
የጦር ሃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ሌ/ጄ አበባው ታደሰን ጨምሮ ጄኔራል መኮንኖችንና ከፍተኛ የጦር አዛዦች በትግራይ ልዩ ሃይል ተገድለዋል የሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ።
ግለሰቡ በተጨማሪም ሎችንም የሀሰት መረጃዎች “የትግራይ ልዩ ሃይል ድል” በሚል ርዕስ ፍሪደም ቲቪ በተባለ የዩቲዩብ አድራሻ በተለያ ጊዜ ያልተጨበጠ መረጃ ያሰራጭ እንደነበረ ተገልጿል።
ይህ ሃጎስ ሰልጠነ ፍስሃዬ የተባለው ግለሰብ ከአዲስ አበባ በመነሳት ኬንያ ከዛም ወደ ዩጋንዳ ካምፓላ ለመውጣት ሲሞክር ሃዋሳ ላይ በደቡብ ዕዝ የሰራዊት አባላት በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገልጿል።
ስራውን እንዲሰራ የቀጠረው እንግሊዝ አገር የሚኖረው ዳዊት አብርሃ ዘረዝጊ የተባለ ሰው መሆኑንና ለአገልግሎቱም 6 መቶ የአሜሪካን ዶላር ይከፍለው እንደነበር ግለሰቡ ተናግሯል፡፡
የሚያሰራጨውን የሃሰት መረጃም እንግሊዝ አገር ሆኖ ዩቲዩቡን ከሚያስተዳድረው ዳዊት አብርሃ እንደሚሰጠውና እሱም በውጭ ካሉ አፍራሽ እንቅስቃሴ ካላቸው ከተለያዩ የቴሌቪዝን ጣቢያዎችና ከግለሰቦች ማህበራዊ ገፅ የሚያገኘውን ያልተጣራ መረጃ አሰሪውን በማስፈቀድ ይጠቀም እንደነበርም በተለይ ለደቡብ ዕዝ ሚዲያ ቡድን ተናግሯል።
ይህንን ስራ ከአመት በፊት እንደ ጀመረ የሚናገረው ግለሰቡ፣ መንግስት በትግራይ የህግ ማስከበር ከጀመረ ጊዜ ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ያልተጨበጠ የበሬ ወለደ መረጃ ማሰራጨት እንደጀመረና “እየቆየሁ ስሄድም እየሰራሁት ያለው ወንጀል የደህንነት ስጋት ላይ ስለጣለኝ፣ ከአገር ለመውጣት ስንቀሳቀስ ነው በመከላከያ በቁጥጥር ስር የዋልኩት” ብሏል።
ደቡብ ዕዝ የሃሰት መረጃ አሰራጭውን ሃጎስ ሰልጠነን ጨምሮ ከአገር ሊወጡ የነበሩ 8 ሰዎችን እና 4 በህገ ወጥ ዝውውሩ ላይ ተሳትፎ የነበራቸውን ግለሰቦች ለፌዴራል ፖሊስ ማስረከቡን ሌ/ኮ ግርማ አየለ አረጋግጠዋል፡፡
ህገ ወጦችን በመያዙ ሂደት የደቡብ ዕዝ የሰራዊት አባላት የነበራቸው ተሳትፎ የሚደነቅ ነበር ሲሉም ተናግረዋል ሲል የመከላከያ ሰራዊት አስታውቋል። (ኢ.ፕ.ድ.)
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ
ውድ ጎልጒል፣
ይህን ማውሳት ምን ይጠቅማል? ይህንኑ ዜና ከነመረጃው በእንግሊዝኛ ቪዲዮ ተቀርጾ እዚያው በውጭ ሚድያ ማሠራጨት ነው! ሃጎስ ያልከው ግለሰብ እንግሊዝ ተቀምጦ ሽብር መፍጠር ትልቅ ወንጀል መሆኑን የዘነጋ ይመስለኛል፤ ወይም አይነቃም ብሎ ይሆናል! ኢትዮጵያውያን ምነው ቀልብ ነሳቸው፤ የቋንቋ ብቃት ያላቸው ስንቱን ጒዳይ በመረጃ አስደግፈው አክብሮትና ከስድብ በጠራ መልኩ ቢዘግቡ ህወሓት ፈረንጆችንና ዲቃሎቻቸውን በገንዘብ አሠማርቶ የሚያወናብደው ይከሽፍ ነበር። ጦር ሃይላችን ይህን ያክል ጀግንነት አሳይቶን እንዴት በእኛ ስንፍና ዋጋ ይጣ? ህወሓት እስካሁን የዓለምን ማህበረሰብ ቀልብ ለመሳብ የተጠቀመባቸው ነጥቦች፦
፩/ አስገድዶ ሴቶችን መድፈር (እነ ስዬ አብርሃ፣ ስብሃት፣ ደ/ጽዮን ወዘተ ሲያደርጉት የነበረውን ማለት ነው
፪/ መስጊድና አክሱም ጽዮንን ማፈረስ ሰባት መቶ ሃምሳ አማንያንን ማረድ (ከሳምንት በፊት አምስት መቶ ነበር)
፫/ ረሃብን እንደ መሳሪያ መጠቀም (ህወሓት ሲያደርገው የነበረውና ደርግ ሲከሥሥበት የነበረው)
፬/ ኢንዱስትሪዎችን አውራ መንገዶችን በቦንብ ማፈራረስ (ህወሓት ቀድሞ የፌዴራል ጸጥታ አስከባሪዎችን ለማስቆም ያደረገው ወንጀል ነው)
፭/ ደ/ጽዮን ድምጹን በወያኔ ሬዲዮ አስተላለፈ (ቪኦኤ ያስተላለፈው)፤
፮/ ጠ/ሚ ዐቢይ ዲክታተር ሆነ፤ ኖቤል ሽልማቱ ይሠረዝ የሚሉ፣ ወዘተ
ይህ ሁሉ ውንጀላና ቱልቱላ፣ ህወሓት ሰላማዊ ሕዝብ ትግሬ አይደላችሁም ብሎ መፍጀቱን፣ አብሮ የተሰለፈውን፣ የትግራይን ሕዝብ አጨዳና አንበጣ ማጥፋት ሲረዳ የዋለውን በተኛበት የፈጸመበትን አሠቃቂ ጭፍጨፋ ለማረሳሳት ነው!
መረጃው እንደ ቅጠል የትም ተበትኖ እያለ፣ በአገር ወዳድ ወገኖቻችን ንዝህላልነት ዋጋ እያጣ ነው!