• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የታሪክ እርማት በየገፁ

October 16, 2017 06:38 am by Editor Leave a Comment

በቅርቡ “የትምህርት ሚኒስቴር” 400 ተማሪዎች በፈተና ቅጾች ላይ ኢትዮጵያውያን አይደለንም ብለው ሞሉ የሚል መረጃ አወጣ ሲባል ሰምቼ ቆሽቴ አርሮ ነበር። የተናደድኩበት ምክንያት የመንግስት የ26 አመት የጸረ-ኢትዮጵያዊነት ፖሊሲ አፈጻጸም ይህን የመሰለ ውጤት እንዴት ሊያመጣ ቻለ በሚል ሳይሆን እንዴት ዛሬ ስርአቱ በሞት አፋፍ ላይ ቆሞ እንኳን የሩብ አመት ድካሙ ከንቱ መሆኑን አይገባውም ብዬ ነበር። እንጂ ኢትዮጵያን የማትመስል ኢትዮጵያን ለመፍጠር ሌት ተቀን ያለመታከት ሲዘራ የኖረው የጎሳ መርዝ 400 የተበላሹ እጽዋትን አበቀለ ቢሉኝ እንኳን ጉዳታችን ከዚህ በላይ አልሆነ ብዬ በእፎይታ እተነፍስ ይሆናል እንጂ ብዙም አላዝንም። መንግስት ግን ላመታት ስራው ከንቱነት ዋቢ የሆነውን መረጃ ዛሬም ሳያፍር  እንደመልካም ዜና ማወጁ ያስገረመኝ መሆኑን ግን መሸሸግ አልችልም።

የዛሬ ርእሴ ግን ይህ አይደለም። የጎሳ ፖለቲካ ቀባሪ አጥቶ እንጂ በህዝብ ህሊና ውስጥ ከሞተ ቆይቷል። አሁን የኢሀዲግ ኢትዮጵያ ቅዠት ሆና የህዝቡ ኢትዮጵያ እውን ልትሆን የተስፋ ቾራ ብቅ ማለት ጀምሯል። ህዝብ ላመታት በጎሰኝነት ፖለቲካ ስትጎሳቆል የኖረቺውን አንዲት ኢትዮጵያ ሊያድስ ሲታጠቅ እየታየ ነው። የሰሞኑ የባለራእይ የዖሮሞ ወጣቶች አስገራሚና አስደማሚ የሰሜንኢትዮጵያ ጉብኝት የዚህ የሀገር መልሶ ግንባታ ጥረት ግሩም ጥንስስ ነው። ኢትዮጵያን ለማፍረስ የታቹት የኢትዮጵያ ዖሮሞ ወጣቶች ኢትዮጵያን ዳግም ለመገንባት አስደናቂ ታሪክ ሰሩ። በጣና አረም ተምሳሌነት የኢትዮጵያን የተበላሸ ታሪክ አረሙት። የደበዘዘውን የህዝብ አንድነት እንደገና በፍቅር አደመቁት። “ኢትዮጵያ ኬኛ” ሲሉ።  የአንድነት ታሪክን ስርዝ ድልዝ በብሩህ የወጣት አእምሯቸው በቀረጹት አዲስ የፍቅር ብእር አድምቀው ጻፉና በሁላችንም ልብ ነገሱ።

ይህ ያልተጠበቀና ኢምንት የሚመስል ግን ደግሞ የኢትዮጵያን የታሪክ አቅጣጫ ከመሰረቱ የሚለውጥ ድንቅ እርምጃ አድማሱ መስፋት ይኖርበታል። በዚህ የፍቅር መርከብ ሁሉም መሳፈር ይኖርበታል። የአማራና ዖሮሞ ህዝብ አንድነት ለኢትዮጵያ አንድነት ያለው ፋይዳ ግዙፍ ነው። ሆኖም ኢትዮጵያ ከዚህም በላይ ናት። የትግራይ፣ የደቡብ፣ የቤኒሻንጉል፣  የጋምቤላና የሶማሌ ህዝብ ከኢትዮጵያ ሌላ እናት የለውም። እናም የዖሮሞ ወጣቶች ያሳዩን የፍቅር አበባ በሁሉም አቅጣጫ ሲበተን ማየት እንሻለን። በተለይ የትግራይ ህዝብ የሚነቃበት ጊዜ አሁን መሆን አለበት። በእኔ እምነት የትግራይ ህዝብ ወንድምና እህቶቹን የሚጠላ ህዝብ አይደለም። እንዲያውም የፍቅር ህዝብ ነው። ባልጠበቀው መንገድ የቅሬታ አጣብቂኝ ውስጥ እንዲገባ ተደረገ እንጂ ህዝቡ በባህሪው ፀረአንድነት አይደለም። ስለዚህ ያለፍላጎቱ የተፈጠረበትን የአንድነት ክፍተት የሚሞላበትን ስልት ለመፈለግ ከዚህ በላይ አጋጣሚ ሊኖር አይችልም። የኢትዮጵያ የፍቅር ልብ ለሁሉም ክፍት ነው። አማራና ዖሮሞ ዜጎች የከፈቱት የፍቅር አዳራሽ ለማንም አይጠብም። ኢትዮጵያውያን አስተዋይ የዖሮሞ ወጣቶች ባቀጣጠሉት የፍቅር ሻማ መብራት እየተመሩ የደበዘዘ ያንድነት ታሪካቸውን ዳግመኛ ሊያደምቁት ይገባል። የዖሮሞ ወጣቶች የጀመሩት የታሪክ እርማት ስርዝ ድልዝ ባለበት ገፅ ሁሉ ሊቀጥል ይገባል። እናንት አስተዋይ የኢትዮጵያ ወጣቶች፣ ባስተዋይ ምግባራችሁ ሁላችንም ኮርተናል፤ ኢትዮጵያም ለዘላለም ትኮራባችhኋለች።

ህሩይ ደምሴ (zobar2006@gmail.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule