• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“አልሲሲ የፈጣሪ ጠላት ነው፤ አገራችንን ለቅቀህ ውጣ” የተቃውሞ ሰልፈኞች

September 29, 2020 01:21 am by Editor Leave a Comment

በግብጹ ፕሬዘዳንት አልሲሲ ላይ የተነሳው ቁጣ በመላው ግብፅ ተቀጣጥሏል፤ የአልሲሲን አገዛዝ ተቃውመው የሚደረጉ ሰልፎች በመላው ግብፅ መደረጋቸውን ቀጥለዋል።

የግብፅ ፕሬዝዳንት አብደል ፈታህ አልሲሲ በግብፅ አለመረጋጋትና ትርምስ ለመፍጠር ጥረት የሚያደርጉ ሁሉ ከድርጊታቸው ቢታቀቡ ይሻላቸዋል ሲሉ ማስጠንቀቃቸውን አልጀዚራ ዘግቧል። ተቃዋሚዎች አልሲሲ ስልጣን እንዲለቁ ይፈልጋሉ፤ እንደ ዋና ምክያት የሚያነሱት ደግሞ ሙሰኝነታቸውን ነው።

ሲሲ ለአመታት ከጦር ኃይሉ ጋር በመሆን ለፕሬዝዳንቱ ቤተሰብ እና ጓደኞች ይሆኑ ዘንድ ከተገነቡ ቅንጡ ቤቶችና ከሌሎች በርካታ የግንባታ ፕሮጀክቶች ጋር በተያያዘ የሙስና ወንጀል ፈፅመዋል እያሉ ነው።

ተቃውሞው ቁጣቸው እየጨመረ በሚመጣ አመፀኞች ተቀጣጥሏል። በተለይ በገጠርና ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው አካባቢዎች በርትቷል። ህገ ወጥ ግንባታዎች ይቁሙ የመሰሉ መፈክሮች እየተሰሙ ነው።

እየወጡ እንዳሉ ዘገባዎች በመላው ግብፅ 40 መንደሮች ላይ የተቀሰቀሰው አመፅ የፖሊስ የኃይል እርምጃ ሊገታው አልቻለም። ኤል ሲሲ ለአመፅ የተጠሩትን ጥሪዎች ግብፃውያን ባለመስማታችሁ አመሰግናለሁ ብለዋል።

በህዝቡ እየተነሱ ያሉ ጥያቄዎችን የሪፎርሙ አካል አድርጎ መንግስት እንደሚተገብራቸውም ገልፀዋል።በስደት ላይ በሚገኘው በግብፃዊው የንግድ ሰው ሞሀመድ አሊ በተደረገው ጥሪ ተቃዋሚዎች በአልሲሲ መንግስት ላይ በማመፅ ጎዳናዎችን እንደ አውሮፓውያኑ ከ መስከረም 20 ጀምሮ እያጥለቀለቁ ነው።

ፖሊስ አመፆቹን ለመበተን አስለቃሽ ጭሶችን ተጠቅሟል። እንደ ሚድል ኢስት ሞኒተር ዘገባ የግብፅ የፀጥታ ሀይሎች 400 ሰዎችን ሲያስሩ 3 ሰዎች ደግሞ ተገድሏል።

አመጹ ከተጀመረ ጀምሮ የተያዙ እድሜያቸው ያልደረሰ 60 ህፃናትም ከእስር እንዲፈቱ እየተጠየቀ ነው።ህፃናቱ ከ 10 እስከ 15 ዕድሜ ሲሆኑ ሁሉም አመፁ በብዛት ከሚደረግበት ላይኛው ግብፅ ናቸው።

አብዛኞቹ አመፆች በመንደሮችና በገጠራማ አካባቢዎች እየተደረጉ ያሉት ካይሮንና አሌክሳንድርያን በመሰሉ ከተሞች የፀጥታ ሀይሉ ጥብቅ ጥበቃ እያደረገ ስለሆነ ነው።

ባለፈው አመት መስከረም መጨረሻ ላይ ስደት ላይ ያለው ሞሀመድ አሊ ስፋት ያለው አመፅ በጠራ ወቅት በሺዎች የሚቆጠሩ ግብፃውያን በተለያዩ ትላልቅ የግብፅ ከተማ ጎዳናዎች በመውጣት የሲሲ መንግስት ስልጣኑን እንዲለቅ ጠይቀው ነበር።

በስፔን በስደት ላይ የሚገኘው ሞሀመድ አሊ፤ ሲሲ በአሁኑም አመት በአገዛዙ ላይ ግብፃውያን እንዲያምፁ ጥሪ በማድረጉ ግብፅ በአመፅ ታምሳለች። በጥሪው ሰልፈኞች በተለያዩ ግዛቶች በመውጣት ያለፉትን አመታት አመፆችንም አስታውሰዋል።

አል ሲሲ በሐምሌ 2013 ነበር በወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት የሀገሪቱን የመጀመርያ በዲሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጡትን ሞሀመድ ሙርሲን አስወግደው ስልጣን ላይ የወጡት። (በሔኖክ አስራት፤ Ethio Fm 107.8)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: Egypt, el-sis

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule