• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢህአዴግ ወደ ወታደራዊ አገዛዝ ሊቀየር ይችላል

August 15, 2016 12:16 pm by Editor 2 Comments

በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች እየተካሄደ ያለው የሕዝብ እምቢተኛነት ያሰጋው የኢህአዴግ አገዛዝ በይፋ ወታደራዊ አገዛዝ ለማወጅ ዕቅድ እንዳለው እየተሰማ ነው። ህወሃት ወታደራዊ አገዛዝን ለማወጅ አማራጭ መንገድ የያዘው “አጋር” በሚላቸው ድቃይ ድርጅቶቹ ላይ ያለው እምነት እየተሟጠጠና የቀድሞው ታዛዥነታቸው በመመናመኑ ነው። አገርን ለማዳን በሚል ለአሠራር ያልተመቹትን እያስወገደ ለብቻው ይነግሣል ተብሎ ተነግሯል፡፡

የጎልጉል ዜና አቀባዮች የመረጃ ምንጮቻቸውን ጠቀሰው እንደዘገቡት በኢህአዴግ ስም ህወሃት ራሱ ያደራጃቸው “አቻ ድርጅቶች” አሁን የተነሳበትን የከፋ ተቃውሞ እንደተቀላቀሉበት፣ በነዚሁ ታዛዥ ድርጅቶች አማካይነት የተዘረጋው የጥርነፋና የስለላ ሰንሰለት መፈረካከሱና አባላቱ እንደከዱት ከድምዳሜ ላይ ደርሷል።

በዚህም የተነሳ ሁኔታዎች ከቁጥጥር ከወጡና ህዝባዊ እምቢተኛነቱ ከሁለቱ ክልሎች ማለትም ከኦሮሚያና ከአማራ ክልል ወደ ሌሎች ከተዛመተ ህወሃት “አጋር” የሚባሉትን ድርጅቶች በይፋ ያፈርሳል፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ያውጃል፤ ለይስሙላ ይጠቀምበት የነበረውን ሕገመንግሥት ያግዳል፤ የሰዓት ዕላፊ ይደነገጋል፤ ከወታደራዊ ምክርቤቱ (ደርግ) በሚወጣ ትዕዛዝ ብቻ አገሪቱን ማስተዳደር ይጀምራል፤ ይህንንም በማድረግ የነፍጥ አንጋች /ወታደራዊ/ አገዛዝ በማቋቋም የሽግግር ጊዜ ያውጃል። በዚህ ወቅት የተወሰኑ መለሳለሶችና ውጥረት ማርገቢያ ውሳኔዎችን ሊያስተላልፍና ተግባራዊ ሊያደርግ ይችላል፤ ይህም ህወሃትን እንደ አዲስ በማደራጀት የላዕላይ መዋቅሩን እንደያዘ አሁን ካለው ሁኔታ “የተሻለ” የሚያስብል “ጥገናዊ ለውጥ” ማድረግን ይጨምራል፡፡ እንደ መረጃው ምንጮች ከሆነ ይህ ሃሳብ በወታደራዊና ደኅንነት ዙሪያ በርካታ መዋዕለ ንዋይ ባፈሰሱት የህወሃት ለጋሾችና አንጋሾችም ጭምር ተቀባይነት አለው።

ኦሮሚያና አማራ ክልል ህዝብ የራሱን አስተዳደር በማወጅ የገጠርና አነስተኛ ከተሞችን በድንገት ይቆጣጠራል የሚል ስጋት ያለው ህወሃት፣ ከወዲሁ ወታደራዊ አስተዳደር የሚያቋቁምበትንና ህገ መንግስት አፍርሶ አገር በማዳን ሰበብ ያፈቀደውን ርምጃ ለመውሰድ ለራሱ ፈቃድ ለመስጠት ከውሳኔ ላይ መድረሱን ለማወቅ ተsoldiers melesችሏል። የመረጃው ምንጮች አካሄዱን “ባጭሩ ኢህአዴግ ፈርሶ ህወሃት ብቻውን ይነግሳል” ሲሉ ነው የገለጹት፡፡

ስለጉዳዩ አስተያየት የሰጡ “ይህ አዲስ አይደለም። አሁንም አገሪቱ በወታደራዊ አስተዳደር ነው የምትመራው። ልዩነት ቢኖር አዋጅ የሚያውጁ ከሆነ ብቻ ነው” ይላሉ። አያይዘውም ካሁን በኋላ እንደኩፍኝ ተገልብጦ የወጣውን የህዝብ ቁጣ አሁን ባለው መልኩ ማስቆም የሚቻል እንዳልሆነ ይናገራሉ። በሌላ በኩል ውሳኔው የሰሩት ግፍና የዘረፉት ሃብት፣ የያዙት እቅድና የተለሙት ህልም ድምር ውጤት ከመሆን እንደማያልፍ ጠቁመዋል።

በኦሮሚያ ለወራት የዘለቀው የመስዋዕትነት ተቃውሞ ኦህዴድ ለመክዳቱ ግልጽ ማስረጃ የሰጠ ሆኗል፡፡ በተለይም በመቶዎች የሚቆጠሩ አባላቱ በህወሃት እንዲወገዱ ከተደረጉ በኋላ በክልሉ የዘለቀው የተቃውሞ እንቅስቃሴ ህወሃት ኦሮሚያን በወታደራዊ ዕዝ ሥር እንዲያውል አስገድዶታል፡፡

በይፋ ባይረጋገጥም ሰሞኑን በማኅበራዊ ገጾች የተሰራጨው መረጃ ህወሃት ተመሳሳይ እርምጃ በአማራ ክልል የመውሰድ ሂደት ላይ መሆኑን ጠቁሟል፡፡ በብአዴን ታዛዥነት ለዓመታት በሥራ ላይ ሲውል የነበረው ስለላና ጥርነፋ ከአገልግሎት ውጪ በመሆኑ የአማራን ክልል በወታደራዊ ዕዝ ለመምራት ዕቅድ መነደፉን ይኸው ራሱን “የአማራ ተጋድሎ” በሚል የመረጃ ልውውጥ የሚያደርገው ክፍል በዝርዝር አስታውቋል፡፡

በፌዴራላዊ አወቃቀር የይስሙላ ሥልጣን ለክልሎች እየሠጠ የአገዛዝ ዕድሜውን ያራዘመው ህወሃት አሁን ከገባበት አጣብቂኝ ለመውጣት “አገርን ማዳን” በሚለው ፈሊጥ አዲስ ስሌት መቀመሩ ከተለያዩ አቅጣጫዎች ይሰማል፡፡ በመሆኑም በኦሮሚያ ተግባራዊ ከሆነው ጋር ተዳምሮ በአማራ ክልል ለመተግበር እየተወጠነ ያለው የአስቸኳይ ጊዜ አስተዳደር በዓለምአቀፍ ኅብረተሰብ ዘንድ (የሰብዓዊ መብቶች አስጠባቂ ድርጅቶችና የተባበሩት መንግሥታትን ጨምሮ) በማያስጠይቅ መልኩ ህወሃት አገሪቱን በፈላጭ ቆራጭ ወታደራዊ የበላይነት እንዲገዛ በር የሚከፍት ይሆናል፡፡

“የብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት” በሚል ነገር ግን ጸረ-እኩልነት በሆነ ስልት አናሳው ህወሃት በአገዛዝ የመቀጠሉ ጉዳይ አሳሳቢ ስለሆነበት ኦህዴድ ላይ እንደዘመተው ሰሞኑን ብአዴን ላይም እያመረረ ይገኛል፡፡ ከዚህ አንጻር የህወሃት ልሣን በሆነው አይጋ ፎረም ላይ ብአዴን መብጠልጠሉ የመጨረሻውን መጀመሪያ እንደሚያመላክት ሃሳብ እየተሰጠበት ይገኛል፡፡ Exhibits of the Hijack of ANDM by Rotten Neftegnas በሚል ርዕስ የወጣው ጽሁፍ ላይ ስለብአዴን እንዲህ ተብሏል፤ (የአማርኛውን ትርጉም ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)

“ብአዴን የራሱ ነፍስ የሌለው ደርግን ለመጣልም በተደረገው ትግልም ብአዴኖቹ ከሞነጫጨሯቸው ጥቂት ግጥሞችና የፍቅር ደብዳቤዎች ውጭ ምንም ሚና የተጫወቱት ነገር አለመኖሩም ገሃድ የወጣ እውነት ነው። እንደውም ብአዴን የህወሃትን ገድል የሚያሳይ ቪዲዮ ሰርቆ ፫፭ኛ ዓመት በዓሉን ሲያከብር በአማራ ቴሌቪዥን ላይ ምንም አይነት ለውጥ ሳያደርግ የራሱ ገድል አስመስሎ አሳይቷል። ብአዴን ይህንን ያደረገው በጦርነቱ ወቅት በባልተቤትነት ይዞት የነበረ አንድ ነጠላ የቪዲዮ ክር እንኳን ስለመኖሩ የሚታውቅ ነገር በሌለበት ሁኔታ ውስጥ ነው።

“በዚሁ የሰላሳ አምስተኛ አመቱ ክብረ በዓል ላይ ከሃቁ ባፈነገጠ መልኩ ተጣመውና ተጋነው ከቀረቡትጭብጦች መካከል ብአዴን ያለማንም እርዳታ በራሱ ግዜ እራሱን ችሎ የተፈጠረ አስመስሎ ለመዘከር የሄደበት ደረጃ ነው። ይህ ማለት ባጭሩ ብአዴንን ህወሃት የፈጠረው አይደለም ለማለት ተፈልጎ ነው።”

ይህ “ፈጣሪህ ነበርኩ፤ አሁን ደግሞ እንዳትኖር አደርግሃለሁ” የሚለው የህወሃት አስተሳሰብ ግልጽ በሆነ መልኩ በህወሃትና በብአዴን መካከል የተከሰተውን ፍቺ የሚያሳይ ሆኗል፡፡ ህወሃት በዚህ መልኩ “ኢህአዴግ” በሚል ማታለያ ከሰበሰባቸው ድርጅቶች ጋር ፍቺ እየፈጸመ ሄዶ ኢህአዴግን ወደ ወታደራዊ አገዛዝ በመቀየር “ንግሥናውን” ለብቻው ይቆጣጠረዋል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. አለም says

    August 15, 2016 07:14 pm at 7:14 pm

    ጎልጉል፤ [እባካችሁ አስተያየቴን አታንሱ። እንኳን እናንተ የህወሓት ገጾች ወቀሳዬን ለጥፈዋል፡)]
    ጻድቃን በህወሓት ብሎግ ሆርን አፌርስ ስለ ለጠፈው ጽሑፍ ትንሽ ልበል። ሁለቴ በጥንቃቄ አንብቤለታለሁ። በዝብዝቡ መንገላታት አያሻንም። በግልጽ ያስቀመጣቸውን እንመልከት። 1/ ስለ ኢትዮጵያ ሁኔታ ከጓደኞቼ ጋር ተመካክረን ነበር ብሎናል፣ ጓደኞቹ እነማን እንደሆኑ ግልጽ ነው 2/ ስለኢትዮጵያ የነገረን የማናውቀውን አይደለም፤ ህወሓትን አሳጥቶ መጻፉ ለአንዳንዶች አስገራሚ መስሎ ይታይ ይሆናል። ጉዳዩ ግን፣ ህወሓት በራሱ ሊለው የማይችለውን ተመካክረው እያለላቸው ነው 3/ ምርጫ ይኑር፣ የምርጫ ውጤት ለመቀበል ፈቃደኛ መሆን አለብን ብሎአል 4/ የርሱ ሃብት ማካበት በራሱ ጥረት እንደሆነ ሊያሳምነን ሞክሯል 5/ ስዬን ጠቅሷል 6/ የኢትዮጵያን ሠራዊት በትኖ የህወሓትን መተካቱን በወቅቱ “National defense and economic development”ብሎ ያቀረበውን ሰነድ ቆንጽሎ ሙሉውን ሰነድ ሊደብቀን ሞክሯል 7/ ዛቻ ብጤም አሰምቷል፤ ካለዚያ ደም በደም እንሆናለን ብሎ። ድምዳሜዬ? 1/ የህወሓት አካሄድ እንደማያዋጣ ተረድቷል፤ ስዬ እንደሞከረው [ትዝ ይልሃል? አንዴ እስር ቤቱ ኦሮምኛ ይናገራል ያላትን?] 2/ ደቡብ ሱዳን ላይ ለአሜሪካኖች ዓላማ አስተባባሪ ሆኖ እየሠራ ነው፤ ስዬ ምዕራብ አፍሪካ ላይ። 3/ ህወሓት ከመለስ ሞት በኋላ መስማማት ስላልቻሉ ኃ/ማርያምን አስቀምጠው ካብ ለካብ እየተያዩ ነው፤ “ኮሌክቲቭ ሊደርሽፕ” በሚል ማጭበርበሪያ ኃ/ማርያምን ደብረጽዮን፣ በረከት፣ አባይ፣ ብርሃነ ገ/ክ ገንዘቡን ሥልጣኑን ተቀራምተውታል፤ አንዱ ችግር ይኸው ነው። አሜሪካኖች የችግሩን መጠን ያውቁታል፤ አታላይነቱ ስለገባቸው የመለስ መወገድ እረፍት ሆኗቸው ነበር፣ አሁን ደግሞ የዋለለ ጉዳይ እንዲቀጥል አይፈልጉም። ህወሓት ሶማሌን፣ ደቡብ ሱዳንን በኢትዮጵያውያን ደም እየነገደ አመቻችቶላቸዋል። ይህን ነገር መፍትሔ ስጡ እያላቸው ነው። የወገኖቻችን ደም መፍሰስ ምንም ያልመሰለው ለዚህ ነው። በተባበሩት መንግሥታት ጸጥታ ጉዳይ ኢትዮጵያ ወንበር ያገኘችው በአሜሪካና በእንግሊዝ እርዳታ ነው። አሁን የሚፈለገው ጻድቃን [ወይም ስዬ] እንደ ታዳጊ ቀርቦ የአሜሪካኖችን ዓላማ ያስፈጽማል፤ በዚያውም የህወሓትን የበላይነት ይታደጋል ማለት ነው። ፕሮፌሰር መሳይ ይህን እንዴት እንዳልተረዳው ገርሞኛል። በናይጄሪያ ያደረጉት ይህንኑ ነው፤ ጆናታን ጉድለክ በጄኔራል ሙሐመዱ ቡሃሪ የተተካው በአሜሪካኖች እርዳታ ቦኮሃራምን ለመዋጋር በሚል ነው። ብዙ ሌላ ሐተታ በማቅረብ እንዳላሰለች ጉዳዩን ለማስረዳት የቀረበው በቂ ይመስለኛል። [በነገራችን ላይ የህወሓት ብሎግ ሆርን አፌርስ በእንግሊዝኛ የተረጎሙት ለህወሓት አመቻችተው ነው፤ ጊዜ ካገኛችሁ ትርጉሙን ከአማርኛው ቅጂ ጋር አስተያዩ። አሁንማ የጻድቅቃንን ኢንተርቪው እያሰሙን ነው። ፐብሊክ ሪሌሽንስ ነው ነገሩ፤ ለምርጫ ውድድሩ ፓርቲ ሳይኖር ተጀምሯል!]። ሌላ የሚያሣስበው የነዶ/ር ብርሃኑ መወላገድ ነው፤ ከጻድቃን ባላነሰ ለአገራችን መቅሠፍት ናቸው የሚል ግንዛቤ ላይ ደርሻለሁ። ብትፈቅዱ ይህን አስተያየቴን አትሙልኝ። እኔም ለአገሬ ማሰቤ ነውና፣ ሌሎች ይስሙትና የሚመስላቸውን ግንዛቤ ይውሰዱ። አመሰግናለሁ።

    Reply
  2. Naji says

    August 21, 2016 09:28 pm at 9:28 pm

    Is anybody surprised? As a matter of fact, I am not. The ruling party has to do anything that helps it survive. When things get tougher, one is in a precarious situation feels hopeless anything that gives a twenty-four hours time can be an option. This is obvious, no one should be surprised.
    The Ethiopian youth is determined and strongly fighting against a menacing, yet an establishment that has huge force at its disposal and service.
    I believe no amount of force will win the determination of the people. To minimize the duration and cost, every effort needs to be coordinated and channeled in an overpowering manner.
    The ruling party is weaker than it was a year ago. Those who claim to love their country and fight, need to have a strategy to isolate TPLf from it base support.
    We heard that TPLF evcuated Tegray origins from towns and cities. Given the long history of togetheness, and metual respect of Ethiopian people to one another, what does this reaction tells us? Do those evacuated individuals really see danger and voletired?
    The ruling party miserably fail to win the hearts and minds of the Ethiopian people. Its support is complitely gone.
    The only way out the ruling party sees is to fool the Tegray people once again. The last one was sychological and rhitoric.This time it has show evidence and display. The main intetion of the ruling part is to scare away the Tegray citizens from joining the Ethiopian popular struggle.That is the evacuation all about.
    soon or later the evacuatees and Tegray people will know what has been done behind the back.
    Tyranny has no compassion and respect to anything, except itself and its bottomless appitiet. Everybody else is either an instrument or a tool. We have seen a lot.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule