• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያ መንግሥት ምንም አይነት ማብራሪያ እና ማረጋገጫ የማቅረብ ግዴታ የለበትም!

October 7, 2021 12:27 pm by Editor Leave a Comment

ትላንት ማክሰኞ መስከረም 26 የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት በኢትዮጵያ ጉዳይ ስብሰባ ሲቀመጥ 2 ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ይኸኛው ለ4ኛ ጊዜ (በዝግ እና በክፍት) ነው።

ይኸኛው ስብሰባው ለምን ተጠራ?

– ኢትዮጵያ 7 የተመድ ሰራተኞችን ከሀገር በማስወጣቷ።

– የሰሜን ኢትዮጵያ ሰብዓዊ ሁኔታ ላይ ለመወያየት።

ስብሰባው እንዲካሄድ የጠየቁት፦ አሜሪካ፣ ዩኬ፣ ኖርዌይ፣ ኢስቶኒያ፣ ፈረንሳይ እና አየርላንድ ናቸው።

በስብሰባው ላይ የኢትዮጵያ ተወካይ አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የተመድ ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ንግግር አድርገዋል። የምክር ቤቱ አባል ሀገራት የተለያዩ ሀሳቦችን ሰንዝረዋል።

ሙሉ ውይይቱን (ክፍት ውይይት ስለሆነ) በተመድ የዩትዩብ ቻናል መከታተል እንደምትችሉ እየጠቆምን የተነሱ ዋና ሃሳቦችን ግን በአጭሩ እንዳስሳለን።

አንቶኒዮ ጉተሬዝ ምን አሉ?

እየተስፋፋ የመጣውን የሰብዓዊ ጉዳይ ችግር ካለፈው ነሃሴ አንስቶ ሲያሳስቡ መቆየታቸውን ነገር ግን ችግሩ እየተባባሰ መምጣቱን ተናግረዋል።

7 ሚሊዮን ሰው በትግራይ፣ አማራ እና አፋር የምግብ እና የተለያዩ አፋጣኝ ድጋፎች እንደሚፈልግ ተናግረው 400 ሺህ ሰዎች ረሃብ በሚመስል ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

ላለው ችግር በቅርቡ መፍትሄ ካልተፈለገ ሁኔታው ሶማሊያ የዛሬ 10 ዓመት ገጥሟት የነበረውን አይነት 200 ሺህ ሰው ያለቀበትን ረሃብ ሁኔታ ወደሚመስል አደጋ ሊለወጥ ይችላል ሲሉ አበክረው አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት ተፈላጊነት የሌላቸው ሲል የወሰነባቸው እና ከሀገር ያስወጣቸው 7 የተመድ አባላት በአፋጣኝ ወደስራቸው እንዲመለሱ እንዲደረግ አሳስበዋል።

ሌሎችም አሉ ያሉትን ችግሮች አንስተው በኢትዮጵያ ያሉ ወገኖች በአፋጣኝ ለሰላም እና ለድርድር እንዲቀመጡ ግጭትም በፍጥነት እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል።

ንግግር የሰላም መሰረት መሆኑን ተናግረው ሰላም የብልፅግና እና የመረጋጋት መሰረት ነው ብለዋል፤ ለሁሉም ኢትዮጵያውያን እና ለአካባቢው ህዝብም ጠንክረን እንስራ ሲሉ ተደምጠዋል።

ከሁለት ቀን በፊት የተመሰረተው እና በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ መንግስት ጠንካራዋን ኢትዮጵያ እንደሚመለስ ተስፋ አደርጋለሁ ያሉ ሲሆን፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ሁሉን አካታች ውይይት ለማድረግ የገቡትን ቃልም አደንቃለሁ ብለዋል።

የኢትዮጵያ ተወካይ አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ ምን አሉ?

አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ በሰጡት ማብራሪያ፥ በዓለም አቀፍ ህግ ሀገራት መብቶቻቸውን መጠቀም ይችላሉ፤ የኢትዮጵያ መንግስት ለውሳኔውም ምንም አይነት ማብራሪያ እና ማረጋገጫ የማቅረብ ግዴታ የለበትም ብለዋል።

ሀገራት የተለያዩ የተመድ ሰራተኞችን እና የሀገራት ዲፕሎማቶችን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከሀገራቸው ማስወጣታቸውን እናውቃለን፤ ሆኖም ግን ተመድ በእነሱ ላይ ስብሰባ አድርጎ ያውቅ ይሆን? ሲሉ ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት እርምጃውን ስለመውሰዱ ለማንኛውም አካል ማብራሪያ የመስጠት ግዴታ የለበትም ሲሉ ተናግረዋል።

የተመድ ሰራተኞች የገለልተኝነት መርሆችን በጣሰ መልኩ ለህወሓት የሚወግኑ መሆናቸውን ገልፀዋል። 

የተመድ ሰራተኞች ያልሞቱ ሰዎችን በረሃብ ሞተዋል በሚል የሀሰት መረጃዎችን ማሰራጨት፤ የመገናኛ መሣሪያዎችን ለህወሓት ወገን ማድረስ፤ ህወሃት መቀሌ ሲገባ ከቡድኑ ጋር ደስታቸውን መግለጽ፤ ከሳዑዲ የትግራይ ተወላጆችን ወደ ሦሥተኛ ሀገር በማምጣት ለቡድኑ እንዲዋጉ ስልጠና የሚያገኙበትን ሁኔታ ማመቻቸትና ህወሓትን የሚደግፉ ጹሑፎችን ማዘገጀት ላይ ተጠምደው ነበር ብለዋል።

ማን ይገባል፤ ማን ይወጣል ፣ ማን ይቆያል የሚለውን የሀገር መሰረታዊ ሉዐላዊ መብት ነው ብለዋል።

አንቶኒዮ ጉተሬዝ በተጨማሪ ምን አሉ?

ከኢትዮጵያ ጋር የተዋጣ ግንኙነት እንዲኖር ጥረት ሲያደርጉ መቆየታቸውን አሁንም እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።

እንደውም ለኢትዮጵያ መንግስት ታደላለህ በሚል ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ሲወቅሱኝ ቆይተዋል ሲሉ ተናግረዋል።

ለአምባሳደር ታዬ ባቀረቡት ጥያቄም በኢትዮጵያ መንግስት በኩል እስካሁን ድረስ ለተመድ የገባ ደብዳቤ የለም፤ ከተባረሩት 7 የተመድ ሰራተኞች በአንዱም ላይ ቢሆን አንድም ደብዳቤ ካለ ያቅርቡልኝ፤ የማውቀው ነገር የለም ስለሚባለው ክስ ብለዋል።

የተመድ ባለስጣናት እና ሰራተኞቹን ኢትዮጵያ የማባረር መብት የላትም ሲሉ ተናግረዋል በግልፅ ፤ ግለሰቦቹን በማባረር ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ህግ ጥሳለች ብለዋል።

ማንኛውም የተመድ አባል ከስነ ምግባር ውጭ ያደረገው ምንም አድራጎት ካለ እንድናውቅ እንፈልጋለን ብለዋል። 

አጀንዳችን አንድ ብቻ ነው እሱም “የኢትዮጵያ ህዝብ መከራ እንዲያበቃ እንፈልጋለን” ይህ ነው አጀንዳችን ሲሉ ተናግረዋል።

አምባሳደር ታዬ የሰጡት ምላሽ

ንግግሮች መደረግ ያለባቸው በኢትዮጵያ እና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት መካከል እንዲሆን ጠይቀው አፋጠነው ማስረጃውን ለማቅረብ እንደሚሰሩ ገልፀዋል። እንዲሁም ልቦናዎች ከኛ ጋር በመሆኑ እናደንቃለን ብለዋል።

** አንቶኒዮ ጉተሬዝ በምክር ቤት ውስጥ ንግግር ሲያደርጉ ከኢትዮጵያ እንዲወጡ የተደረጉት 8 ሰራተኞች ናቸው ያሉ ሲሆን ውጭ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ላይ ግን 7 እያሉ ነበር ሲጠሩ የነበረው።

የቻይና ተወካይ ምን አሉ?

ተመድ እና የተመድ ሰራተኞች የተቋሙን መርህ ተከትለው ለኢትዮጵያ አስፈላጊውን ድጋፍ ሊያደርሱ ይገባል ብለዋል።

ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን አካላት ለመድረስ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አስፈላጊ የሆኑ ድጋፎችን ቀጣይነት ባለው መልኩ ለኢትዮጵያ መንግስት ሊያቀርቡ እንደሚገባ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት ለችግር ለተጋለጡ ሰዎች ድጋፎችን ለማድረስ ኃላፊነት ወስዶ እየሰራ ላለው ስራ ቻይና እውቅና ትሰጣለች ብለዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት ለሰብአዊ ድጋፍ ቅድሚያ በመስጠት ወደ ሀገር ለሚገቡ ሰራተኞች የቪዛ ሂደቶችን ማቅለሉን፣ የፍተሸ ጣያዎች ቁጥርን መቀነሱን እና የሰብአዊ ድጋፍ ሰራተኞች አስፈላጊውን የተግባቦት መሳሪያ እንዲያስገቡ መፍቀዱንም አስታውሰዋል።

በኢትዮጵያ አሁን ያለውን ችግር ለመቅረፍ እና ድጋፎች እንዲደርሱ ለማድረግ ያለው ብቸኛ አማራጭ ዲፕሎማሲያው መንገድ ብቻ ነውም ብለዋል።

ቻይና አዲስ ለተመሰረተው መንግስት ሙሉ ድጋፍ እንደምታደርግ ገልጻ፤ ዓለም አቀፍ ማህበረሰብም ይህንን እንዲያድርግ ጠይቃለች።

አንዳንድ ሀገራት በኢትዮጵያ እና ኤርትራ ላይ የተናጠል ማዕቀብ ለመጣል ማሰባቸው ዓለም አቀፍ ህግን መጣስ መሆኑን አስታውቃለች። 

በመሆኑም አስመራ እና አዲስ አበባ የተጣሉ ማዕቀብ በአስቸኳይ ሊነሳ ይገባል ብላለች።

የሩሲያ ተወካይ ምን አሉ?

የሩሲያ ተወካይ በተናጠል የሚወሰዱ የማዕቀብ እርምጃዎች ችግሩን እንደሚያባብሱ ገልፀው ተቃውመዋል ።

ሀገራቸው ለኢትዮጵያ ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥል የገለጹ ሲሆን የግጭቱ መፍትሄ ፓን አፍሪካዊ በሆነ መንገድ ይሆን ዘንድ አቋማችን ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ የተከሰተውን ችግር መፍታት የኢትዮጵያ መንግስት መሆኑን ሩሲያ ታምናለች ብለዋል። አለማቀፉ ማህቀረሰብም ይህንኑ ከግምት ሊያስገባው አስፈላጊ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ መንግሰት በሚያደርገው የመፍትሄ ተግባራት ውስጥ የአለማቀፉ ማህበረሰብ ድጋፍ ከጎኑ ሊሆን ይገባዋል። 

ቀውሱን ለማስወገድ ብቸኛው መንገድ የተቀናጀ ትብብር መሆኑን ገልፀዋል።

የአሜሪካ ተወካይ ምን አሉ?

የአሜሪካ ተወካይ (ሊንዳ ቶማስ) የኢትዮጵያ መንግስት 7 የተመድ ሰራኞችን ከሀገር የማስወጣት እርምጃ አሳሳቢ ነው ብለውታል፤ ኢትዮጵያ ይህንን ላደረገችበት ምንያት ምንም አሳማኝ ማስረጃ ማቅረብ አትችልም ብለዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት ውሳኔውን ሊቀለብስ ይገባልም ሲሉ ለምክር ቤቱ ተናግረዋል።

በጦርነቱ ላይ የተካፈሉ ሁሉም አካላት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ አጠቃላይ የሆነ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ እንዲደርሱ ጠይቀዋል።

ይህ የማይሆን ከሆን ግን የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምር ቤት በአፋጣኝ እርምጃ ሊወስድ ይገባል ሲሉም አሳስበዋል።

የአሜሪካ ተወካይ በምክር ቤቱ ካሰሙት ንግግር ባለፈም ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸው በምክር ቤቱ የተናግሩትን ንግግር አጠናክረዋል።

የአሜሪካ ተዋካይ፤ የፀጥታው ምክር ቤት እሳቸው ኃላፊነት የጎደለው/ግዴለሽ ሲሉ የጠሩት የኢትዮጵያን እርምጃ በበጎ አልተቀበለውም ብለዋል። 

ስብሰባው የተባረሩት ሰዎች እንዲመለሱ የሚያሳስብ መልዕክት ያለው ስብሰባ ነበር ሲሉም ተደምጠዋል።

ቃል በቃልም፥ የኢትዮጵያ መንግስት እርምጃ በምክር ቤቱ ላይ በአባል መንግስታት ላይ እንዲሁም በተመድ የሰብዓዊ ጉዳዮች አቅርቦት ላይ የተፈፀመ ድፍረት ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ ኢትዮጵያውያን በራሳቸው ላይ እያደረሱ ያሉት ጉዳት ነው ያሉ ሲሆን ኢትዮጵያውያን ኢትዮጵያውያን ነው እየገደሉ ያሉት፤ ኢትዮጵያውያን ኢትዮጵያውያን እየደፈሩ ያሉት ብለዋል፤ አምባሳደሯ መሪዎችንም ወንጅለው “ህዝቡን ረስተውታል” ሲሉ ገልፀዋል።

ከ3 ዓመት በፊት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ተስፋ ሰጪ ሀገር ትሆናለች ብለን ተስፋ አድርገን ነበር የዛሬ ዓመት አካባቢ ግን ለ2 ሳምንት የተጀመረው የህግ ማስከበር እርምጃ ተራዝሞ አሁን ያለበት ደርሷል በማለት የደረሱትን ጉዳቶችን ዘርዝረው ተናግረዋል።

ተጨማሪ፦

ብሪታኒያ ፣ኢስቶኒያ ፣አየርላንድ ፣ ፈረንሳይ ፣ ኖርዌይ ኢትዮጵያ የተመድ ሰራተኞችን ማባረር አልነበረባትም ብለዋል።

ፈረንሳይ ጠ/ሚ ዐቢይ ሁሉን አካታች ውይይት ለማስጀመር ለወሰዱት ኃላፊነት ድጋፍ አለኝ ብላለች። (ቲክቫህ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: Taye, tplf terrorist, UNSC

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule