• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አቶ ለማ መገርሳ – በህወሃት የማስፈራሪያ አጣብቂኝ ውስጥ

January 10, 2020 01:03 am by Editor 3 Comments

ከለውጡ ሾፌሮች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ለማ መገርሳ የሽግግሩ ጊዜ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆኑ ጃዋር መሐመድ አጥብቆ ሲከራረከር ነበር። አቶ ለማ የፌዴራል ፓርላማ ተወካይ ባለመሆናቸው እርሳቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር እንዳይሆኑ የሚከለክላቸው መሆኑ የታወቀ ቢሆንም በወቅቱ ግን ጃዋር ከጓደኞቹ እነ ሕዝቅኤል ገቢሣ ጋር በመሆን “ኢህአዴግ አዲስ መመሪያ/ሕግ አውጥቶም ቢሆ አቶ ለማ ጠቅላይ ሚኒስትር ሊያደርጋቸው ይገባል” በማለት ሃሳብና መመሪያ ቢጤም ሲሰጥ ነበር።

ጃዋር ያለውና ያሰበው ሳይሆን አቶ ለማ በለውጡ ሙቀት ውስጥ ባሉበት ወቅት “እኔና ዐቢይን ሞት ብቻ ነው የሚለየን” በማለት የድርጅት ሊቀመንበርነታቸውን ለዶ/ር አብይ አሳልፈው በመስጠት ዐቢይ አህመድ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆን የበኩላቸውንና ድርጅታዊ ኃላፊነታቸውን ከባልደረቦቻቸው ጋር ሆነው እውን አደረጉ።

የሆሮ ጉድሩ ተወላጅ የሆኑት አቶ ለማ በዚህ ተግባራቸውና ከለውጡ መፈንዳት ጀምሮ ለህዝብ ባቀረቡት ዲስኩር የተወደዱትን ያህል ከህወሃት አፍቃሪዎችና ጭፍራዎች ዘንድ ግን ተቃውሞ በስፋት ይሰነዘርባቸው የጀመረው ወዲያው ነበር። በተለይም በኦሮሚያ የደኅንነት ቢሮ ሥልጣናቸው ወቅት የሰሩትን በመጥቀስ። 

ስለ አዲስ አበባ የሕዝብ አሠፋፈር (ዴሞግራፊ) የተናገሩት ቅጂ አደባባይ ከወጣ በኋላ ተቃውሞ እየከበባቸው የመጣው አቶ ለማ በዛው ቅጽበት ከጃዋር መሀመድ ጋር በየዕለቱ እንደሚገናኙና አብረው እንደሚሰሩ ከየአቅጣጫው መረጃዎች ይሰራጩ ጀመር። በዚያው መጠን ከዶ/ር ዐቢይ ጋር ልዩነት እንደፈጠሩ በተደጋጋሚ በተለያዩ የሚዲያ ማሰራጫዎችና ማህበራዊ ገጾች ተዘገበ። በዳያስፖራ የሚገኙትና ራሳቸውን ተንታኝ አድርገው የሰየሙ ዜናውን ዞሩበት። 

ከኦሮሚያ ርዕስመስተዳድርነታቸው ተነስተው ወደ መከላከያ ሚኒስትርነት የመዛወራቸው ሚስጢርም ይኸው የልዩነቱ ነጸብራቅ እንደሆነ ትርጉምና ትንታኔ እየቀረበበት ከሚዲያ ወደ ሚዲያ ተራባ። በመጨረሻም ራሳቸው አቶ ለማ በቪኦኤ ቀርበው ልዩነት እንዳላቸውና “እንደመር” እያሉ ሲፈክሩበት ከነበረው ሃሳብ ጋር መጣላታቸውን ይፋ አደረጉ።

በተለይም የብልጽግናን መመሥረት፣ የኢህአዴግ እህት ድርጅቶችና አጋር ድርጅቶች ውህደት እንደማይቀበሉ ሲናገሩ ተቃውሟቸውን በሚያሳምን መንገድ ባለማስረዳታቸው ሕዝብ ደነገጠ። መሠረታዊ ምክንያታቸው ምን ይሆን ሲል በማኅበራዊ ሚዲያ ክርክርና መላምት ማስቀመጥ ተጀመረ። 

የለውጡ ተጻራሪዎችና ጭፍን ነቃፊዎች፣ በተለይም የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር በፓርቲ ደረጃ፣ እንዲሁም ደጋፊ የማኅበራዊ ገጽ ጭፍሮቹ የአቶ ለማን ቃለ ምልልስ አጯጯሁት። “ብለን ነበር” ሲሉ የለውጡ ሃዲድ እንደተሰበረ፤ ባቡሩ አቅጣጫውን እንደሳተ አወጁ። 

የጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ከዘወትር ታማኝ ምንጮቹ ባገኘው መረጃ አቶ ለማ እዚህ ችግር ውስጥ የወደቁት ፈልገውና ወደው እንዲሁም የለውጡ የትግል አጋሮቻቸውን ለማስቀየም አስበው ሳይሆን ከፌደራሉ የመረጃና የደህንነት አጄንሲ (ደኅንነት) ጋር በጥምረት በሚሠራው የኦሮሚያ የስለላ መዋቅር ውስጥ በከፋ ሁኔታ ተነክረው ስለነበር ነው።

“ማበስበስ” በሚባለው በህወሃት ስልት ውስጥ በኦሮሞ ተወላጅ የኦነግ ታጋዮች፣ ደጋፊዎችና ተቃዋሚዎች ላይ ሲያከናውኑት የነበረው የስለላ ሪፖርት ሪኮርዶች ህወሃት እጅ አሉ። ህወሃት በክልሉ መሪ ሳይቀር “ሚስጢር እናወጣለን” በሚል የሚሰነዝሩት ዛቻ በአብዛኛው በአቶ ለማ ላይ ያነጣጠረ መሆኑንን የጎልጉል ዘጋቢ ለህወሃት ቅርብ የሆኑ ክፍሎችን ጠቅሶ ዘግቧል። ይህ የህወሃት ዛቻ በዶ/ር ዐቢይ ላይ ቢሆን ኖሮ መዛትም አያስፈልጋቸውም ነበር፤ ውሸት ፈጥሮ በሚያናፍሰው የዲጂታል ወያኔ መስተጋብራቸው ያለገደብ ያራግቡት ነበር።  

ከወራት በፊት “አቶ ለማ የኦሮሞ ተወላጆችን ሲያሳድድ የነበረ ዋናው ወንጀለኛ ነው” ሲል የህወሃት ደጋፊና ፕሮፓጋንዲስት የሆነው ዳንኤል ብርሃኔ፤ ጌታቸው አሰፋ ላይ የሚቀርበውን የነፍሰ በላነት ውንጀላ ለመከላከል ባቀረበው ጽሁፍ ላይ መጥቀሱ አይዘነጋም። ከዚያም በኋላ የብልጽግና ፓርቲ መቋቋሙን ተከትሎ ይኸው ሚስጢር ይፋ እናደርጋለን የሚለው ጉዳይ በስፋት ሲናፈስ የከረመውም ያለምክንያት አልነበረም።

በዚሁ ምክንያት አቶ ለማ ከኦሮሞ ህዝብ ሊነጥላቸው የሚችለው ይህ ሚስጢር እንዳይወጣ ኦዲፒን ወይም ብልጽግና ፓርቲን እንዲለዩና ህወሃት ጠፍጥፎ እየሠራቸው ካሉት የፌዴራል ኃይሎች ጋር እንዲዋሃዱ አማራጭ እንደቀረበላቸው ነው ለህወሃት ቅርብ የሆኑት ለጎልጉል መረጃ የሰጡት።

ህወሃት ከፌዴራል ኃይሎች ጋር በማበር ዳግም መንግሥት ለመሆን እንደሚሰራ በግልጽ ማሳወቁና አቶ ለማም ፓርቲያቸውን ጥለው ወደ ፌዴራል ኃይሎች የመንደርደራቸው ዜና ሌላ ምክንያት እንደሌለው የጎልጉል ዘጋቢ ካሰባሰበው መረጃ ለመረዳት ተችሏል።

አቶ ለማ መገርሳ ብልጽግና መቃወምና መደመርን በማጣጣል የተናገሩትን ቃለ ምልልስ “አንዱ የመጫወቻ ካርዴ ነው” ሲል ገልጾት የነበረው ጃዋር ረቡዕ ዕለት ለኤልቲቪ ባልደረባ ጋር ባደረገው ጭውውት መሳይ ቃለ መጠይቅ፣ በመጪው ምርጫ አቶ ለማን አካትተው ወደ ውድድር እንደሚገቡ በገደማዳሜና በሳቅ አረጋግጧል። ጃዋር ለጊዜው መናገር ያልፈለገው የፓርቲዎች ጥምረት እንደሚኖርም ጠቁሟል። ህወሃትም በጌታቸው ረዳ አማካይነት ጃዋር ከተቀላቀለው ኦፌኮ ጋር ህወሃት ግንባር የመፍጠር ሥራ እየሠራ መሆኑንን የበቀለ ገርባን ስም በመጥራት አረጋግጧል። ይህ ሁሉ ትሥሥርና ቅንነት የጎደለው፣ በሤራ የተሸበበ “ሥልጣን ወይም ሞት” በማለት በጭፍን የሚመራው ፖለቲካ አምስት ሺህ ሰው የተገበረበት ህወሃትን የማስወገድ ትግል ወዴት ይወስደዋል? ወይም ወዴት ይመልሰዋል? የሚለው ጥያቄ በስፋት እንዲነሳ ያደርገዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, jawar massacre, lemma megerssa, Middle Column, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Wondemagne Ejigu says

    January 10, 2020 02:19 pm at 2:19 pm

    አብይና ለማ በሕወሐት ጊዜ በአገዛዙ የስለላ መዋቅር ይሰሩ እንደነበር የሚታወቅ ነው። ሕዝቡም ይሕን እያወቀ ነበር እኮ ለውጡን በይቅርታ መንፈስ ሙሉ ለሙሉ የደገፈው። በእርግጥ የለማ አስተዋጽኦ የከፋ ቢሆንም። ነገር ግን አሁን ላይ ቆመን አቶ ለማን ሕወሐት የበፊት ታሪክ መዛ ስላስፈራራች ነው፣ አቋም የለወጡት-የሚለው ክርክር ውሐ አይቋጥርም። ቢያንስ፣ቢያንስ በቃኝ ብለው ስልጣናቸውን በመልቀቅ ሕዝብ የሰጣቸውን ክብር መጠበቅ ይችሉ ነበር።የአሁኑ እርምጃቸው በጥፋት ላይ ሌላ ጥፋት ከመደራረብ ያለፈ ፋይዳ የለውም!

    Reply
  2. nahom asnake says

    January 10, 2020 06:56 pm at 6:56 pm

    You hateful idiot!! You will lose.

    Reply
    • Wondemagne Ejigu says

      January 11, 2020 12:53 pm at 12:53 pm

      Lose what? If I may ask the smart Nahom

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule