• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አቶ ለማ መገርሳ – በህወሃት የማስፈራሪያ አጣብቂኝ ውስጥ

January 10, 2020 01:03 am by Editor 3 Comments

ከለውጡ ሾፌሮች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ለማ መገርሳ የሽግግሩ ጊዜ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆኑ ጃዋር መሐመድ አጥብቆ ሲከራረከር ነበር። አቶ ለማ የፌዴራል ፓርላማ ተወካይ ባለመሆናቸው እርሳቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር እንዳይሆኑ የሚከለክላቸው መሆኑ የታወቀ ቢሆንም በወቅቱ ግን ጃዋር ከጓደኞቹ እነ ሕዝቅኤል ገቢሣ ጋር በመሆን “ኢህአዴግ አዲስ መመሪያ/ሕግ አውጥቶም ቢሆ አቶ ለማ ጠቅላይ ሚኒስትር ሊያደርጋቸው ይገባል” በማለት ሃሳብና መመሪያ ቢጤም ሲሰጥ ነበር።

ጃዋር ያለውና ያሰበው ሳይሆን አቶ ለማ በለውጡ ሙቀት ውስጥ ባሉበት ወቅት “እኔና ዐቢይን ሞት ብቻ ነው የሚለየን” በማለት የድርጅት ሊቀመንበርነታቸውን ለዶ/ር አብይ አሳልፈው በመስጠት ዐቢይ አህመድ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆን የበኩላቸውንና ድርጅታዊ ኃላፊነታቸውን ከባልደረቦቻቸው ጋር ሆነው እውን አደረጉ።

የሆሮ ጉድሩ ተወላጅ የሆኑት አቶ ለማ በዚህ ተግባራቸውና ከለውጡ መፈንዳት ጀምሮ ለህዝብ ባቀረቡት ዲስኩር የተወደዱትን ያህል ከህወሃት አፍቃሪዎችና ጭፍራዎች ዘንድ ግን ተቃውሞ በስፋት ይሰነዘርባቸው የጀመረው ወዲያው ነበር። በተለይም በኦሮሚያ የደኅንነት ቢሮ ሥልጣናቸው ወቅት የሰሩትን በመጥቀስ። 

ስለ አዲስ አበባ የሕዝብ አሠፋፈር (ዴሞግራፊ) የተናገሩት ቅጂ አደባባይ ከወጣ በኋላ ተቃውሞ እየከበባቸው የመጣው አቶ ለማ በዛው ቅጽበት ከጃዋር መሀመድ ጋር በየዕለቱ እንደሚገናኙና አብረው እንደሚሰሩ ከየአቅጣጫው መረጃዎች ይሰራጩ ጀመር። በዚያው መጠን ከዶ/ር ዐቢይ ጋር ልዩነት እንደፈጠሩ በተደጋጋሚ በተለያዩ የሚዲያ ማሰራጫዎችና ማህበራዊ ገጾች ተዘገበ። በዳያስፖራ የሚገኙትና ራሳቸውን ተንታኝ አድርገው የሰየሙ ዜናውን ዞሩበት። 

ከኦሮሚያ ርዕስመስተዳድርነታቸው ተነስተው ወደ መከላከያ ሚኒስትርነት የመዛወራቸው ሚስጢርም ይኸው የልዩነቱ ነጸብራቅ እንደሆነ ትርጉምና ትንታኔ እየቀረበበት ከሚዲያ ወደ ሚዲያ ተራባ። በመጨረሻም ራሳቸው አቶ ለማ በቪኦኤ ቀርበው ልዩነት እንዳላቸውና “እንደመር” እያሉ ሲፈክሩበት ከነበረው ሃሳብ ጋር መጣላታቸውን ይፋ አደረጉ።

በተለይም የብልጽግናን መመሥረት፣ የኢህአዴግ እህት ድርጅቶችና አጋር ድርጅቶች ውህደት እንደማይቀበሉ ሲናገሩ ተቃውሟቸውን በሚያሳምን መንገድ ባለማስረዳታቸው ሕዝብ ደነገጠ። መሠረታዊ ምክንያታቸው ምን ይሆን ሲል በማኅበራዊ ሚዲያ ክርክርና መላምት ማስቀመጥ ተጀመረ። 

የለውጡ ተጻራሪዎችና ጭፍን ነቃፊዎች፣ በተለይም የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር በፓርቲ ደረጃ፣ እንዲሁም ደጋፊ የማኅበራዊ ገጽ ጭፍሮቹ የአቶ ለማን ቃለ ምልልስ አጯጯሁት። “ብለን ነበር” ሲሉ የለውጡ ሃዲድ እንደተሰበረ፤ ባቡሩ አቅጣጫውን እንደሳተ አወጁ። 

የጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ከዘወትር ታማኝ ምንጮቹ ባገኘው መረጃ አቶ ለማ እዚህ ችግር ውስጥ የወደቁት ፈልገውና ወደው እንዲሁም የለውጡ የትግል አጋሮቻቸውን ለማስቀየም አስበው ሳይሆን ከፌደራሉ የመረጃና የደህንነት አጄንሲ (ደኅንነት) ጋር በጥምረት በሚሠራው የኦሮሚያ የስለላ መዋቅር ውስጥ በከፋ ሁኔታ ተነክረው ስለነበር ነው።

“ማበስበስ” በሚባለው በህወሃት ስልት ውስጥ በኦሮሞ ተወላጅ የኦነግ ታጋዮች፣ ደጋፊዎችና ተቃዋሚዎች ላይ ሲያከናውኑት የነበረው የስለላ ሪፖርት ሪኮርዶች ህወሃት እጅ አሉ። ህወሃት በክልሉ መሪ ሳይቀር “ሚስጢር እናወጣለን” በሚል የሚሰነዝሩት ዛቻ በአብዛኛው በአቶ ለማ ላይ ያነጣጠረ መሆኑንን የጎልጉል ዘጋቢ ለህወሃት ቅርብ የሆኑ ክፍሎችን ጠቅሶ ዘግቧል። ይህ የህወሃት ዛቻ በዶ/ር ዐቢይ ላይ ቢሆን ኖሮ መዛትም አያስፈልጋቸውም ነበር፤ ውሸት ፈጥሮ በሚያናፍሰው የዲጂታል ወያኔ መስተጋብራቸው ያለገደብ ያራግቡት ነበር።  

ከወራት በፊት “አቶ ለማ የኦሮሞ ተወላጆችን ሲያሳድድ የነበረ ዋናው ወንጀለኛ ነው” ሲል የህወሃት ደጋፊና ፕሮፓጋንዲስት የሆነው ዳንኤል ብርሃኔ፤ ጌታቸው አሰፋ ላይ የሚቀርበውን የነፍሰ በላነት ውንጀላ ለመከላከል ባቀረበው ጽሁፍ ላይ መጥቀሱ አይዘነጋም። ከዚያም በኋላ የብልጽግና ፓርቲ መቋቋሙን ተከትሎ ይኸው ሚስጢር ይፋ እናደርጋለን የሚለው ጉዳይ በስፋት ሲናፈስ የከረመውም ያለምክንያት አልነበረም።

በዚሁ ምክንያት አቶ ለማ ከኦሮሞ ህዝብ ሊነጥላቸው የሚችለው ይህ ሚስጢር እንዳይወጣ ኦዲፒን ወይም ብልጽግና ፓርቲን እንዲለዩና ህወሃት ጠፍጥፎ እየሠራቸው ካሉት የፌዴራል ኃይሎች ጋር እንዲዋሃዱ አማራጭ እንደቀረበላቸው ነው ለህወሃት ቅርብ የሆኑት ለጎልጉል መረጃ የሰጡት።

ህወሃት ከፌዴራል ኃይሎች ጋር በማበር ዳግም መንግሥት ለመሆን እንደሚሰራ በግልጽ ማሳወቁና አቶ ለማም ፓርቲያቸውን ጥለው ወደ ፌዴራል ኃይሎች የመንደርደራቸው ዜና ሌላ ምክንያት እንደሌለው የጎልጉል ዘጋቢ ካሰባሰበው መረጃ ለመረዳት ተችሏል።

አቶ ለማ መገርሳ ብልጽግና መቃወምና መደመርን በማጣጣል የተናገሩትን ቃለ ምልልስ “አንዱ የመጫወቻ ካርዴ ነው” ሲል ገልጾት የነበረው ጃዋር ረቡዕ ዕለት ለኤልቲቪ ባልደረባ ጋር ባደረገው ጭውውት መሳይ ቃለ መጠይቅ፣ በመጪው ምርጫ አቶ ለማን አካትተው ወደ ውድድር እንደሚገቡ በገደማዳሜና በሳቅ አረጋግጧል። ጃዋር ለጊዜው መናገር ያልፈለገው የፓርቲዎች ጥምረት እንደሚኖርም ጠቁሟል። ህወሃትም በጌታቸው ረዳ አማካይነት ጃዋር ከተቀላቀለው ኦፌኮ ጋር ህወሃት ግንባር የመፍጠር ሥራ እየሠራ መሆኑንን የበቀለ ገርባን ስም በመጥራት አረጋግጧል። ይህ ሁሉ ትሥሥርና ቅንነት የጎደለው፣ በሤራ የተሸበበ “ሥልጣን ወይም ሞት” በማለት በጭፍን የሚመራው ፖለቲካ አምስት ሺህ ሰው የተገበረበት ህወሃትን የማስወገድ ትግል ወዴት ይወስደዋል? ወይም ወዴት ይመልሰዋል? የሚለው ጥያቄ በስፋት እንዲነሳ ያደርገዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, jawar massacre, lemma megerssa, Middle Column, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Wondemagne Ejigu says

    January 10, 2020 02:19 pm at 2:19 pm

    አብይና ለማ በሕወሐት ጊዜ በአገዛዙ የስለላ መዋቅር ይሰሩ እንደነበር የሚታወቅ ነው። ሕዝቡም ይሕን እያወቀ ነበር እኮ ለውጡን በይቅርታ መንፈስ ሙሉ ለሙሉ የደገፈው። በእርግጥ የለማ አስተዋጽኦ የከፋ ቢሆንም። ነገር ግን አሁን ላይ ቆመን አቶ ለማን ሕወሐት የበፊት ታሪክ መዛ ስላስፈራራች ነው፣ አቋም የለወጡት-የሚለው ክርክር ውሐ አይቋጥርም። ቢያንስ፣ቢያንስ በቃኝ ብለው ስልጣናቸውን በመልቀቅ ሕዝብ የሰጣቸውን ክብር መጠበቅ ይችሉ ነበር።የአሁኑ እርምጃቸው በጥፋት ላይ ሌላ ጥፋት ከመደራረብ ያለፈ ፋይዳ የለውም!

    Reply
  2. nahom asnake says

    January 10, 2020 06:56 pm at 6:56 pm

    You hateful idiot!! You will lose.

    Reply
    • Wondemagne Ejigu says

      January 11, 2020 12:53 pm at 12:53 pm

      Lose what? If I may ask the smart Nahom

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሆሩ ጉዱሩ ወለጋ ዞን የጉደኔ ጫላ ሲበሬ ቀበሌ ነዋሪዎች በኦነግ ሸኔ ላይ ጀብዱ ፈፀሙ August 11, 2022 03:04 pm
  • በኢትዮጵያ ግብርና ላይ ግብጽ ለዓመታት የፈጸመችው ሤራ August 10, 2022 10:58 am
  • የስሪ ላንካው “FamilyCracy” – ከመዓቱ እስከ ተውኔቱ August 8, 2022 09:45 am
  • “አበበ እንጂ መቼ ሞተ!”          July 19, 2022 04:57 pm
  • ሸኔ አመራሮቹንና ጠንካራ ይዞታዎቹን እያጣ ነው July 19, 2022 01:55 am
  • የወልቃይት አማራ የተሰቃየባቸው የትህነግ 15 ድብቅ እስር ቤቶች! July 18, 2022 03:13 pm
  • ገቢ የማያስገኙ የዜና ርዕሶች July 17, 2022 05:36 pm
  • “ዛሬ ‘ኃያል ነን’ የሚሉ ሀገራት ኢትዮጵያ ላይ በሚዲያ /በመረጃ/፣ በዲፕሎማሲ፣ በሳይበር እና በተልእኮ የተቀነባበረ ‘ግራጫ ጦርነት’ እያካሄዱባት ነው” ጠ/ሚ ዐቢይ July 7, 2022 10:03 am
  • የኦሮሞ ልሂቃንና ፖለቲከኞች በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን “የዘር ማጥፋት” ወንጀል እንዲያወግዙት አብን ጠየቀ July 6, 2022 01:38 pm
  • “አማራን ኦሮሚያ ውስጥ የመግደል እና የመጨፍጨፍ እቅድ የኦነግ ሳይሆን የኦሮሚያ ብልጽግና ነው” አቶ ሃንጋሳ July 6, 2022 01:53 am
  • “በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” አይማን አብድልአዚዝ ግብጻዊው ፖለቲከኛ July 5, 2022 12:57 pm
  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule