• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሳዑዲው አልጋወራሽ ሞተዋል? ወይስ በህይወት አሉ? ጠ/ሚ/ር ዓቢይ አላሙዲንን “ያስፈቱት” ማንን አነጋግረው ነው?

June 1, 2018 11:47 am by Editor 3 Comments

በሙስና ወንጀል በሚል በርካታ የሳዑዲ ባለሃብቶችን ዘብጥያ የጣሉት የዙፋን ተስፈኛው የሳዑዲ አረቢያ አልጋ ወራሽ ሞሐመድ ቢን ሳልማን በሳዑዲ ሚዲያ ከታዩ አንድ ወር አልፏቸዋል። በአንዳንዶች ግምት በቤተመንግሥት በተደረገ የተኩስ ልውውጥ ተገድለዋል ይባላል። አልጋወራሹ በህይወት ከሌሉ ጠ/ሚ/ር ዓቢይ አህመድ አላሙዲንን “አስፈትተው” የመጡት ማንን አነጋግረው ነው የሚል ጥያቄ ተነስቷል። የሳዑዲ መንግሥት አልጋወራሹ በሥራቸው ላይ እንዳሉ የሚያሳይ ቪዲዮ ለቋል።

የሳዑዲ የዙፋን ተስፈኛ አልጋ ወራሽ ሞሐመድ ቢን ሳልማን 11 ልዑላንን እና 38 የመንግሥት ባለሥልጣናትን (የቀድሞውን ጨምሮ) እንዲሁም የንግድ ሰዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋላቸውን፤ ደላላ (ተጠሪ ወይም front man) ባለሃብት እንደሆነ የሚነገርለት በግማሽ ኢትዮጵያዊ የሆነው ሞሐመድ አላሙዲ (አል-አሙዲ) በቁጥጥር ሥር ከዋሉት መካከል መሆኑን በኅዳር ወር ጎልጉል አረጋግጦ መዘገቡ ይታወሳል።

ይህ “በሳዑዲ አረቢያ ታሪክ ተፈጽሞ አያውቅም” ተብሎ የሚነገርለትን የጸረ ሙስና ዘመቻ የሚያካሂደው ኮሚቴ “ማንኛውንም የማሰር፣ የመያዝ፣ ወዘተ ሥልጣን” እንደተሰጠውና ይህንንም በኃላፊነት የሚመሩት አልጋወራሹ መሆናቸውን አስመልክተው ንጉሥ ሳልማን በሳዑዲ ቲቪ ላይ እንደተናገሩት፤ “የሕዝብን ገንዘብ በነካ፣ በመዘበረ፣ ወይም እንዳይሰረቅ ባልተከላከለ ወይም ሥልጣኑን ተጠቅሞ (ይህንን ዓይነት ተግባር በፈጸመ) በማንኛውም ግለሰብ ላይ ሕጉ በጽናት ተግባራዊ ይደረጋል። ይህ የሚፈጸመው በትልልቆቹም ሆነ በትንንሾቹም ላይ ይሆናል፤ ማንንም አንፈራም” ማለታቸውን የጎልጉል ዘገባ በወቅቱ ትንታኔ የሰጠበት ነበር።

በዚህ ዓይነት ከፍተኛ ሥልጣንና ተስፋ የፊት መሪ የተደረጉት አልጋወራሽ ሳልማን ከኤፕሪል 21 ወዲህ በሳዑዲ ሚዲያ ፈጽሞ ያልታዩ መሆናቸውን በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ የሚዲያ ዘገባዎች ሰሞኑን ጠቅሰዋል። ይህንንም ተከትሎ የምዕራቡ የዜና ዘገባዎች ሁልጊዜ የሚዲያውን ትኩረት የሚሹት አልጋወራሽ ለሕዝብ ሳይታዩ የመቆየታቸውን ሁኔታ በማንሳት ሲዘግቡ ሰንብተዋል።

ከሳዑዲ አረቢያ ጋር በጠላትነት የምትተያየው ኢራን ግን አልጋወራሹ በቤተመንግሥት አካባቢ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ ቆስለዋል ወይም ሞተዋል በማለት በርግጠኝነት ትናገራለች። የጸረ ሙስናውን ዘመቻ እና የአገሪቱን ሥልጣን ለብቻቸው ጠቅልለው በመያዛቸው በሳዑድ ቤተሰብ በተከፈተው ጠላትነትና የሥልጣን ሽኩቻ ኤፕሪል 21 ቀን ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ ተደርጎ እንደነበር የኢራን ጋዜጣ ዘገባ ያመለክታል።

ካይሃን የተባለው የኢራን ጋዜጣ የስለላና የመረጃ ምንጮች ዘገባ ጠቅሶ እንደሚለው ከሆነ በተኩስ ልውውጡ ወቅት አልጋወራሹ “ቢያንስ በሁለት ጥይት ተመትተዋል፤ በዚህም ሳቢያ ሞተዋል” ይላል። በመቀጠልም አልጋወራሹ በህይወት ካሉ ለምን የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፔዮ በሳዑዲ ጉብኝት ሲያደርጉ ከአልጋወራሹ ጋር የተነሱት ፎቶ ይፋ አልተደረገም በማለት ይጠይቃል።

የሳዑዲ አረቢያ መንግሥት ግን ይህንን አቋም በግልጽ ይቃወማል። አልጋወራሹ በህይወት እንዳሉና መንግሥታዊ ሥራቸውንም በሥርኣት እያከናወኑ መሆናቸውን ይናገራል። ለዚህም የተለያዩ ፎቶዎችንና ተንቀሳቃሽ ምስሎችን በዋቢነት ያቀርባል። ሆኖም የትኞቹም ምስሎች ቀን የሌላቸው ከመሆናቸው በላይ በየትኛውም ምንጭ ማረጋገጥ እንዳልቻለ ሲኤንኤን ዘግቧል።

በኤፕሪል 21 የተካሄደውን የተኩስ ልውውጥ በተመለከተ የሳዑዲ መንግሥት ተኩስ አልተሰማም በማለት አይክድም። ሁኔታው የተከሰተው ለመዝናኛ የሚውል ሰው አልባ በራሪ (ድሮን) ሳይፈቀድለት በቤተመንግሥቱ ሰማይ ሲበር በመታየቱ ያንን ለማክሸፍ የተወሰደ እርምጃ ነው በማለት ያስተባብላል።

አልጋወራሹ ከፊፋው ፕሬዚዳንት ጋር (ፎቶ፤ አረብ ኒውስ ፋይል)

የምዕራብ ዜና ወኪሎች በተለይም ሲኤንኤን የአልጋወራሹን በህይወት አለመኖር አጽንዖት ሰጥቶ ከዘገበ የተወሰኑ ሰዓታት በኋላ የሳዑዲ መንግሥት መቼ እንደተከሰተ የማይታወቅ አልጋወራሹ የንግድ ልማት ስብሰባ ሲመሩ የሚያሳይ ቪዲዮ ለቋል። የሳዑዲ መንግሥት ስብሰባው ከሁለት ቀን በፊት የተካሄደ ነው ቢልም ሲኤንኤን ግን ስብሰባው በቅርቡ ወይም ከኤፕሪል 21 በኋላ ለመቀረጹ ማረጋግጥ አልቻልኩም ብሏል።  ከዚህ በተጨማሪም የሳዑዲ መንግሥት አልጋወራሹ  የየመኑን ፕሬዚዳንት ሲቀበሉ የሚያሳይ ተጨማሪ ቪዲዮ ለቋል። በሌላ በኩል አልጋወራሹ የፊፋውን ፕሬዚዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ባለፈው አርብ አነጋግረዋል በማለት አረብ ኒውስ ቢዘግብም የተጠቀመው ፎቶ ግን ከፋይል ክምችቱ እንደሆነ አልካደም።

አልጋወራሹ በህይወት አሉ፤ ይህ የሳዑዲና የምዕራቡ ዓለም ጠላት የሆነችው ኢራን አፍራሽ ፕሮፓጋንዳ ነው የሚሉ የአሜሪካና የአውሮፓ የፖለቲካ ተንታኞች ልዑሉ ከጸረ ሙስናው ዘመቻ ጋር በተያያዘ ምናልባት በብዛት በሚዲያ ሲታዩ ስለነበሩ አሁን ለመቀነስ የወሰዱት እርምጃ ነው ይላሉ። ይህንንም እንደሽፋን አድርጋ ኢራን በሳዑዲ አለመረጋጋት መኖሩን በመጠቆም የራሷን የፖለቲካ ፍላጎት ለማሟላት እየተጠቀመችበት ነው ሲሉ ይሟገታሉ።

ከጸረሙስናው ጋር በተያያዘ አላሙዲንን ለውርደትና በሌብነት ክስ ለእስራት የዳረጉት አልጋወራሽ በህይወት ከሌሉ ጠ/ሚ/ር ዓቢይ አህመድ ባለፈው ወደ ሳዑዲ በሄዱ ጊዜ በርግጥ አልጋወራሹን አግኝተዋቸዋል የሚል ጥያቄ መነሳቱ አይቀሬ ነው። በኢትዮጵያ ህወሓት/ኢህአዴግ የሚቆጣጠራቸው የሚዲያ ውጤቶች ጠ/ሚ/ሩ ከአልጋወራሹ ጋር መገናኘታቸውን በስፋት ቢዘግቡም ያሳዩት ቪዲዮም ሆነ ፎቶ ግን አልነበረም።

ከዚህ ጋር በተያያዘ ጠ/ሚ/ሩ ከሳዑዲ እንደተመለሱ በፍጥነት በሚሊኒየም አዳራሽ በመገኘት በሌብነትና ዝርፊያ ተጠርጥሮ በቁጥጥር ሥር የዋለውን አላሙዲንን ለማስፈታት ስምምነት ላይ መደረሱን ለተሰብሳቢው ይፋ አደረጉ። ከመስመርም አለፍ ብለው አላሙዲንን በተዋቡ ቃላት አሞካሹት፣ አወደሱት፣ አመሰገኑት። ምንም እንኳን በወቅቱ ጠ/ሚ/ር ዓቢይ በአገራችን ሕግ በተገቢው አላሙዲንን እንጠይቃለን ቢሉም ትርፍ የሄዱበት መንገድ ሳዑዲ ሄደው ያከናወኗቸው ሌሎች ተግባራት የበለጠ ሚዛን በመድፋታቸው እንጂ ስለ አላሙዲን የተናገሩት ኢትዮጵውያን አሳዝኗል፤ አስቆጥቷል።

ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ እንደሚሉት በርግጥ አልጋወራሹ በህይወት ከሌሉ የአላሙዲን “ተፈትተዋል” መባል፤ “ከተፈቱም ወደ አገር ሳይመጡ መቅረታቸው” ከዚህ ውስብስብ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ምክንያት ሊሆን ይችላል ይላሉ።

ለበርካታ ዓመታት ግብር ባለመክፈል፣ እጅግ ሰፋፊ የመሬት ይዞታዎችን (በተለይ ከኦሮሚያ)  አጥሮ ያለ ሥራ በማስቀመጥ፣ እስካሁን ያልተከፈለ ከፍተኛ መጠን ያለው ብድር በመውሰድ፣ ወዘተ በርካታ ጥያቄዎች የሚቀርብበት አላሙዲ ወደ አገር እንዲመጣ የተፈለገው ከዚህ ጋር በተያያዘ ነው የሚሉ ወገኖች አሉ።

ከእነዚህ ያልተወራዱ ሒሳቦች በተጨማሪ የአላሙዲ ሚድሮክ በስሙ የያዛቸውና ኢትዮጵያ ከዓለምአቀፍ የፋይናንስ ተቋማት የገንዘብ ዋስትና የገባችባቸው፣ ያልተጠናቀቁ ትልልቅ ፕሮጀክቶች ይገኛሉ። የእነዚህንም ሒሳብ ማወራረድ የፌዴራሉ ብቻ ሳይሆን የኦሮሚያም ከፍተኛ ፍላጎት ነው ይላሉ አስተያየት ሰጪዎች።

ስለዚህ ይህንን ጉዳይ በቶሎ ወደፍጻሜ በማድረስ በሚድሮክ ሥር የሚገኙትን ሃምሳ ሺህ ሠራተኞች ኅልውና መታደግ ያልተፈለገ ችግር ከመግባት የሚያድን ነው የሚሉ ወገኖች፤ ሁኔታዎች ከፈቀዱም በሕጋዊ መልኩ ንብረቶቹን እስከመውረስ ለመሄድ እንዲቻል በጠ/ሚ/ሩ ቀጥተኛ ተሳትፎ አላሙዲንን ለማስፈታት የተፈለገው ለዚህ ነው የሚለው አስተያየት በርካታዎችን የሚያሳምን ነው።

ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ የአልጋወራሹ በህይወት መኖርም ሆነ አለመኖር በተጨባጭ አልተረጋገጠም።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: abiy, alamoudi, corruption, crown prince salman, Ethiopia, Full Width Top, Middle Column, saudi arabia

Reader Interactions

Comments

  1. እዝራ says

    June 2, 2018 01:28 am at 1:28 am

    ጎልጉሎች በጣም ነው የማደነቃችሁ።
    ሁሌም ውኃ ያልነካው ጮማ ዜና ይዛችሁ ስለምትመጡ በጣም ነው የማደንቃችሁ፡የማከበራችሁ።
    ፕሮፌሽናል ጋዜጠኞች ናችሁ። በርቱ

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    June 2, 2018 11:48 pm at 11:48 pm

    ጎልጉሎች!! በጣም ነው የናቅኋችሁ!!

    Reply
  3. Belhu says

    June 4, 2018 10:08 am at 10:08 am

    Always hate.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule