• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የግማሽ ቢሊዮን ብሩ የናዝሬቱ ኃይሌ ሪዞርት ተመረቀ

September 3, 2020 09:39 pm by Editor 1 Comment

የኃይሌ ሆቴሎችና ሪዞርቶች ድርጅት በ500 ሚሊየን ብር በናዝሬት ከተማ ያስገነባው 7ኛው የኃይሌ ሪዞርት ዛሬ ተመርቋል።

በሪዞርቱ የምርቃት ሥነስርዓት ላይ ሻለቃ ኃይሌን ጨምሮ የሪዞርቱ የሥራ ኃላፊዎች መግለጫ ሰጥተዋል።

ዛሬ የተመረቀው ሪዞርት ሰፋፊና ምቹ የመመገቢያና የስብሰባ አዳራሾች ጨምሮ 106 የእንግዳ ማረፊያ ክፍሎች፣ የስፖርት ማዘወትሪያ ስፍራዎች፣ የመዋኛ ገንዳዎች እና ሌሎችንም መሠረተ ልማቶችን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል።

በናዝሬት የተገነባው ሰባተኛው ሪዞርት በ 500 ሚሊየን ወይም በግማሽ ቢሊየን ብር ወጪ ተገነባ መሆኑን ኃይሌ በመግለጫው ገልጿል።

ከዚያም ባለፈ 300 ለሚሆኑ ዜጎችም የሥራ ዕድል መፍጠሩን ተናግሯል።

ሪዞርቱ በግንባታም ሆነ በአገልግሎቱ ከሌሎች ሪዞርቶች ለየት ባለ መልኩ መቅረቡን የተናገረው ሻለቃ ሀይሌ÷ ከባለ 4 እና 5 ኮኮብ ደረጃን የሚያሟሉ አገልግሎቶችን እንደሚሠጥ ገልጿል።

ግንባታውንም ለማጠናቀቅ ሁለት ዓመታትን የፈጀ ሲሆን በአዲሱ ዓመት እየተገነቡ ያሉ ሶስት ሪዞርቶችእንደሚጠናቀቁ ገልጿል። (ከፋና እና ሌሎች የተጠናቀረ መረጃ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Right Column, Social Tagged With: haile resort

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    September 5, 2020 01:33 pm at 1:33 pm

    ይመስለኛል ሻለቃ ሃይሌ የሃበሻው ፓለቲካን ልብ አላለውም። በአንድ ቃለ መጠየቅ ላይ እንዲህ ሲል ሰማሁት ” አስር ጊዜም ቢቃጠል መልሼ እሰራለሁ” የእብደት መጀመሪያው ይህ ነው። እንዴት ሆን ተብሎ የሰው ሃብትና ንብረት ከእነ ህይወቱ እየተመረጠ በሚወድምበት የኦሮሞ ክልል ውስጥ ምንም ዋስትና ሳይኖርና ላይኖር እንደገና ንዋይ ይፈሳል? አስገራሚ የፓለቲካ ድራማ ነው። የኦሮሞን ለኦሮሞ የሚሉት የጠባብ ብሄርተኞች ስብስቦች በዚህም በዚያም ይህንም እንደሚያጋዪት የታወቀ ነገር ነው። ግን በዘሩ በሰከረ የፓለቲካ አለም ውስጥ እውነትና ውሸትን ለይቶ ህዝባዊ እይታ ለመያዝ አስቸጋሪ ነው።
    አንድ የቢቢሲ ዘገባ በሰፋ መልኩ ኢትዮጵያ የዪጎዝላቪያ አይነት መሰነጣጠቅ ይገጥማታል በማለት ያቀረበውን ዘገባ ስመለከት እኔም ለዘመናት ወያኔ የሃገር መሪ ሆኖ ቆርሶ መውሰድንና መስጠትን ከጀመረ ወዲህ ሃገር ትኖራለች የሚል እምነት ኑሮኝ አያውቅም። አሁን መቀሌ ላይ ሆኖ አሻፈረኝ የሚለው ገንጣይና አስገንጣይ ቡድን ከግብጽና ከሱዳን ጋር በማበር ኢትዮጵያን ፍርክርኳን እንደሚያወጣት ጭራሽ አልጠራጠርም። ልክ እንደ ወያኔ የኦሮሞ ፓለቲከኞችም ጥላቸው በኢትዮጵያ አንድ መሆን ላይ ነው። ህገ መንግስቱ አልተከበረም የሚለው ወያኔ 27 ዓመት ሙሉ ሲያፍን ሲያስገድል ሲገድል አካል ሲያጎል ሲዘርፍ ጥፍር ሲነቅል ሶዶማዊ ተግባር ሲፈጽም የነበረ ድርጅት አሁን ለመብት ተሟጋች ሆኖ መቅረቡ የፓለቲካውን ዝቅጠት ያሳያል። ፓለቲካ የእብዶች መጠለያ ጊዜአዊ ድንኳን ነው የምለውም ለዚሁ ነው። ትላንት ሲገርፈው፤ ሲዘርፈው፤ እንደ ለማኝ አቆማዳ ሲፈታ ሲያስረው ከነበረው የወያኔ ሃይል ጋር ነው አሁን ኦሮሞዎቹ ቂጥ ገጥመው በወለጋ በነጻነት ስም ሰው የሚገድሉትና የሚዘርፉት። ይባስ ብሎ አሁን በቅርብ ቀን ብቅ ያሉ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ባሌ ላይ ሾንኮፉን የተከለና በሌሎችም የኦሮሞ ክልሎች እየተንሰራፋ ያለ የእስልምና እምነትን ተከትሎ የጃሃድ ውጊያ የሚያራምድ ቡድን አማርኛ ቋንቋ እየተናገረ ብቅ ማለቱን በቪዲዪ በተደገፈ መረጃ ተመልክተናል። አረቡና ለነጩ አለም እኛ እንድንገድልና እንድንገዳደል የፈለገውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ በፊትም የታወቀ ነው። ታዲያ በዚህ ሁሉ የፓለቲካ አሸሸ ገዳሚ ውስጥ ዘፋኝና አቀንቃኝን ለይቶ ማወቅ እጅግ ከባድ ነው። የሃበሻ ፓለቲከኞች እድል ፈንታ ሶስት ነው። ግዞት፤ እስራትና ሞት። ኢትዮጵያ ተከባለች። በሱዳን በሱዳኖች፤ በሶማሊያ በሱማሊያዎችና በቱርኮች፤ በኬኒያ ድንበር በኦሮሞ ተኩሶ ሯጭ ስመ ታጋዪች በሃገር ውስጥ በስም በበዙ የተቃዋሚ ፓለቲከኞች ነን በሚሉ ጽንፈኞች፤ በሰሜን በወያኔ የጦር መሳሪያና ድንፋታ ዙሪያዋ ተከቧል። ይህን ሁሉ መከራና ጉድ ያልመዘነ ገንዘቡን በሜዳ ላይ እንደበተነ የሚቆጠረው የሃይሌ ሪዞርት የወደፊት እድል ፈንታ ምን እንደሚሆን ከአሁኑ መገመት ይቻላል። ልሽጥ ቢል እንኳን በህጋዊ መንገድ መሸጥ የማይችልበት ቦታ ላይ ወደ 20 ሚሊዪን ዶላር ማፍሰስ አዋቂነት ነው አልልም። ግን ለሃገሩና ለወገኑ ሃሳቢ ለመሆኑ ሌላ ምስክር አያሻኝም። የእኔ ሃሳብ አያሰሩትም። ሃገሪቱ በዘር ሰክራለች ነው። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule