• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ

May 15, 2022 09:38 am by Editor Leave a Comment

በየጊዜው እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ሰለባ ላለመሆን ዜጎች ማንነታቸው ከማይታወቁ ግለሰቦች ጋር በበይነመረብ በሚደረጉት ግንኙነት ላይ ጥንቃቄ እንዲወስዱ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት እና የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ጥምር ግብረ- ኃይል አሳሰበ።

ግብረ-ኃይሉ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ በኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ማህበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም የሚፈጸሙ የማጭበርበር ወንጀሎች በይዘትም ሆነ በአፈጻጸም ስልታቸው ውስብስብ እየሆኑ ከመምጣታቸው ባሻገር በርካታ ግለሰቦች የጉዳቱ ሰለባ እንዲሆኑ እያደረገ ነው።

የማጭበርበር ወንጀሎቹ በዋናነት የሚፈጸሙት በውጭ ሀገር የሚኖሩ፣ በቱሪስት ቪዛ ወደ አገር ውስጥ በሚገቡ የተለያዩ ሀገራት ዜግነት ባላቸው ግለሰቦች መሆኑንም በመግለጫው ተጠቅሷል፡፡

ኢትዮጵያዊያን በስፋት የሚጠቀሟቸው ማህበራዊ ሚዲያዎች ማለትም ፌስቡክ፣ ኢ-ሜይል፣ ዋትስአፕ፣ ቴሌግራም፣ ኢንስታግራም፣ ኢሞና ቫይበርን በመጥለፍና ወዳጅ መስሎ በመቅረብ ወንጀሎቹ እንደሚፈጸሙ ከተደረገው ክትትል ማወቅ እንደተቻለም ተገልጿል።

የማጭበርበር ተግባሩን የሚፈጽሙ ግለሰቦችም ሀሰተኛ የሆኑ በአገር ውስጥና በውጭ አገር የሚገኙ ድርጅቶችን ሰነድ፣ የፋይናንስ ተቋማትና የጉምሩክ ሰነዶች የተቋም መለያዎችና ሎጎዎችን፣ የኃላፊዎችን ፊርማ፣ መታወቂያ እንዲሁም የተለያዩ ውሎችን ጭምር ለማጭበርበሪያነት እንደሚጠቀሙ አመልክቷል፡፡

የወንጀሉ ፈጻሚዎች የሚጠቀሙባቸው ስልቶች በየጊዜው የሚለዋወጡ መሆኑን ያመለከተው መግለጫው፤ በውጭ አገራት በኢንቨስትመንት ሥራ ላይ የተሰማሩ በማስመሰል በኢትዮጵያ ውስጥም በዚህ ሥራ ላይ ለመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸውና አብሯቸው የሚሰራ ሰው እንደሚፈልጉ በመግለጽ፣ ለተማሪዎች በዉጭ አገር የትምህርት ዕድል አመቻችተናል በማለትና ሌሎች ተመሳሳይ የማጭበርበሪያ መንገዶችን እንደሚጠቀሙ ተገልጿል።

የተለያዩ የጽህፈት መሳሪያዎችና ላፕቶፖች እንደላኩ በመግለጽ፤ ዉጭ አገር ቤተሰብ ያላቸዉን ግለሰቦች ከቤተሰቦቻቸዉ ጋር የሚደረግን የማህበራዊ ሚዲያ ግንኙነት በመጥለፍ ቤተሰቦቻቸዉ ዕቃ እንደላኩላቸዉ በማስመሰልና በጠለፉት መስመር እንደ ቤተሰብ ሆነዉ በመጻፍ ማረጋገጫ በመስጠት ጭምር እንደሚያታልሉም ተመልክቷል።

በተጨማሪም በፍቅር እንደወደቁና አግብተዉ ወደ ዉጭ ሃገር መውሰድ እንደሚፈልጉ በማሳመን፣ በሰላም ማስከበር ሥራ ላይ ተሰማርተዉ የሚገኙ የዉጭ ሃገራት ወታደሮች ነን በማለት ከአሸባሪዎች በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር እንደያዙና ገንዘቡን ወደ ሃገራቸዉ ይዘው ለመግባት አስቸጋሪ ስለሆነ ዶላሩን ወይም የውጭ አገር ገንዘቡን በስማቸዉ ልከንላችኋል በማለትም በርካታ ዜጎችን እንዳጭበረበሩ ተጠቅሷል።

በሌላ መልኩም በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚንቀሳቀሱ እንደ አንዳንድ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች እድለኛ ሆነዉ እንደመረጧቸዉ እና የድርጅቱ ዋና መስሪያ ቤት ከዉጭ ሀገር ሽልማት እንደላኩላቸዉ በማስመሰል እና ሌሎች የተለያዩ የማጭበርበሪያ መንገዶችን በመጠቀም በከፍተኛ ሁኔታ ጉዳት እያደረሱ ይገኛሉ ብሏል መግለጫው፡፡

ግለሰቦቹ የተለያዩ የማጭበርበሪያ መንገዶችን ተጠቅመዉ ካሳመኑ በኋላ ዉድ እቃዎችን ማለትም የወርቅ ሰዓት፣ ብራስሌት፣ ሃብል፣ ሽቶ፣ ጫማ፣ ቦርሳ፣ የተለያዩ አልባሳት፣ ስማርት ስልኮች፣ ላፕቶፕ እንዲሁም የዉጭ ሃገር ገንዘብ እንደላኩ በማስመሰል እንደሚያታልሉ ተገልጿል።

ለዚህም የላኪና የተቀባይ ስም እና አድራሻ የተጻፈበትን ማሸጊያና የጉምሩክ ሂደቱን በቪዲዮ ቀርጸዉ በመላክ እቃዉን በተጓዦች በኩል በዲፕሎማት፣በጉምሩክ፣ በፖስታ ቤት፣ በዲኤች ኤል፣ ስካይ ወርልድ ወይም በሌሎች አማራጮች ልከንላችኋል በማለት እቃው ለተላከበት ክፍያ የሚሆን ገንዘብ ሃገር ውስጥ በሚገኙት ተባባሪዎቻቸዉ አማካኝነት ሃሰተኛ መታወቂያ በመጠቀም የተከፈተ የሂሳብ ቁጥር ውስጥ ገቢ እንዲያደርጉ ካሳመኗቸዉ በኋላ የገባዉን ገንዘብ ወዲያውኑ ወጪ በማድረግ ወንጀሉን ይፈጽሙታል ብሏል መግለጫው፡፡

በዚህ የማጭበርበር ድርጊቶች ላይ የተሰማሩት ግለሰቦች በተጨማሪም ሀሰተኛ የብር ኖቶችን ማተም፤ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀትና መገልገል እንዲሁም የአደንዛዥ እፅ ዝዉዉር ወንጀል ጭምር ላይ ተሳታፊ ሆነዉ የተገኙ ሲሆን፤ በተደረገው ክትትል የውጭ አገር ዜጎች እንዲሁም ኢትዮጵያዊያን በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ ተጣርቶባቸዉ በማረሚያ ቤት የሚገኙ፤ ከአገር እንዲወጡ የተደረጉ እና ጉዳያቸው በምርመራ ሂደት ላይ የሚገኙም እንዳሉ ተጠቅሷል፡፡

ይህ የማጭበርበር ድርጊት ግለሰቦች ለረዥም ጊዜ ያፈሩትን ቋሚና ተንቀሳቃሽ ንብረት በመሸጥ ለዚሁ ክፍያ በማዋል ከሚደርስባቸዉ ኢኮኖሚያዊ ጉዳት በተጨማሪ ባለትዳሮች ከትዳር አጋራቸው እውቅና ውጭ የጋራ ንብረትን መሸጥና በዚህ ምክንያት ለትዳር መፍረስ እና ለቤተሰብ መበተን መንስኤ በመሆን ላይ መሆኑም በመግለጫው ተመላክቷል፡፡

በተጨማሪም ከፋይናንስ ተቋማትና ከግለሰቦች በአራጣ ጭምር ገንዘብ በመበደር ከፍተኛ ወለድ እንዲከፍሉ በመደረጋቸዉ በግለሰቦች ህይወት ላይ ጫና እንዲፈጠርና ህይወታቸው አጣብቂኝ ውስጥ መግባቱ ዜጎች በድንገት ሀብት ንብረታቸውን በማጣታቸው የጤና መታወክ ብሎም የስነ-ልቦና ችግር እንዲደርስባቸው በማድረግ ቀውስ እንዲፈጠር እያደረገ እንደሚገኝም መግለጫው አመልክቷል፡፡

ይህን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም የሚፈጸሙ ወንጀሎችን ለመከላከል ዜጎች የማህበራዊ ሚዲያን ሲጠቀሙ ማንነታቸው ከማይታወቁ ግለሰቦች ጋር የሚደረጉ ግንኙነትን በጥንቃቄ ማየት እንዳለባቸው ግብረ-ኃይሉ አሳስቧል፡፡

በማንኛውም መንገድ እቃ ተላከላችሁ ሲባሉም እቃውን አይተው ሳያረጋግጡ ምንም አይነት ክፍያ አለመፈጸም፤ እቃው ተላከ ወደተባለበት ተቋም በአካል በመሄድ በስማቸው የተላከ እቃ ስለመኖሩ ማረጋገጥ እንዳለባቸውም አሳስቧል፡፡

እንዲሁም በጉምሩክ፣ በፖስታ ቤት፣ በዲኤች ኤል ወይም በሌሎች ድርጅቶች በኩል የተላከ እቃ ወጪ ለማድረግ ገንዘብ ገቢ የሚደረገው በተቋማቱ ስም በተከፈተ የሂሃብ ቁጥር እንጂ በግለሰቦች ስም በተከፈተ የሂሳብ ቁጥር አለመሆኑን ማወቅና በእንዲህ ዓይነት ሁኔታ ምንም ገንዘብ ገቢ ከማድረግ መቆጠብ እንደሚገባ መግለጹን ኢዜአ ዘግቧል።

እንዲህ ያለ ድርጊት ሲያጋጥምም በቅርብ ለሚገኙ የሕግ አስከባሪ አካላት ሪፖርት በማድረግ የዜግነት ግዴታን መወጣትና ራስንም ከጉዳት መከላከል እንደሚገባ ግብረ-ኃይሉ አሳስቧል፡፡ (አዲስ ሚዲያ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Politics Tagged With: operation dismantle tplf, social media, social media fake info

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አበበ እንጂ መቼ ሞተ!”          July 19, 2022 04:57 pm
  • ሸኔ አመራሮቹንና ጠንካራ ይዞታዎቹን እያጣ ነው July 19, 2022 01:55 am
  • የወልቃይት አማራ የተሰቃየባቸው የትህነግ 15 ድብቅ እስር ቤቶች! July 18, 2022 03:13 pm
  • ገቢ የማያስገኙ የዜና ርዕሶች July 17, 2022 05:36 pm
  • “ዛሬ ‘ኃያል ነን’ የሚሉ ሀገራት ኢትዮጵያ ላይ በሚዲያ /በመረጃ/፣ በዲፕሎማሲ፣ በሳይበር እና በተልእኮ የተቀነባበረ ‘ግራጫ ጦርነት’ እያካሄዱባት ነው” ጠ/ሚ ዐቢይ July 7, 2022 10:03 am
  • የኦሮሞ ልሂቃንና ፖለቲከኞች በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን “የዘር ማጥፋት” ወንጀል እንዲያወግዙት አብን ጠየቀ July 6, 2022 01:38 pm
  • “አማራን ኦሮሚያ ውስጥ የመግደል እና የመጨፍጨፍ እቅድ የኦነግ ሳይሆን የኦሮሚያ ብልጽግና ነው” አቶ ሃንጋሳ July 6, 2022 01:53 am
  • “በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” አይማን አብድልአዚዝ ግብጻዊው ፖለቲከኛ July 5, 2022 12:57 pm
  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule