• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የግማሽ ቢሊዮን ብሩ የናዝሬቱ ኃይሌ ሪዞርት ተመረቀ

September 3, 2020 09:39 pm by Editor 1 Comment

የኃይሌ ሆቴሎችና ሪዞርቶች ድርጅት በ500 ሚሊየን ብር በናዝሬት ከተማ ያስገነባው 7ኛው የኃይሌ ሪዞርት ዛሬ ተመርቋል።

በሪዞርቱ የምርቃት ሥነስርዓት ላይ ሻለቃ ኃይሌን ጨምሮ የሪዞርቱ የሥራ ኃላፊዎች መግለጫ ሰጥተዋል።

ዛሬ የተመረቀው ሪዞርት ሰፋፊና ምቹ የመመገቢያና የስብሰባ አዳራሾች ጨምሮ 106 የእንግዳ ማረፊያ ክፍሎች፣ የስፖርት ማዘወትሪያ ስፍራዎች፣ የመዋኛ ገንዳዎች እና ሌሎችንም መሠረተ ልማቶችን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል።

በናዝሬት የተገነባው ሰባተኛው ሪዞርት በ 500 ሚሊየን ወይም በግማሽ ቢሊየን ብር ወጪ ተገነባ መሆኑን ኃይሌ በመግለጫው ገልጿል።

ከዚያም ባለፈ 300 ለሚሆኑ ዜጎችም የሥራ ዕድል መፍጠሩን ተናግሯል።

ሪዞርቱ በግንባታም ሆነ በአገልግሎቱ ከሌሎች ሪዞርቶች ለየት ባለ መልኩ መቅረቡን የተናገረው ሻለቃ ሀይሌ÷ ከባለ 4 እና 5 ኮኮብ ደረጃን የሚያሟሉ አገልግሎቶችን እንደሚሠጥ ገልጿል።

ግንባታውንም ለማጠናቀቅ ሁለት ዓመታትን የፈጀ ሲሆን በአዲሱ ዓመት እየተገነቡ ያሉ ሶስት ሪዞርቶችእንደሚጠናቀቁ ገልጿል። (ከፋና እና ሌሎች የተጠናቀረ መረጃ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Right Column, Social Tagged With: haile resort

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    September 5, 2020 01:33 pm at 1:33 pm

    ይመስለኛል ሻለቃ ሃይሌ የሃበሻው ፓለቲካን ልብ አላለውም። በአንድ ቃለ መጠየቅ ላይ እንዲህ ሲል ሰማሁት ” አስር ጊዜም ቢቃጠል መልሼ እሰራለሁ” የእብደት መጀመሪያው ይህ ነው። እንዴት ሆን ተብሎ የሰው ሃብትና ንብረት ከእነ ህይወቱ እየተመረጠ በሚወድምበት የኦሮሞ ክልል ውስጥ ምንም ዋስትና ሳይኖርና ላይኖር እንደገና ንዋይ ይፈሳል? አስገራሚ የፓለቲካ ድራማ ነው። የኦሮሞን ለኦሮሞ የሚሉት የጠባብ ብሄርተኞች ስብስቦች በዚህም በዚያም ይህንም እንደሚያጋዪት የታወቀ ነገር ነው። ግን በዘሩ በሰከረ የፓለቲካ አለም ውስጥ እውነትና ውሸትን ለይቶ ህዝባዊ እይታ ለመያዝ አስቸጋሪ ነው።
    አንድ የቢቢሲ ዘገባ በሰፋ መልኩ ኢትዮጵያ የዪጎዝላቪያ አይነት መሰነጣጠቅ ይገጥማታል በማለት ያቀረበውን ዘገባ ስመለከት እኔም ለዘመናት ወያኔ የሃገር መሪ ሆኖ ቆርሶ መውሰድንና መስጠትን ከጀመረ ወዲህ ሃገር ትኖራለች የሚል እምነት ኑሮኝ አያውቅም። አሁን መቀሌ ላይ ሆኖ አሻፈረኝ የሚለው ገንጣይና አስገንጣይ ቡድን ከግብጽና ከሱዳን ጋር በማበር ኢትዮጵያን ፍርክርኳን እንደሚያወጣት ጭራሽ አልጠራጠርም። ልክ እንደ ወያኔ የኦሮሞ ፓለቲከኞችም ጥላቸው በኢትዮጵያ አንድ መሆን ላይ ነው። ህገ መንግስቱ አልተከበረም የሚለው ወያኔ 27 ዓመት ሙሉ ሲያፍን ሲያስገድል ሲገድል አካል ሲያጎል ሲዘርፍ ጥፍር ሲነቅል ሶዶማዊ ተግባር ሲፈጽም የነበረ ድርጅት አሁን ለመብት ተሟጋች ሆኖ መቅረቡ የፓለቲካውን ዝቅጠት ያሳያል። ፓለቲካ የእብዶች መጠለያ ጊዜአዊ ድንኳን ነው የምለውም ለዚሁ ነው። ትላንት ሲገርፈው፤ ሲዘርፈው፤ እንደ ለማኝ አቆማዳ ሲፈታ ሲያስረው ከነበረው የወያኔ ሃይል ጋር ነው አሁን ኦሮሞዎቹ ቂጥ ገጥመው በወለጋ በነጻነት ስም ሰው የሚገድሉትና የሚዘርፉት። ይባስ ብሎ አሁን በቅርብ ቀን ብቅ ያሉ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ባሌ ላይ ሾንኮፉን የተከለና በሌሎችም የኦሮሞ ክልሎች እየተንሰራፋ ያለ የእስልምና እምነትን ተከትሎ የጃሃድ ውጊያ የሚያራምድ ቡድን አማርኛ ቋንቋ እየተናገረ ብቅ ማለቱን በቪዲዪ በተደገፈ መረጃ ተመልክተናል። አረቡና ለነጩ አለም እኛ እንድንገድልና እንድንገዳደል የፈለገውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ በፊትም የታወቀ ነው። ታዲያ በዚህ ሁሉ የፓለቲካ አሸሸ ገዳሚ ውስጥ ዘፋኝና አቀንቃኝን ለይቶ ማወቅ እጅግ ከባድ ነው። የሃበሻ ፓለቲከኞች እድል ፈንታ ሶስት ነው። ግዞት፤ እስራትና ሞት። ኢትዮጵያ ተከባለች። በሱዳን በሱዳኖች፤ በሶማሊያ በሱማሊያዎችና በቱርኮች፤ በኬኒያ ድንበር በኦሮሞ ተኩሶ ሯጭ ስመ ታጋዪች በሃገር ውስጥ በስም በበዙ የተቃዋሚ ፓለቲከኞች ነን በሚሉ ጽንፈኞች፤ በሰሜን በወያኔ የጦር መሳሪያና ድንፋታ ዙሪያዋ ተከቧል። ይህን ሁሉ መከራና ጉድ ያልመዘነ ገንዘቡን በሜዳ ላይ እንደበተነ የሚቆጠረው የሃይሌ ሪዞርት የወደፊት እድል ፈንታ ምን እንደሚሆን ከአሁኑ መገመት ይቻላል። ልሽጥ ቢል እንኳን በህጋዊ መንገድ መሸጥ የማይችልበት ቦታ ላይ ወደ 20 ሚሊዪን ዶላር ማፍሰስ አዋቂነት ነው አልልም። ግን ለሃገሩና ለወገኑ ሃሳቢ ለመሆኑ ሌላ ምስክር አያሻኝም። የእኔ ሃሳብ አያሰሩትም። ሃገሪቱ በዘር ሰክራለች ነው። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule