ እና ተፈራ ድሪቦ ግምገማው ከመጠናቀቁ በፊት በጋትሉዋክና በሰናይ ምትክ ዑመድ ኡጁሉ የጋህአዴን ሊቀመንበር፤ ታንኩዌይ ጆክ ምክትል አድርገው አስመርጠዋል። ሆኖም ሁለቱ ከፌዴራል የተወከሉትን የግምገማ መሪዎች በርካታ የተዓማኒነት ጥያቄዎች የሚቀርብባቸው ብቻ ሳይሆኑ ምናልባትም የጋትሉዋክን ዓላማ በማሳካት ሰፊ ሚና የተጫወቱ ናቸው ተብለው በአንዳንዶች ዘንድ ይወቀሳሉ” ብሎ ነበር።

ግምገማው ከመጠናቀቁ በፊት የግምገማው መሪዎች የክልሉ ርዕሰ መስተዳድርና ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሹመት መወሰን አለበት በሚል ያቀረቡት አጀንዳ በስብሰባው ላይ ከፍተኛ አለመግባባትን ፈጥሮ እንደነበር ጎልጉል ከተሰብሳቢዎቹ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ፈቃዱ ተሰማ እና ተፈራ ድሪቦ የተባሉት የግምገማው መሪዎች የጋትሉዋክ ሚስት ወንድምና የፓርቲው (ጋሕአዴን) ምክትል ሊቀመንበር እንዲሆኑ የተመረጡትን ታንኩዌይ ጆክ ሮምን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር፤ የፓርቲውን ሊቀመንበር ዑመድ ዑጁሉን ደግሞ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እንዲሆኑ ሃሳብ ያቀርባሉ።

ይህንን ከአሠራር ውጪ የሆነ ሃሳብ ከሊቀመንበሩ ሌላ የስብሰባው ተሳታፊዎች አጥብቀው ይቃወማሉ። ያቀረቡትም መከራከሪያ በኢህአዴግ ድርጅታዊ አሠራር መሠረት የፓርቲው ሊቀመንበር የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ይሆናል፤ ሆኖም ሊቀመንበሩ በፌዴራል ደረጃ ከፍተኛ ሥልጣን ካለውና ክልሉን ማስተዳደር የማይችል ከሆነ ብቻ ነው ምክትሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር የሚሆነው፤ በአማራ፣ በኦሮሚያ፣ በደቡብ፣ በሶማሊ ክልሎች የተደረገው ይኸው ነው፤ ከዚህ ውጪ የሆነ ምደባ በጋምቤላ ማድረግ ሕዝቡን መናቅ ብቻ ሳይሆን ክልሉን ለከፍተኛ ብጥብጥ የሚዳርግ ነው፤ ሕዝቡ የሚፈልገው መሪ ሊሾምለት ይገባል የሚል ነበር።

በዚህ ወቅት የግምገማው መሪዎች ወደ ክልላችሁ ሄዳችሁ ከሕዝባችሁ ጋር ተነጋግራችሁ ጉዳዩን ፍቱት በማለት ለግምገማ የተጠራውን ስብሰባ ያጠናቅቃሉ። ከግምገማው መጠናቀቅ በኋላ ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ ላይ አዳዲሶቹ የፓርቲው አመራሮች ሂስና ግለሂስ ማድረጋቸውን ገለጾ “በዚህ መሠረት ሶስት የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትን እስከሚቀጥለው ጉባዔ ድረስ ከማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ሲያግድ አንድ የሥራ አስፈፃሚ አባልን ደግሞ ወደ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት እንዲወርድ” መወሰኑን አስታወቀ።

የድርጅቱ መግለጫ ይፋ ከሆነ በኋላ የተገኘው መረጃ እንደሚጠቁመው ከድርጅቱ የታገዱትና እርምጃ የተወሰደባቸው አባላት እንደተባለው በሂስና ግለሂስ ምክንያት ሳይሆን ኢፍትሓዊ የሆነውን የርዕሰ መስተዳድር አመዳደብ የተቃወሙ ነበሩ። ከህወሓትና ከሌሎች በርካታ በጥቅም ከተሳሰሩ ጋር የተወሳሰበውን የጋትሉዋክን አመራር በሌላ መልኩ ለማስቀጠል የተቀነባበረ ሤራ አንዱ አካል እንደሆነ ለጎልጉል የደረሰው መረጃ ያመለክታል። እነዚህ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አጠራር “ሌቦች” የሚባሉትና “የሌብነት” ሥራቸው እንዳይጋለጥ የሚፈልጉ በአገር ውስጥና በውጪ የሚገኙ ኃይሎች፤ በጋምቤላ የሚፈለገው ለውጥ እንዳይመጣና አሁንም በግፍና በሌብነት የተሳሰረው ሠንሠለት እንዳይበጠስ እስከ 10 ሚሊዮን ብር እንደመደቡ ይህንንም ለአስፈጻሚዎቹ እንዳስረከቡ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ያስረዳሉ።

የጋሕአዴንን ምክትል ሊቀመንበር የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ለማድረግ የታቀደው ሤራ ከከሸፈ በኋላ አዲሶቹ አመራሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት እንደሚፈለጉና ወደ አዲስ አበባ እንዲመጡ ጥሪ ይደርሳቸዋል። ጥሪው ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት ዕውቅና ውጪ የተደረገ መሆኑን ሊቀመንበሩ ዑመድ ኡጁሉ ያውቁት አዲስ አበባ ሲደርሱና የስብሰባው ገምጋሚዎች ከሌሎች ወታደራዊና የደኅንነት አባላት ጋር ጠርተው ሲያነጋግሯቸው ነው።

ወደ አዲስ አበባ እንዲመጡ የተደረጉት አመራሮች በተለይ ሊቀመንበሩ ከፍተኛ ዛቻና ማስፈራሪያ የተሰጣቸው ሲሆን ይህም ዋንኛ ምክንያት ምክትል ሊቀመንበርና የጋትሉዋክ ሚስት ወንድም የሆኑትን ታንኩዌይ ጆክ ሮምን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዲሆኑ እንዲቀበሉ ሲሆን ሊቀመንበሩ ግን በአቋማቸው ፀንተዋል። ከሕዝባቸውና ከፓርቲው አሠራር ውጪ የሚደረገውን ምደባ እንደማይቀበሉ ለተናገሩት ሊቀመንበር ተጨማሪ ዛቻና ማስፈራሪያ ተሰጥቷቸው ቅዳሜ ጥቅምት 24፤ 2011 ለሌላ ስብሰባ እንዲመጡ ተነግሯቸው ከስብሰባው ወጥተዋል።

ይህንን በጋምቤላ ሕዝብ ላይ ያለፍላጎቱ ለማስቀጠል የሚደረገው የህወሓትና የለውጡ ተቃዋሚዎች ሤራ በፌዴራል መንግሥቱ ቀጥተኛ ጣልቃገብነት ካልተቀለበሰ በክልሉ ከፍተኛ ቀውስ እንደሚያስከትል ጎልጉል ያነጋገራቸው የክልሉ የቀድሞ አመራር ሥጋታቸውን ይገልጻሉ። በሌሎች ክልሎች በተለይ በሶማሊ ክልል ከተደረገው ያነሰ በጋምቤላ እንዲሆን መፍቀድ ለዓመታት መሬቱን እየተነጠቀ፣ ግፍ እየተፈጸመበት የኖረውን የጋምቤላ ሕዝብ ወገብ የሚሰብር ብቻ ሳይሆን ግፍ የመረረውን የክልሉን ወጣት ላልተፈለገ አመጽ መጋበዝ ነው ሲሉ እኚሁ ሰው ይናገራሉ። ከደቡብ ሱዳን ጋር የተቆራኘው የጋምቤላ ጉዳይ የክልሉን ሕዝብ ፍላጎት በሚያረካ መልኩ ካልተጠናቀቀ አሁንም በግፍ፣ በጉቦ፣ በማስፈራራትና በዛቻ የሚደረገው አሠራር በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ገና በሁለት እግሯ ባልቆመችውን ደቡብ ሱዳንና በቀጣናው ከፍተኛ አለመረጋጋት እንደሚፈጥር በብዙዎች ይታመናል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Gambella, gatluak, Left Column, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. ምንውየለት ፈንቴ says

    November 3, 2018 06:32 am at 6:32 am

    መቸ ነው ሃገሩ የባላገሩ የሚሆነው? ከዚህ ቀደም በጋምቤላ በ”የሠላምና የዲሞክራሲ ኮንፈረንስ” ስም በመጀመሪያ በአቶ ተፈራ ዋልዋ መሪነት የመጀመሪያው የክልሉ ፕሬዚደንት ከሥልጣን ወርደው ለእሥር ተዳርገዋል፡፡ ለሁለተኛ ጊዜ ደግሞ በአቶ አባይ ፀሐዬ መሪነት እንዲሁ ግምገማ ተደርጎ የክልሉ መሪዎች ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ተደርገዋል፡፡ እነሆ አሁን ደግሞ ሌላ ዙር ሹም ሽር፡፡ ከመሃል አገር ገምጋሚ ወደነዚህ ክልልሎች እየተላከ እስከመቼ ይሆን አውጪና አውራጅ የሚሆነው? በክልሉ የሚገኙ ፊደል የቆጠሩ ተወላጆች አሥር ወይ ሃያ አይሞሉም ማለት ነው? እነርሱ ስለሕዝባቸው ግድ የሚላቸው መቸ ነው? ቆም በለው የሚያስቡት መቸ ነው? ለነገሩ ጋምቤላ ብቻ ሣይሆን እንዲህ ዓይነት ተመሣሣይ ተግባራት በደቡብ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በሶማሌ ክልሎች በተደጋጋሚ ይፈፀማል፡፡ መቼ ይሆን እንዝህ ሰዎች ጡጦ የሚጥሉት?

    Reply
  2. Tesfa says

    November 4, 2018 01:18 pm at 1:18 pm

    የሻምበል ፍቅረስላሴ በቅርቡ ሰጡት በተባለው ውይይት ወያኔ ካልፈራረሰ ጤና የለም ሲሉ ይህኑ እይታ የሻቢያው መሪም ለሃገራቸው ጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ላይ ደግመውታል፡፡ መቀሌ ላይ የተሰገሰጉት የወያኔ የቀድሞ ባለስልጣኖች በተለያየ መንገድ የሚሰጡት አስተያየቶች ማን አለብኝ፤ አንተ ማን ነህ የሚል ለመሆኑ ሜቴክን የመዘበረው ጀኔራል ክንፈ በቅርቡ የሰጠውን አሳፋሪ ቃለ መጠየቅ መመልከት በቂ ይሆናል፡፡ የኢትዮጵያን የወደፊት ፈተናዎችን በሶስት ከፍለን ማየት እንችላለን።
    1. የወያኔ መሰሪ እጆችና በእጃቸው ያለ ሃብትና የጦር መሳሪያ የሚያመነጨው ክፋት – አዎን ጥቂቶች በለውጡ የመደመር ህሳቤ ባቡር ላይ እንደተሳፈሩ የሚያመላክቱ ነገሮች አሉ። ይሁን እንጂ እነዚህ ሃይሎች አብረው ለመዝለቅ እቅድ ስለለላቸው ከውስጥ በመሆን ነገርን ማሰናከላቸውን ይቀጥላሉ። በኢትዮጵያ ሶማሊያ፤ በጋምቤላና ቤኒሻንግሉ ወዘተ የሚቀሰቀሱ ግጭቶ ሁሉ በወያኔ የተዘዋዋሪ ተላላኪዎችና እንደ ኦነግ ባሉ የዘር ፓለቲካ አራማጆች የሚፈጠሩ ችግሮች ናቸው።
    2. ሌላው ሃበሣ አመንጪ ድርጅት ኦነግ ነው – ኦነግ በራሱ የፓለቲካ ምህዳር የሰከረ ኦሮሚያ የምትባል ሃገር አለች እያለ የውጭና የውስጡን ዓለም ሲያማታ የኖረ የህዝባችንን ሰቆቃ ያራዘመ አጥፊ ድርጅት ነው። ህቡዕ በሆኑ የአውሮጳና የሰሜን አሜሪካ ሃገሮች እየኖሩ ዛሬም የኦነግን ባንዲራ በማውለብለብ እኔን እዪኝ የሚሉት እነዚህ ጠባቦች ቢዘፈን የማይዘፍኑ ቢለቀስ የማያለቅሱ በራሳቸው ታቡር ብቻ ዳንኪራ የሚወርድ ተምረናል ብለው የደነቆሩ ስብስቦች ናቸው። ዛሬ የወለጋን ህዝብ የሚያምሱት እነርሱ ናቸው፡፡ ሲመቻቸው ከቤተክርሲቲያኖች፤ ሳይመቻቸው ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር በመተባበርና ንዋይ በመለመን ሃገርን ለማፍረሰ ከሚጥሩ ልበ ቢስ ሃገር በቀል አራሙቻ የፓለቲካ ድርጅቶች መካከል ኦነግ ቀዳሚ ስፍራውን ይይዛል። ኦነግ ሚኒሊክ ጡት ቆረጠ በማለት የወያኔን የከፋፍለህ ግዛው ተንኮል በቁሙ የጠጣ ድርጅት ሲሆን በአንጻሩ የራሱ ደጋፊዎች ያለምንም ፍርድ በጠራራ ጸሃይ ሰው ዘቅዝቀው የሚሰቅሉበት፤ ያለምንም መረጃ ሴትና ወንድ ልጅን በደቦ የሚደበድቡበት አለቅጥ የተጣመመ ፓለቲካ አራማጆች ናቸው።
    3. የኢትዮጵያን መበልጸግና መጎልበት በጥርጣሪ አይናቸው የሚመለከቱት የአረብ ሃገራት በተለይም ሳውዲዎችና ግብጽዎች ሃገር በቀል የሆኑ የፓለቲካና የሃይማኖት ድርጅቶችን በማገዝ የሃገራችን ሰላም እንዲደፈርስ ያደርጋሉ። በማድረግም ላይ ናቸው።
    እነዚህ ሶስት ሃይሎች የዛሬና የወደፊት የሃገሪቱ ፈተናዎች ናቸው። አዎን ቀንና ሃላፊ ጎርፍ የሚያመጣው አይታወቅምና በውሉ ተምኖ ችግራችን ከእነዚህ ብቻ የሚመነጭ ነው ብሎ ማመን ራስን ማጃጃል ይሆናል። ያልታለሙ ነገሮች ብቅ ሊሉ ይችላሉና።
    በቅርቡ የትግራይ የዮንቨርሲቲ ተማሪዎች ትግራይ ላይ እንመደብ ሌላ ክልል መሄድ አንፈልግም በማለት ያሰሙትን ተቃውሞ ሳነብ ምን ያህል የሃገራችን ፓለቲካ ወልጋዳ እንደሆነ አስገንዝቦኛል። ማንም ዜጋ በፈለገበት ቦታ በዜግነቱ ኮርቶና ተምሮ ሰርቶ የማይኖርባት ሃገር ባፍንጫዬ ትውጣ።

    Reply
  3. degusa says

    November 5, 2018 04:54 pm at 4:54 pm

    በርግጠኝነት እንስሳ እንኳን ካንተ የተሻለ ያመዛዝናል፡፡ደንቆሮ፡፡ኦነግ ድርጅት ነው፣ድርጅት ደግሞ በሰዎች ይወከላል፡፡ሰዎች ደግሞ ሁሉም መጥፎ ሁሉም ጥሩዎች ባይሆኑም የሌላውን መብት እስካልነኩ ድረስ ማንም ሰው የመሰለውን ሃሳብ የመያዝ መብት አለው፡፡አህያ ነፍጠኛ ለራስህ እምዬ እትዮጵያ ብለህ የሌለህ ታሪክና ተረት ይዘህ ስታቦካ እንዴት ኦሮሚያ ሚባል ሀገር አለ ይላል ብለህ አፍህን ትከፍታለህ፡፡ሃዳራው፡፡

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule