• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“አልሲሲ የፈጣሪ ጠላት ነው፤ አገራችንን ለቅቀህ ውጣ” የተቃውሞ ሰልፈኞች

September 29, 2020 01:21 am by Editor Leave a Comment

በግብጹ ፕሬዘዳንት አልሲሲ ላይ የተነሳው ቁጣ በመላው ግብፅ ተቀጣጥሏል፤ የአልሲሲን አገዛዝ ተቃውመው የሚደረጉ ሰልፎች በመላው ግብፅ መደረጋቸውን ቀጥለዋል።

የግብፅ ፕሬዝዳንት አብደል ፈታህ አልሲሲ በግብፅ አለመረጋጋትና ትርምስ ለመፍጠር ጥረት የሚያደርጉ ሁሉ ከድርጊታቸው ቢታቀቡ ይሻላቸዋል ሲሉ ማስጠንቀቃቸውን አልጀዚራ ዘግቧል። ተቃዋሚዎች አልሲሲ ስልጣን እንዲለቁ ይፈልጋሉ፤ እንደ ዋና ምክያት የሚያነሱት ደግሞ ሙሰኝነታቸውን ነው።

ሲሲ ለአመታት ከጦር ኃይሉ ጋር በመሆን ለፕሬዝዳንቱ ቤተሰብ እና ጓደኞች ይሆኑ ዘንድ ከተገነቡ ቅንጡ ቤቶችና ከሌሎች በርካታ የግንባታ ፕሮጀክቶች ጋር በተያያዘ የሙስና ወንጀል ፈፅመዋል እያሉ ነው።

ተቃውሞው ቁጣቸው እየጨመረ በሚመጣ አመፀኞች ተቀጣጥሏል። በተለይ በገጠርና ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው አካባቢዎች በርትቷል። ህገ ወጥ ግንባታዎች ይቁሙ የመሰሉ መፈክሮች እየተሰሙ ነው።

እየወጡ እንዳሉ ዘገባዎች በመላው ግብፅ 40 መንደሮች ላይ የተቀሰቀሰው አመፅ የፖሊስ የኃይል እርምጃ ሊገታው አልቻለም። ኤል ሲሲ ለአመፅ የተጠሩትን ጥሪዎች ግብፃውያን ባለመስማታችሁ አመሰግናለሁ ብለዋል።

በህዝቡ እየተነሱ ያሉ ጥያቄዎችን የሪፎርሙ አካል አድርጎ መንግስት እንደሚተገብራቸውም ገልፀዋል።በስደት ላይ በሚገኘው በግብፃዊው የንግድ ሰው ሞሀመድ አሊ በተደረገው ጥሪ ተቃዋሚዎች በአልሲሲ መንግስት ላይ በማመፅ ጎዳናዎችን እንደ አውሮፓውያኑ ከ መስከረም 20 ጀምሮ እያጥለቀለቁ ነው።

ፖሊስ አመፆቹን ለመበተን አስለቃሽ ጭሶችን ተጠቅሟል። እንደ ሚድል ኢስት ሞኒተር ዘገባ የግብፅ የፀጥታ ሀይሎች 400 ሰዎችን ሲያስሩ 3 ሰዎች ደግሞ ተገድሏል።

አመጹ ከተጀመረ ጀምሮ የተያዙ እድሜያቸው ያልደረሰ 60 ህፃናትም ከእስር እንዲፈቱ እየተጠየቀ ነው።ህፃናቱ ከ 10 እስከ 15 ዕድሜ ሲሆኑ ሁሉም አመፁ በብዛት ከሚደረግበት ላይኛው ግብፅ ናቸው።

አብዛኞቹ አመፆች በመንደሮችና በገጠራማ አካባቢዎች እየተደረጉ ያሉት ካይሮንና አሌክሳንድርያን በመሰሉ ከተሞች የፀጥታ ሀይሉ ጥብቅ ጥበቃ እያደረገ ስለሆነ ነው።

ባለፈው አመት መስከረም መጨረሻ ላይ ስደት ላይ ያለው ሞሀመድ አሊ ስፋት ያለው አመፅ በጠራ ወቅት በሺዎች የሚቆጠሩ ግብፃውያን በተለያዩ ትላልቅ የግብፅ ከተማ ጎዳናዎች በመውጣት የሲሲ መንግስት ስልጣኑን እንዲለቅ ጠይቀው ነበር።

በስፔን በስደት ላይ የሚገኘው ሞሀመድ አሊ፤ ሲሲ በአሁኑም አመት በአገዛዙ ላይ ግብፃውያን እንዲያምፁ ጥሪ በማድረጉ ግብፅ በአመፅ ታምሳለች። በጥሪው ሰልፈኞች በተለያዩ ግዛቶች በመውጣት ያለፉትን አመታት አመፆችንም አስታውሰዋል።

አል ሲሲ በሐምሌ 2013 ነበር በወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት የሀገሪቱን የመጀመርያ በዲሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጡትን ሞሀመድ ሙርሲን አስወግደው ስልጣን ላይ የወጡት። (በሔኖክ አስራት፤ Ethio Fm 107.8)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: Egypt, el-sis

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule