• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሳይታገት ታግቻለሁ ብሎ ከባለቤቱ 500ሺ ብር የተቀበለው ግለሰብ ተያዘ

July 10, 2024 04:12 pm by Editor Leave a Comment

የ63 ዓመት የዕድሜ ባለፀጋ እና የ5 ልጆች አባት የሆነው አቶ ገብረ ተንሳኢ ተክላይ ከወይዘሮ ዘነበች በርሄ ጋር ለ14 አመታት በትዳር ተጣምረው በአሶሳ ከተማ የንግድ ስራ ላይ ተሰማርተው 4 ልጆችን አፍርተዋል።

በትዳር ህይወታቸው ውስጥ ምንም አይነት እንከን እንደሌለ የሚገልፀው አቶ ገብረተንሳኢ ተክላይ ወይዘሮ ዘነበችን ከማግባቱ በፊት አንዲት ሴት ልጅ እንዳለችውና እሷም ለብቻዋ አዲስ አበባ እንደምትኖር በመግለፅ ይህንን እኩይ ተግባር ለመፈፀም የተነሳሳውም የግል ልጁን ለመርዳት እንደሆነ ተናግሯል።

ከሚኖርበት አሶሳ ከተማ ወደ ነቀምት ከተማ በመጓዝ “ኦጌቲ” በሚባል ሆቴል ውስጥ ለሁለት ቀናት አልጋ ይዞ በመተኛት ከሆቴሉ አስተናጋጆች የ21 ዓመት ልጅ የሆነውን ወጣት ገመቹ ዮናስን በመግባባት የአጋችና ታጋች ድራማውን አብሮት እንዲሰራና ለዚህም ታግቻለሁ ብሎ ከሚላክለት ብር ላይ 25,000 ብር እንደሚሰጠው በመንገር ያሳምነዋል።

በዚህም መሰረት ባል አቶ ገብረተንሳኢ ተክላይ በሸኔ ታግቻለሁ ብሎ ለባለቤቱ ደውሎ በመንገር ስልኩን ይዘጋል። ሚስት ወይዘሮ ዘነበች የምትይዘው የምትጨብጠው ይጨንቃታል። ከ24 ሰዓታት በኋላ ወጣት ገመቹ ዮናስ ደውሎ ኦነግ ሸኔ ነን አግተነዋል 800,000 ብር ካላስገባሽ ባልሽን አታገኝውም ይላታል። ሚስት እባካችሁ የልጆቼ አባት ነው እንዳትገሉብኝ ለምኘም ቢሆን ያገኘሁትን ብር እልክላችኋለሁ ስትል መልስ ሰጠች።

በወቅቱ ይህ የሃሰት የወንጀል ድራማ ከምዕራብ ዕዝ የመረጃ ሞያተኞች ጆሮ በመድረሱ በከፍተኛ ጥንቃቄ የጉዳዩን መነሻና መድረሻ በመከታተል የተሟላ መረጃና ማስረጃ ለመያዝ መንቀሳቀሳቸውን የዕዙ መረጃ መኮነን ተናግረዋል።

ወይዘሮ ዘነበችም በዙሪያዋ ያሉ ዘመድ ወዳጆቿን አስተባብራና ያላትን ሁሉ ጨምራ የልጆቿን አባት ለማስፈታት 500,000 ብር ለመላክ አዘጋጅታለች። በሁለተኛው ቀን አጋች ነኝ ያለው ወጣት ገመቹ ዮናስ ደውሎ ባልሽን አትፈልጊውም ? ይላታል ። በፈጠራችሁ አምላክ 4 ልጆች ያለ አባት ማሳደግ አልችልም እያለች በመማፀን ያለኝ 500,000 ብር ነው ልላክላችሁ እና ልቀቁልኝ ትላለች።

ሃሰተኛ አጋችና ታጋች አገኘሁ ባለችው ብር ተስማምተው ገንዘቡን የምትልክበት አካውንት በመላክ ሌላ ነገር ብታስቢ ግን እንገለዋለን ብሎ ያስፈራራታል። ብሩም በወጣት ገመቹ ዮናስ አካውንት ተላከ።

አቶ ገብረተንሳኢ ተክላይ ለገመቹ የገባውን ቃል 25,000 ብር በመስጠት ቀሪውን አውጥቶ የግል ልጁ በሆነችው አካውንት አስገብቶ እንዲቀመጥ ይነግራታል።

ከዚህ ሁሉ በኋላ በንቃትና በትኩረት ጉዳዩ ሲከታተል መረጃና ማስረጃዎችንም ሲያሰባስቡ መቆየታቸውን የገለፁት የምዕራብ ዕዝ የመረጃ ቡድን የሃሰት አጋችና ታጋችን በቁጥጥር ስር በማዋል ገንዘቡንም በፍጥነት ከገባበት አካውንት ተመላሽ እንዲሆን በማድረግ ዋና ወንጀል አድራጊና የወንጀሉ ተባባሪን ለነቀምት ከተማ ፖሊስ አስረክበዋል።

ወይዘሮ ዘነበች በርሄን ከአሶሳ ከተማ በስልክ አናግረን በጉዳዩ ላይ በሰጠችን ቃለ- ምልልስ 14 አመታትን አብሮኝ ከኖረውና ከልጆቼ አባት ይህንን ፍፁም አልጠበቅም። ማመንም ተስኖኛል። በተግባሩ አፍሬአለሁ አንገት የሚያስደፋ ነው። የያዘው ህግ ነው ህግ የሚወስነውን ይወስን። እውነታን አፈላልገው ለዚህ ሃቅ ላበቁኝ የህግ አካላት ግን ምስጋናዬ ከፍተኛ ነው ስትል ሃሳቧን ሰጥታለች። (የመከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም ገጽ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column, Social

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule