• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ

May 15, 2022 09:38 am by Editor Leave a Comment

በየጊዜው እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ሰለባ ላለመሆን ዜጎች ማንነታቸው ከማይታወቁ ግለሰቦች ጋር በበይነመረብ በሚደረጉት ግንኙነት ላይ ጥንቃቄ እንዲወስዱ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት እና የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ጥምር ግብረ- ኃይል አሳሰበ።

ግብረ-ኃይሉ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ በኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ማህበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም የሚፈጸሙ የማጭበርበር ወንጀሎች በይዘትም ሆነ በአፈጻጸም ስልታቸው ውስብስብ እየሆኑ ከመምጣታቸው ባሻገር በርካታ ግለሰቦች የጉዳቱ ሰለባ እንዲሆኑ እያደረገ ነው።

የማጭበርበር ወንጀሎቹ በዋናነት የሚፈጸሙት በውጭ ሀገር የሚኖሩ፣ በቱሪስት ቪዛ ወደ አገር ውስጥ በሚገቡ የተለያዩ ሀገራት ዜግነት ባላቸው ግለሰቦች መሆኑንም በመግለጫው ተጠቅሷል፡፡

ኢትዮጵያዊያን በስፋት የሚጠቀሟቸው ማህበራዊ ሚዲያዎች ማለትም ፌስቡክ፣ ኢ-ሜይል፣ ዋትስአፕ፣ ቴሌግራም፣ ኢንስታግራም፣ ኢሞና ቫይበርን በመጥለፍና ወዳጅ መስሎ በመቅረብ ወንጀሎቹ እንደሚፈጸሙ ከተደረገው ክትትል ማወቅ እንደተቻለም ተገልጿል።

የማጭበርበር ተግባሩን የሚፈጽሙ ግለሰቦችም ሀሰተኛ የሆኑ በአገር ውስጥና በውጭ አገር የሚገኙ ድርጅቶችን ሰነድ፣ የፋይናንስ ተቋማትና የጉምሩክ ሰነዶች የተቋም መለያዎችና ሎጎዎችን፣ የኃላፊዎችን ፊርማ፣ መታወቂያ እንዲሁም የተለያዩ ውሎችን ጭምር ለማጭበርበሪያነት እንደሚጠቀሙ አመልክቷል፡፡

የወንጀሉ ፈጻሚዎች የሚጠቀሙባቸው ስልቶች በየጊዜው የሚለዋወጡ መሆኑን ያመለከተው መግለጫው፤ በውጭ አገራት በኢንቨስትመንት ሥራ ላይ የተሰማሩ በማስመሰል በኢትዮጵያ ውስጥም በዚህ ሥራ ላይ ለመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸውና አብሯቸው የሚሰራ ሰው እንደሚፈልጉ በመግለጽ፣ ለተማሪዎች በዉጭ አገር የትምህርት ዕድል አመቻችተናል በማለትና ሌሎች ተመሳሳይ የማጭበርበሪያ መንገዶችን እንደሚጠቀሙ ተገልጿል።

የተለያዩ የጽህፈት መሳሪያዎችና ላፕቶፖች እንደላኩ በመግለጽ፤ ዉጭ አገር ቤተሰብ ያላቸዉን ግለሰቦች ከቤተሰቦቻቸዉ ጋር የሚደረግን የማህበራዊ ሚዲያ ግንኙነት በመጥለፍ ቤተሰቦቻቸዉ ዕቃ እንደላኩላቸዉ በማስመሰልና በጠለፉት መስመር እንደ ቤተሰብ ሆነዉ በመጻፍ ማረጋገጫ በመስጠት ጭምር እንደሚያታልሉም ተመልክቷል።

በተጨማሪም በፍቅር እንደወደቁና አግብተዉ ወደ ዉጭ ሃገር መውሰድ እንደሚፈልጉ በማሳመን፣ በሰላም ማስከበር ሥራ ላይ ተሰማርተዉ የሚገኙ የዉጭ ሃገራት ወታደሮች ነን በማለት ከአሸባሪዎች በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር እንደያዙና ገንዘቡን ወደ ሃገራቸዉ ይዘው ለመግባት አስቸጋሪ ስለሆነ ዶላሩን ወይም የውጭ አገር ገንዘቡን በስማቸዉ ልከንላችኋል በማለትም በርካታ ዜጎችን እንዳጭበረበሩ ተጠቅሷል።

በሌላ መልኩም በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚንቀሳቀሱ እንደ አንዳንድ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች እድለኛ ሆነዉ እንደመረጧቸዉ እና የድርጅቱ ዋና መስሪያ ቤት ከዉጭ ሀገር ሽልማት እንደላኩላቸዉ በማስመሰል እና ሌሎች የተለያዩ የማጭበርበሪያ መንገዶችን በመጠቀም በከፍተኛ ሁኔታ ጉዳት እያደረሱ ይገኛሉ ብሏል መግለጫው፡፡

ግለሰቦቹ የተለያዩ የማጭበርበሪያ መንገዶችን ተጠቅመዉ ካሳመኑ በኋላ ዉድ እቃዎችን ማለትም የወርቅ ሰዓት፣ ብራስሌት፣ ሃብል፣ ሽቶ፣ ጫማ፣ ቦርሳ፣ የተለያዩ አልባሳት፣ ስማርት ስልኮች፣ ላፕቶፕ እንዲሁም የዉጭ ሃገር ገንዘብ እንደላኩ በማስመሰል እንደሚያታልሉ ተገልጿል።

ለዚህም የላኪና የተቀባይ ስም እና አድራሻ የተጻፈበትን ማሸጊያና የጉምሩክ ሂደቱን በቪዲዮ ቀርጸዉ በመላክ እቃዉን በተጓዦች በኩል በዲፕሎማት፣በጉምሩክ፣ በፖስታ ቤት፣ በዲኤች ኤል፣ ስካይ ወርልድ ወይም በሌሎች አማራጮች ልከንላችኋል በማለት እቃው ለተላከበት ክፍያ የሚሆን ገንዘብ ሃገር ውስጥ በሚገኙት ተባባሪዎቻቸዉ አማካኝነት ሃሰተኛ መታወቂያ በመጠቀም የተከፈተ የሂሳብ ቁጥር ውስጥ ገቢ እንዲያደርጉ ካሳመኗቸዉ በኋላ የገባዉን ገንዘብ ወዲያውኑ ወጪ በማድረግ ወንጀሉን ይፈጽሙታል ብሏል መግለጫው፡፡

በዚህ የማጭበርበር ድርጊቶች ላይ የተሰማሩት ግለሰቦች በተጨማሪም ሀሰተኛ የብር ኖቶችን ማተም፤ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀትና መገልገል እንዲሁም የአደንዛዥ እፅ ዝዉዉር ወንጀል ጭምር ላይ ተሳታፊ ሆነዉ የተገኙ ሲሆን፤ በተደረገው ክትትል የውጭ አገር ዜጎች እንዲሁም ኢትዮጵያዊያን በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ ተጣርቶባቸዉ በማረሚያ ቤት የሚገኙ፤ ከአገር እንዲወጡ የተደረጉ እና ጉዳያቸው በምርመራ ሂደት ላይ የሚገኙም እንዳሉ ተጠቅሷል፡፡

ይህ የማጭበርበር ድርጊት ግለሰቦች ለረዥም ጊዜ ያፈሩትን ቋሚና ተንቀሳቃሽ ንብረት በመሸጥ ለዚሁ ክፍያ በማዋል ከሚደርስባቸዉ ኢኮኖሚያዊ ጉዳት በተጨማሪ ባለትዳሮች ከትዳር አጋራቸው እውቅና ውጭ የጋራ ንብረትን መሸጥና በዚህ ምክንያት ለትዳር መፍረስ እና ለቤተሰብ መበተን መንስኤ በመሆን ላይ መሆኑም በመግለጫው ተመላክቷል፡፡

በተጨማሪም ከፋይናንስ ተቋማትና ከግለሰቦች በአራጣ ጭምር ገንዘብ በመበደር ከፍተኛ ወለድ እንዲከፍሉ በመደረጋቸዉ በግለሰቦች ህይወት ላይ ጫና እንዲፈጠርና ህይወታቸው አጣብቂኝ ውስጥ መግባቱ ዜጎች በድንገት ሀብት ንብረታቸውን በማጣታቸው የጤና መታወክ ብሎም የስነ-ልቦና ችግር እንዲደርስባቸው በማድረግ ቀውስ እንዲፈጠር እያደረገ እንደሚገኝም መግለጫው አመልክቷል፡፡

ይህን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም የሚፈጸሙ ወንጀሎችን ለመከላከል ዜጎች የማህበራዊ ሚዲያን ሲጠቀሙ ማንነታቸው ከማይታወቁ ግለሰቦች ጋር የሚደረጉ ግንኙነትን በጥንቃቄ ማየት እንዳለባቸው ግብረ-ኃይሉ አሳስቧል፡፡

በማንኛውም መንገድ እቃ ተላከላችሁ ሲባሉም እቃውን አይተው ሳያረጋግጡ ምንም አይነት ክፍያ አለመፈጸም፤ እቃው ተላከ ወደተባለበት ተቋም በአካል በመሄድ በስማቸው የተላከ እቃ ስለመኖሩ ማረጋገጥ እንዳለባቸውም አሳስቧል፡፡

እንዲሁም በጉምሩክ፣ በፖስታ ቤት፣ በዲኤች ኤል ወይም በሌሎች ድርጅቶች በኩል የተላከ እቃ ወጪ ለማድረግ ገንዘብ ገቢ የሚደረገው በተቋማቱ ስም በተከፈተ የሂሃብ ቁጥር እንጂ በግለሰቦች ስም በተከፈተ የሂሳብ ቁጥር አለመሆኑን ማወቅና በእንዲህ ዓይነት ሁኔታ ምንም ገንዘብ ገቢ ከማድረግ መቆጠብ እንደሚገባ መግለጹን ኢዜአ ዘግቧል።

እንዲህ ያለ ድርጊት ሲያጋጥምም በቅርብ ለሚገኙ የሕግ አስከባሪ አካላት ሪፖርት በማድረግ የዜግነት ግዴታን መወጣትና ራስንም ከጉዳት መከላከል እንደሚገባ ግብረ-ኃይሉ አሳስቧል፡፡ (አዲስ ሚዲያ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Left Column, Politics Tagged With: operation dismantle tplf, social media, social media fake info

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule