• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሴት ልጅ በሽፍታ እጅ ወድቃ የሚተኛ ጎን የለኝም

January 28, 2020 05:45 am by Editor Leave a Comment

ከሃምሳ ቀናት በላይ በአጋቾች እጅ ያሉት እህቶቻችን ጉዳይ እጅግ አሳሳቢ ሆኖብናል። የአንድ ሃገር ህዝብ ከሁሉ በፊት የሚፈልገው ነገር ዋስትና ነው። ተማሪው፣ ነጋዴው፣ ገበሬው፣ ሰራተኛው ሁሉ ከመንግስት የሚጠብቀው ዋና ነገር ደህንነቱ እንዲረጋገጥለት ነው። የመንግስት ተቀዳሚ ተግባርም ይሄ ነው።

ለውጥ በሃገራችን ጀመረ ካልንበት ማግስት ጀምሮ ከፍተኛ መፈናቀልና አለመረጋጋት ሃገራችንን እየናጣት ነው። ይህንን ችግር የለውጥ ባህርይ ኣድርገን የምናይ ካለን ስህተት ነው። የሰው ደም ሳንገብር ወደ ለውጥ የምናልፍበትን መንገድ ነው የምንሻው እንጂ ከዚህ በፊት በየለውጡ ያየነውን ኣይነት የኢትዮጵያውያን ስቃይ እንዲደገም አንሻም። በመሆኑም የለውጥ መሪዎች ቁጥር አንድ ስራ የህዝቡን ሰላምና ደህንነት ማስጠበቅ መሆን ኣለበት።

ከሃምሳ ቀናት በላይ በእገታ ላይ የሚገኙት የሃገር ተስፋ የሆኑ እህቶቼና ወንድሞቼ ህይወት በአንድም በሌላም መልኩ ከመንግስት የጸጥታ አመራር ጋር በቀጥታ የተገናኘ ችግር ነው። ስለሆነም መንግስት ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ እነዚህን ወጣቶች የማዳን ስራ መስራት አለበት። ወታደራዊ ጥበቦችና የአመራር ጥበቦች ሁሉ ወደነዚህ ወገኖች ሊያዘነብሉ ይገባል። እኔ እንደገባኝ አጋቹ ታውቋል። ምክንያቱም የጠቅላይ ሚንስትሩ ጽህፈት ቤት ሰክሬታሪያት አቶ ንጉሱ ጥላሁን ሲናገሩ እንደሰማሁት የተለቀቁ ተማሪዎች እንዳሉና ለቀሩት ድርድር እየተደረገ እንደሆነ ገልጸዋል። ይህ ማለት መንግስት ኣጋቹን ኣውቋል ማለት ነው። ስለዚህ እነዚህ እህቶቻችንና ወንድሞቻችንን የማትረፍ ኦፐሬሽን መደረግ ኣለበት። ይህ ኦፐሬሽን በከፍተኛ የሰኪዩሪቲና ወታደራዊ ጥበብ የታገዘ መሆንም አለበት። መረጃዎች ለህብረተሰቡ መገለጽ አለበት።

በተለይ ደግሞ ሴት ልጅ በሽፍታ እጅ ወድቃ የሚተኛ ማህበረሰብ የለንም። ሴት በሽፍታ እጅ ወድቃ እንቅልፍ ኣይኖረንም። የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችም ሆናችሁ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በተቀናጀ ትግል እነዚህን ሴቶች መታደግ ያስፈልጋል። ይህንን በማድረግ በሃገራችን ቀድሞ የማናውቀውን ይህንን የማገት ጅማሮ ከስሩ መንቀል ኣለብን። ኢትዮጵያችን የቦኮሃራም ዋሻ ልትሆን በምንም ዓይነት ኣንፈቅድም። በመላ ሃገሪቱ የምትገኙ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የብሄር ልዩነትን ጌጥ አድርጋ ሁ ኢትዮጵያ ውስጥ ቦኮሃራም ቦታ የለህም ማለት አለባችሁ። ለአጠቃላይ የሃገራችን የደህንነት ዋስትና ቆርጣችሁ መነሳት አለባችሁ። የትም ዓለም ቢሆን ዴሞክራሲና መልካም ኣስተዳደር የመጣው በትግል ነው። መንግስት በገፋነው ልክ የሚሄድ ነገር ነውና ለውጡ በሰዎች መጉላላትና ደም ላይ ሳይሆን በሰላምና በአንድነት እንዲቀጥል ንቅናቄዎች ያስፈልጋሉ።

ሴት ልጁ የተነካበት ማህበረሰብ ቀፎው እንደተነካበት ንብ ብድግ ብሎ ሊነሳ ይገባል። ለውጥን የሚመራው ህዝብ ነውና በየጊዜው ለውጡን የሚያስቱ ሁኔታዎች ሲፈጠሩ ህዝቡ አቅጣጫ የማሳየትና የመታገል ሃላፊነቱን በንቃት ሊወጣ ይገባል።

እግዚአብሄር ኢትዮጵያን ይባርክ!

ገለታው ዘለቀ (geletawzeleke@gmail.com)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions, Social Tagged With: bring back our sisters, Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule