
የኃይሌ ሆቴሎችና ሪዞርቶች ድርጅት በ500 ሚሊየን ብር በናዝሬት ከተማ ያስገነባው 7ኛው የኃይሌ ሪዞርት ዛሬ ተመርቋል።
በሪዞርቱ የምርቃት ሥነስርዓት ላይ ሻለቃ ኃይሌን ጨምሮ የሪዞርቱ የሥራ ኃላፊዎች መግለጫ ሰጥተዋል።
ዛሬ የተመረቀው ሪዞርት ሰፋፊና ምቹ የመመገቢያና የስብሰባ አዳራሾች ጨምሮ 106 የእንግዳ ማረፊያ ክፍሎች፣ የስፖርት ማዘወትሪያ ስፍራዎች፣ የመዋኛ ገንዳዎች እና ሌሎችንም መሠረተ ልማቶችን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል።
በናዝሬት የተገነባው ሰባተኛው ሪዞርት በ 500 ሚሊየን ወይም በግማሽ ቢሊየን ብር ወጪ ተገነባ መሆኑን ኃይሌ በመግለጫው ገልጿል።
ከዚያም ባለፈ 300 ለሚሆኑ ዜጎችም የሥራ ዕድል መፍጠሩን ተናግሯል።
ሪዞርቱ በግንባታም ሆነ በአገልግሎቱ ከሌሎች ሪዞርቶች ለየት ባለ መልኩ መቅረቡን የተናገረው ሻለቃ ሀይሌ÷ ከባለ 4 እና 5 ኮኮብ ደረጃን የሚያሟሉ አገልግሎቶችን እንደሚሠጥ ገልጿል።
ግንባታውንም ለማጠናቀቅ ሁለት ዓመታትን የፈጀ ሲሆን በአዲሱ ዓመት እየተገነቡ ያሉ ሶስት ሪዞርቶችእንደሚጠናቀቁ ገልጿል። (ከፋና እና ሌሎች የተጠናቀረ መረጃ)
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ
ይመስለኛል ሻለቃ ሃይሌ የሃበሻው ፓለቲካን ልብ አላለውም። በአንድ ቃለ መጠየቅ ላይ እንዲህ ሲል ሰማሁት ” አስር ጊዜም ቢቃጠል መልሼ እሰራለሁ” የእብደት መጀመሪያው ይህ ነው። እንዴት ሆን ተብሎ የሰው ሃብትና ንብረት ከእነ ህይወቱ እየተመረጠ በሚወድምበት የኦሮሞ ክልል ውስጥ ምንም ዋስትና ሳይኖርና ላይኖር እንደገና ንዋይ ይፈሳል? አስገራሚ የፓለቲካ ድራማ ነው። የኦሮሞን ለኦሮሞ የሚሉት የጠባብ ብሄርተኞች ስብስቦች በዚህም በዚያም ይህንም እንደሚያጋዪት የታወቀ ነገር ነው። ግን በዘሩ በሰከረ የፓለቲካ አለም ውስጥ እውነትና ውሸትን ለይቶ ህዝባዊ እይታ ለመያዝ አስቸጋሪ ነው።
አንድ የቢቢሲ ዘገባ በሰፋ መልኩ ኢትዮጵያ የዪጎዝላቪያ አይነት መሰነጣጠቅ ይገጥማታል በማለት ያቀረበውን ዘገባ ስመለከት እኔም ለዘመናት ወያኔ የሃገር መሪ ሆኖ ቆርሶ መውሰድንና መስጠትን ከጀመረ ወዲህ ሃገር ትኖራለች የሚል እምነት ኑሮኝ አያውቅም። አሁን መቀሌ ላይ ሆኖ አሻፈረኝ የሚለው ገንጣይና አስገንጣይ ቡድን ከግብጽና ከሱዳን ጋር በማበር ኢትዮጵያን ፍርክርኳን እንደሚያወጣት ጭራሽ አልጠራጠርም። ልክ እንደ ወያኔ የኦሮሞ ፓለቲከኞችም ጥላቸው በኢትዮጵያ አንድ መሆን ላይ ነው። ህገ መንግስቱ አልተከበረም የሚለው ወያኔ 27 ዓመት ሙሉ ሲያፍን ሲያስገድል ሲገድል አካል ሲያጎል ሲዘርፍ ጥፍር ሲነቅል ሶዶማዊ ተግባር ሲፈጽም የነበረ ድርጅት አሁን ለመብት ተሟጋች ሆኖ መቅረቡ የፓለቲካውን ዝቅጠት ያሳያል። ፓለቲካ የእብዶች መጠለያ ጊዜአዊ ድንኳን ነው የምለውም ለዚሁ ነው። ትላንት ሲገርፈው፤ ሲዘርፈው፤ እንደ ለማኝ አቆማዳ ሲፈታ ሲያስረው ከነበረው የወያኔ ሃይል ጋር ነው አሁን ኦሮሞዎቹ ቂጥ ገጥመው በወለጋ በነጻነት ስም ሰው የሚገድሉትና የሚዘርፉት። ይባስ ብሎ አሁን በቅርብ ቀን ብቅ ያሉ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ባሌ ላይ ሾንኮፉን የተከለና በሌሎችም የኦሮሞ ክልሎች እየተንሰራፋ ያለ የእስልምና እምነትን ተከትሎ የጃሃድ ውጊያ የሚያራምድ ቡድን አማርኛ ቋንቋ እየተናገረ ብቅ ማለቱን በቪዲዪ በተደገፈ መረጃ ተመልክተናል። አረቡና ለነጩ አለም እኛ እንድንገድልና እንድንገዳደል የፈለገውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ በፊትም የታወቀ ነው። ታዲያ በዚህ ሁሉ የፓለቲካ አሸሸ ገዳሚ ውስጥ ዘፋኝና አቀንቃኝን ለይቶ ማወቅ እጅግ ከባድ ነው። የሃበሻ ፓለቲከኞች እድል ፈንታ ሶስት ነው። ግዞት፤ እስራትና ሞት። ኢትዮጵያ ተከባለች። በሱዳን በሱዳኖች፤ በሶማሊያ በሱማሊያዎችና በቱርኮች፤ በኬኒያ ድንበር በኦሮሞ ተኩሶ ሯጭ ስመ ታጋዪች በሃገር ውስጥ በስም በበዙ የተቃዋሚ ፓለቲከኞች ነን በሚሉ ጽንፈኞች፤ በሰሜን በወያኔ የጦር መሳሪያና ድንፋታ ዙሪያዋ ተከቧል። ይህን ሁሉ መከራና ጉድ ያልመዘነ ገንዘቡን በሜዳ ላይ እንደበተነ የሚቆጠረው የሃይሌ ሪዞርት የወደፊት እድል ፈንታ ምን እንደሚሆን ከአሁኑ መገመት ይቻላል። ልሽጥ ቢል እንኳን በህጋዊ መንገድ መሸጥ የማይችልበት ቦታ ላይ ወደ 20 ሚሊዪን ዶላር ማፍሰስ አዋቂነት ነው አልልም። ግን ለሃገሩና ለወገኑ ሃሳቢ ለመሆኑ ሌላ ምስክር አያሻኝም። የእኔ ሃሳብ አያሰሩትም። ሃገሪቱ በዘር ሰክራለች ነው። በቃኝ!