• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አበበ በለው በአማራ ሚዲያ? እንዴት ሆኖ?!

December 12, 2021 09:49 am by Editor 1 Comment

እንደ አገርም፣ እንደ ሕዝብም የገባንበትን የችግር ማዕበል በቅጡ የመረዳት ችግር እንዳለ የሚያመላክቱ ጉዳዮች አሉ። እነዚህን ጉዳዮች ባስቸኳይ ካላቆምን ውርደት በግል፣ በቤተሰብ፣ በቀዬና በአገር ደረጃ በደጅ ቆሞ እየጠበቀን ነውና “ግባ በለው” የማለት ያህል ይሆንብናል። ይህ ከሆነ ደግሞ ዕድሜ ልክ ቀና ማለት አይቻልም። እንግሊዞች ተንበርክከው እንደ ከብት ሳር እንደጋጡት እንኳን ዕድል የሚሰጥ የለም።

ኢትዮጵያ ከዳር እስከዳር ተነስታ፣ ልጆቿ አንድ ሆነው፣ የቻለ ህይወቱን፣ ያላቻለ በደጀን ተጋምዶ በከፈሉት ዋጋ ዛሬ የተገኘው ድል ተመዝግቧል። ከትግሬ ወራሪ ኃይል ነጻ በወጡ አካባቢዎች እንደታየው ዓላማው አገሪቱን መዘረፍ፣ ቀሪውን ማውደምና ወደ ዓመድነት መቀየር ነው። ይህ በዓይን ብረታችን ያየነው እውነት በመሆኑ ማስተባበያ አይቀርብበትም። ይልቁኑም ትምህርት ቤት፣ ክሊኒክና ሆስፒታል፣ ወፍጮ ቤትና የሃይማኖት ተቋም ማውደሙ አፈጣጠሩ ላይ ስህተት እንዳለ እንድናጠና፣ እንድንመረመር የሚያደርግ ሆኗል።

ከዝርፊያና ማውደሙ ቀጥሎ ሰዎች በዘራቸው ብቻ ተለይተው ከቀያቸው ድረስ በመጡ ወራሪ የትግሬ ኃይሎች ተጭፍጭፈዋል። በጅምላ ተቀብረዋል። ሴት እህቶቻችን ዕድሜና የጤና ሁኔታቸው ሳይለይ በደቦ ተደፍረዋል። ስሜትን በሚጎዳና መኖርን በሚተናነቅ ደረጃ ግፍ በንጹሃን ላይ ተፈጽሟል።

ይህ ምክንያት አልባ ወራሪ ቡድን አማራ ክልልን ብቻ ሳይሆን አፋርንም በተመሳሳይ አውድሟል። ንጹሃንን ገድሏል። ደፍሯል። በጅምላ ቀብሯል። ዛሬም “ዳግም ተደራጅቼ፣ ስልት ቀይሼ ዳግም እመጣለሁ” እያለ ነው። ሁለተኛ ዓላማው ያልዘርፈበትን አካባቢ አዳርሶ ለማውደምና “እኔ ከሞትኩ” እንዲሉ ወደ ዓመድ መቀየር እንደሆነ የመጀመሪያ ዘመቻው ማረጋገጫ ነው።

እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ በቅልብነት ዩቲዩብ ውስጥ ተቀርቅረው መርዝ የሚረጩት የአውዳሚው ትህነግ “ቅምጦች” ሳያንስ፣ በአገር ውስጥ በተለይም በአማራ ስም እየማሉ ከወዲሁ ሽርሸራ የጀመሩ እንዳለ እየታዩ ነው። በግል የፈለጉትን አቋም መያዛቸው ችግር ባይኖረውም፣ መከላከያን ለማሳነስ፣ መከላከያን ለመተቸት፣ መከላከያን ለመገሰጽ የሚሞክሩ የአገርና የአማራ ክልል ዕጢዎችን እያየን ነው።

ይህ ወራሪ ኃይል መውጫና መግቢያ አጥቶ የሞት ሽረት ውጊያ ላይ መሆኑ እየታወቀ፣ ለመውጫ ሁሉንም ዓይነት ጉድጓድ እየቆፈረ መሆኑ እየታየ፣ ከሸዋ ጀምሮ እየተገፋ ከመደምሰስ የተረፈው እየሸሸ ከኮምቦልቻ ከሚሴና ደሴ ኃይሉ ጋር እንድ ላይ ሲገጥም ሰፊ ቁጥር ያለው ኃይል መሆኑ በቂ ግንዛቤ እያለ፣ ልክ ጦርነቱ እንዳለቀና ድል እንደተጨበጠ በማስመሰል የጅግንነት ሽሚያ እየተስተዋለ ነው። ምንም ክፋት የማያውቁ አገር ወዳድ ፋኖዎችንና ሚሊሻዎችን በስልክ እየገኙ ለሳንቲም ለቀማና ለስውር ዓላማ ማስፈጸሚያ ሲደረግ እያየን ነው።

ዛሬ ዳያስፖራው ወገቡን አስሮ ለአገሩ እየሞገተ ነው። ዛሬ ደጀኑ ሕዝብ በሴረኞች የኑሮ ውድነት ቢጠብሰውም “አገሬ ትዳን” ብሎ ተነስቷል። ከዳር እስከዳር ማለት በሚቻል ደረጃ ሕዝብ አንድ ሆኖ የኃያላኑን መርዛማ ዘመቻ እየመከተ ነው። ትግሉ ገና መጀመሩ እንጂ ገና አልተነካም። እናም ተራ የዝና ሽሚያ ሌላ ዋጋ እንዳያስከፍለን እንጠንቀቅ። ፉከራና ቀረቶ አይጠቅምም። ዛሬ የፉከራና ወደላይ ጥይት በማንኳኳት የሚጮኽበት ወቅት አይድለም። አድብቶ፣ ዝም ብሎ፣ ፍም ሆኖ ጠላትን ማረመጥ እንጂ በየአቅጣጫው መዛበት ዳግም ውርደትን እንጂ ክብርን አይወልድም።

በዚህ የህልውና ዘመቻ ድንቅ የሪፖርት ስራ በመሥራት የተዋጣለት የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ተግባሩን በታላቅ ጥንቃቄ እያካሄደ ይገኛል። የወራሪውን ኃይል በስሙ “የትግሬ ወራሪ ሠራዊት/ኃይል” በማለት በመጥራትና በመሰየም የሠራው ብቻ ትልቅ ክብር የሚሰጠው ነው። የወልቃይትን ሰቆቃ፣ የጦር ሜዳ ውሎ፣ ያልተዘመረላቸውን ጀግኖች ወደፊት በማምጣት፣ ወዘተ አሁን እዚህ ተዘርዝሮ የማያልቅ ድንቅ የጋዜጠኛነት ተግባር በመፈጸም የአማራን ሕዝብ ብቻ ሳይሆን መላ ኢትዮጵያዊን ያነቃ የሚዲያ ተቋም ነው።

ወራሪውን የትግሬ ኃይል ከመቀሌ ሆነው ከሚመሩት ወንበዴዎች መካከል አንዳንዶቹ ሰሞኑን በሚዲያው ላይ ያወረዱት ውርጅብኝ በእርግጥም አሚኮ በጠንካራ መሠረት ላይ ያለ እና ሙያውን በተግባር እየፈጸመ የሚገኝ ተቋም መሆኑን ያስመሰከረ ነው። የዚያኑ ያህል ደግሞ በሤራ አወቃቀረር ወደር የማይገኝለት ትህነግ አሚኮን ለማጥቃትና ሰርጎገቦችን ለማስረጽ ዓላማ እንዳለው አመላካችም ተደርጎ መወሰድ ይገባዋል።    

ስለሆነም አሚኮ በዘመቻ ስም ያገኘውን ሁሉ አደባባይ አያምጣ። ትናንት ሻለቃ ዳዊት ወልደ ጊዮርጊስ የሚባል የክህደት ሊቅን ጋብዞ የሽግግር መንግሥትና ትህነግ መራሽ የአዲስ መንግሥት ምስረታ ሲያውጅ፣ አሁን ያለውን መንግሥት ዕውቅና እንደማይሰጡ ጦር ሜዳ ድረስ ወርደው እየተፋለሙ ያሉ መሪያችንን ሳይቀር ባገኘው አጋጣሚ ሲዘለፍ የከረመ፣ በሤራ የተገደሉ ውድ የአማራ አይተኬ ልጆች አሟሟት ላይ “ለአንድ ወገን” ወግኖ ለማተራመስ ሲጠቀምበት የነበረንና ዛሬ መረጃ ቴሌቪዥን ሲቀረቀርበት አማራ ቲቪ ፕሮግራም ላይ ማቅረብ አሳፋሪ ብቻ ሳይሆን እንዳንሸረሸርም የሚያሰጋ ነው። የመድረክ ተወዛዋዡን አበበ በለው በአሚኮ ላይ ቀርቦ ማየት ወይ ስለ ግለሰቡ ማንነት ሳይታወቅ የተፈጸመ ቅን ስህተት ነው፤ ወይም አሚኮ ጓዳውን እንዲመለከት የሚጋብዝ የማንቂ ደወል ነው።

የረሃብተኛ ኢትዮጵያውያንን ገንዘብ ዘርፎ አሜሪካ ቤት የገዛውና ከዚያው ሆኖ አገራችንን ለማፍረስ ዕድሜ ልኩን “ሲተጋ” የኖረውን ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስን የዛሬ ሰባት ወር አበበ በለው “ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ ሃቁን አፈረጡት” በማለት ዕድሜ ልኩን ሃቅን ሲጾማት የኖረውን ሰው አቅርቦት ነበር። አበበ ለሃያ አምስት ደቂቃ ዳዊትን በሙገሳ እስክስታ ሲያወርድለት ቆይቶ ሲያበቃ ዳዊትም በአጸፋው መልሶ “እንዳንተ ያለ …” ብሎ አበበን ሲያሞቀውና ውዳሴ አበበ ሲያቀርብለት “በእርሶ መሞገስ …” እየተባባሉ ጀምረው ኢትዮጵያ ላይ ያለውን ሕዝብ የመረጠውን መንግሥት እንደማይቀበሉ፣ የሽግግር መንግሥት መመሥረት አለበት፣ ከማት አልፎ “አማራና ኦሮሞ አብሮ መኖር አይችልም” የሚል ቅስቀሳ ማካሄዱ እየታወቀ፣ ዛሬ የአንበሳ ምስል እያሳየ “ማሸነፍ ብቻ” ለሚለው የአማራ ሚዲያ አበበ በለው እንዴት ሊመጥን ቻለ?

አበበ እየመራ ሻለቃው የጋለቡበትን የዩቲዩብ ቪዲዮ ላፍታ ተመልከቱ።

አበበ የሚታዘዝላቸው የሻለቃ ዳዊት አፍራሽ ኃይሎች ምን እየሠሩ እንደሆነ፣ ከማን ጋር ገጥመው አማራና ኦሮሞውን አላኩሰው እሳት ሊሞቁ እንደተዘጋጁ አቶ ተመስገን ጥሩነህን ደንነት ቢሮ ጎራ ብሎ መጠየቁ ብዙ መረጃ ይሰጣል።

ከዚህ ሌላ አበበ ራሱ በተደጋጋሚ በየቀኑ እየወጣ በሚናገርበት የሚያቀርባቸው እጅግ መርዛምና በሤራ የተሞሉ አፍራሽ ሃሳቦች እንዴት ተዘንግተው ነው ዛሬ የአሚኮ “ጀግና” ሆኖ ለዕውቅና የበቃው? ወይስ የሤራ ሽረባው የሚተላለፍበት መረጃ ሚዲያ ስለተዘጋና ድሉ ከትግሬ ወራሪ ኃይል እጅ ማምለጡ የ“አስገቡኝ” ማመልከቻ ነው? ጋዜጠኛውስ በምን መነሻ ነው አበበ ዕንግዳው ለማድረግ የበቃው? እንደ ጀግናው ታማኝ በየነ ወደ አገር ቤት ገብቶ ትግሉን አልተቀላቀለ? ወይም ሰሞኑን የፈጸመው አንድ የተለየ ተግባር የለ? ጀግኖቹ የቁርጥ ቀን የአብን ልጆች ዩሱፍና ጋሻው በሚቀርቡበት ስንቱ ጀግና በሚወደስበት ሚዲያ ለመንግሥት ግልበጣ ከሚያሤሩ ጋር የሚሞዳሞደው አበበ በለው በምን መሥፈርት ነው የአሚኮን ደጅ መርገጥ የቻለው? ወይስ ጋዜጠኛው ስለ አበበ ምንም ሳያውቅ ወይም እያወቀ የምንደኝነት ተግባሩን እየፈጸመ ነው?

በትግሬው ወራሪ ኃይል የወደሙ መሠረተልማቶችን መልሶ ለማቋቋም ብዙ ዕቅዶች እየወጡ ነው። ከእነርሱ አንዱ በዳያስፖራ የገንዘብ ማሰባሰብ ማካሄድ ነው። ታዲያ በውዳሴ የታጀበው ቃለምልልስ ለአበበ የ“አስገቡኝ” ማመልከቻ በር መክፈቻ ይሆን? ይህንን መፈጸም የትግሬ ወራሪ ኃይል ካፈረሰው በላይ የራስን እጅ በራስ ቢላ መጉመድ ነው የሚሆነው። ኮምቦልቻና ደሴ በትግሬ ወራሪ ኃይል ቁጥጥር ሥር የወደቁት በማንም ሳይሆን እዚያው ከተሞቹ ውስጥ ተወልደው ባደጉ ትግሬዎችና ባንዳዎች ፊት አውራሪነት እንደሆነ ጋሻውና ዩሱፍ በተደጋጋሚ ነግረውናል።

ከላይ እንዳልኩት በሙያዊ ልሕቀቱ ከፍተኛ ሽልማት የሚገባው የአሚኮ ሥራ በትህነግ ደጅ ብዙ ውዥንብር ፈጥሯል። ወደ በቀል የሚወስድ ብስጭትም አስነስቷል፤ ሤረኛው ትህነግ ደግሞ ለአማራ ሕዝብ መቼም እንደማይተኛ “ሒሳብ አወራርዳለሁ” በሚለው ቃሉ ነግሮናል። የደረሰብን መከራና ስቃይ ሳንጠረጥር ከመታረድ ይልቅ ጠርጥረን ብንሳሳት ትክክል ነው ወደሚል ድምዳሜ አድርሶናል። የሆነው ሆኖ ግን ከጋዜጠኛነት ሙያ ጽዱ የሆነው የዕውቀት ጾመኛው አበበ በለው በግብርም ሆነ በምግባር በአሚኮ መስኮት ለመታየት አይመጥንም፤ ቢቻል ማስተካከያ ተደርጎ ለወደፊት ጥንቃቄ ቢደረግ ጥቆማ እሰጣለሁ።

ዳዊት በለው


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Opinions Tagged With: operation dismantle tplf

Reader Interactions

Comments

  1. አምባው በቀለ says

    December 28, 2021 01:46 pm at 1:46 pm

    ሻለቃው በድርቅ የተጎዱ ኢትዮጵያውያንን ጉረሮ ዘግቶ ከእርዳታ መስተባበሪያ ኮሚሺን ከወያኔ ባልተናነሰ መልኩ ኢትዮጵያን ገንዘብ እና ንብረት ዘርፎ ከወያኔ ባልተናነሰ መልኩ ወገኖቹን በረሃብ አለንጋ የገረፈ ያስገረፈ፤የፈጀ ያስፈጀ፤ቁጥር አንድ የኢትዮጵያ ጠላት ሲሆን የሚዘርፈውን ዘርፎ እና አዘርፎ ወደ ሁለተኛ እናት እና አባቱ አገር የመጣው የስልጣን ጥመኛነቱን ለማርካት አለቆቹ የደርግ አባላትን ገልጦ ስልጣን መያዝ ስለተሳነው ነበር።በመሠረቱ ይህ ሰው ስልጣንን እንደተመኘ ሳይሳከለት በሁለት እግሩ መራመድ እየተሳነው በሁዊል ቸር መገፋት ደረጃ ደርሶም የስልጣን ጥመኝነቱ መርካት ባለመቻሉ ኑዛዜም ስልጣን ሲሆን የሰው ልጅ አንድ እናትና አንድ አባት ሲኖረው ይህ ሰው ግን ከሁለት እናትና ከሁለት አባት የተጸነሰ የሰንበት ጽንስ ነው።በመሆኑም “ቢጽ ለቢጽ” እንደሚባለው አበበ በለውም ወስፋቱን ለመሙላት የሚያደርገው ውጣ ውረድ በመሆኑ በአማራ ሚዲያ እንዲሁም በሌሎች እንዳይቀርብ ጥንቢራው ማለቱ የተሻለ ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule