• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ

February 4, 2021 08:48 am by Editor 1 Comment

የጦር ሃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ሌ/ጄ አበባው ታደሰን ጨምሮ ጄኔራል መኮንኖችንና ከፍተኛ የጦር አዛዦች በትግራይ ልዩ ሃይል ተገድለዋል የሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ።

ግለሰቡ በተጨማሪም ሎችንም የሀሰት መረጃዎች “የትግራይ ልዩ ሃይል ድል” በሚል ርዕስ ፍሪደም ቲቪ በተባለ የዩቲዩብ አድራሻ በተለያ ጊዜ ያልተጨበጠ መረጃ ያሰራጭ እንደነበረ ተገልጿል።

ይህ ሃጎስ ሰልጠነ ፍስሃዬ የተባለው ግለሰብ ከአዲስ አበባ በመነሳት ኬንያ ከዛም ወደ ዩጋንዳ ካምፓላ ለመውጣት ሲሞክር ሃዋሳ ላይ በደቡብ ዕዝ የሰራዊት አባላት በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገልጿል።

ስራውን እንዲሰራ የቀጠረው እንግሊዝ አገር የሚኖረው ዳዊት አብርሃ ዘረዝጊ የተባለ ሰው መሆኑንና ለአገልግሎቱም 6 መቶ የአሜሪካን ዶላር ይከፍለው እንደነበር ግለሰቡ ተናግሯል፡፡

የሚያሰራጨውን የሃሰት መረጃም እንግሊዝ አገር ሆኖ ዩቲዩቡን ከሚያስተዳድረው ዳዊት አብርሃ እንደሚሰጠውና እሱም በውጭ ካሉ አፍራሽ እንቅስቃሴ ካላቸው ከተለያዩ የቴሌቪዝን ጣቢያዎችና ከግለሰቦች ማህበራዊ ገፅ የሚያገኘውን ያልተጣራ መረጃ አሰሪውን በማስፈቀድ ይጠቀም እንደነበርም በተለይ ለደቡብ ዕዝ ሚዲያ ቡድን ተናግሯል።

ይህንን ስራ ከአመት በፊት እንደ ጀመረ የሚናገረው ግለሰቡ፣ መንግስት በትግራይ የህግ ማስከበር ከጀመረ ጊዜ ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ያልተጨበጠ የበሬ ወለደ መረጃ ማሰራጨት እንደጀመረና “እየቆየሁ ስሄድም እየሰራሁት ያለው ወንጀል የደህንነት ስጋት ላይ ስለጣለኝ፣ ከአገር ለመውጣት ስንቀሳቀስ ነው በመከላከያ በቁጥጥር ስር የዋልኩት” ብሏል።

ደቡብ ዕዝ የሃሰት መረጃ አሰራጭውን ሃጎስ ሰልጠነን ጨምሮ ከአገር ሊወጡ የነበሩ 8 ሰዎችን እና 4 በህገ ወጥ ዝውውሩ ላይ ተሳትፎ የነበራቸውን ግለሰቦች ለፌዴራል ፖሊስ ማስረከቡን ሌ/ኮ ግርማ አየለ አረጋግጠዋል፡፡

ህገ ወጦችን በመያዙ ሂደት የደቡብ ዕዝ የሰራዊት አባላት የነበራቸው ተሳትፎ የሚደነቅ ነበር ሲሉም ተናግረዋል ሲል የመከላከያ ሰራዊት አስታውቋል። (ኢ.ፕ.ድ.)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: fake news, operation dismantle tplf, social media fake info, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. አለም says

    February 5, 2021 04:15 pm at 4:15 pm

    ውድ ጎልጒል፣
    ይህን ማውሳት ምን ይጠቅማል? ይህንኑ ዜና ከነመረጃው በእንግሊዝኛ ቪዲዮ ተቀርጾ እዚያው በውጭ ሚድያ ማሠራጨት ነው! ሃጎስ ያልከው ግለሰብ እንግሊዝ ተቀምጦ ሽብር መፍጠር ትልቅ ወንጀል መሆኑን የዘነጋ ይመስለኛል፤ ወይም አይነቃም ብሎ ይሆናል! ኢትዮጵያውያን ምነው ቀልብ ነሳቸው፤ የቋንቋ ብቃት ያላቸው ስንቱን ጒዳይ በመረጃ አስደግፈው አክብሮትና ከስድብ በጠራ መልኩ ቢዘግቡ ህወሓት ፈረንጆችንና ዲቃሎቻቸውን በገንዘብ አሠማርቶ የሚያወናብደው ይከሽፍ ነበር። ጦር ሃይላችን ይህን ያክል ጀግንነት አሳይቶን እንዴት በእኛ ስንፍና ዋጋ ይጣ? ህወሓት እስካሁን የዓለምን ማህበረሰብ ቀልብ ለመሳብ የተጠቀመባቸው ነጥቦች፦
    ፩/ አስገድዶ ሴቶችን መድፈር (እነ ስዬ አብርሃ፣ ስብሃት፣ ደ/ጽዮን ወዘተ ሲያደርጉት የነበረውን ማለት ነው
    ፪/ መስጊድና አክሱም ጽዮንን ማፈረስ ሰባት መቶ ሃምሳ አማንያንን ማረድ (ከሳምንት በፊት አምስት መቶ ነበር)
    ፫/ ረሃብን እንደ መሳሪያ መጠቀም (ህወሓት ሲያደርገው የነበረውና ደርግ ሲከሥሥበት የነበረው)
    ፬/ ኢንዱስትሪዎችን አውራ መንገዶችን በቦንብ ማፈራረስ (ህወሓት ቀድሞ የፌዴራል ጸጥታ አስከባሪዎችን ለማስቆም ያደረገው ወንጀል ነው)
    ፭/ ደ/ጽዮን ድምጹን በወያኔ ሬዲዮ አስተላለፈ (ቪኦኤ ያስተላለፈው)፤
    ፮/ ጠ/ሚ ዐቢይ ዲክታተር ሆነ፤ ኖቤል ሽልማቱ ይሠረዝ የሚሉ፣ ወዘተ

    ይህ ሁሉ ውንጀላና ቱልቱላ፣ ህወሓት ሰላማዊ ሕዝብ ትግሬ አይደላችሁም ብሎ መፍጀቱን፣ አብሮ የተሰለፈውን፣ የትግራይን ሕዝብ አጨዳና አንበጣ ማጥፋት ሲረዳ የዋለውን በተኛበት የፈጸመበትን አሠቃቂ ጭፍጨፋ ለማረሳሳት ነው!
    መረጃው እንደ ቅጠል የትም ተበትኖ እያለ፣ በአገር ወዳድ ወገኖቻችን ንዝህላልነት ዋጋ እያጣ ነው!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule