• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሴት ልጅ በሽፍታ እጅ ወድቃ የሚተኛ ጎን የለኝም

January 28, 2020 05:45 am by Editor Leave a Comment

ከሃምሳ ቀናት በላይ በአጋቾች እጅ ያሉት እህቶቻችን ጉዳይ እጅግ አሳሳቢ ሆኖብናል። የአንድ ሃገር ህዝብ ከሁሉ በፊት የሚፈልገው ነገር ዋስትና ነው። ተማሪው፣ ነጋዴው፣ ገበሬው፣ ሰራተኛው ሁሉ ከመንግስት የሚጠብቀው ዋና ነገር ደህንነቱ እንዲረጋገጥለት ነው። የመንግስት ተቀዳሚ ተግባርም ይሄ ነው።

ለውጥ በሃገራችን ጀመረ ካልንበት ማግስት ጀምሮ ከፍተኛ መፈናቀልና አለመረጋጋት ሃገራችንን እየናጣት ነው። ይህንን ችግር የለውጥ ባህርይ ኣድርገን የምናይ ካለን ስህተት ነው። የሰው ደም ሳንገብር ወደ ለውጥ የምናልፍበትን መንገድ ነው የምንሻው እንጂ ከዚህ በፊት በየለውጡ ያየነውን ኣይነት የኢትዮጵያውያን ስቃይ እንዲደገም አንሻም። በመሆኑም የለውጥ መሪዎች ቁጥር አንድ ስራ የህዝቡን ሰላምና ደህንነት ማስጠበቅ መሆን ኣለበት።

ከሃምሳ ቀናት በላይ በእገታ ላይ የሚገኙት የሃገር ተስፋ የሆኑ እህቶቼና ወንድሞቼ ህይወት በአንድም በሌላም መልኩ ከመንግስት የጸጥታ አመራር ጋር በቀጥታ የተገናኘ ችግር ነው። ስለሆነም መንግስት ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ እነዚህን ወጣቶች የማዳን ስራ መስራት አለበት። ወታደራዊ ጥበቦችና የአመራር ጥበቦች ሁሉ ወደነዚህ ወገኖች ሊያዘነብሉ ይገባል። እኔ እንደገባኝ አጋቹ ታውቋል። ምክንያቱም የጠቅላይ ሚንስትሩ ጽህፈት ቤት ሰክሬታሪያት አቶ ንጉሱ ጥላሁን ሲናገሩ እንደሰማሁት የተለቀቁ ተማሪዎች እንዳሉና ለቀሩት ድርድር እየተደረገ እንደሆነ ገልጸዋል። ይህ ማለት መንግስት ኣጋቹን ኣውቋል ማለት ነው። ስለዚህ እነዚህ እህቶቻችንና ወንድሞቻችንን የማትረፍ ኦፐሬሽን መደረግ ኣለበት። ይህ ኦፐሬሽን በከፍተኛ የሰኪዩሪቲና ወታደራዊ ጥበብ የታገዘ መሆንም አለበት። መረጃዎች ለህብረተሰቡ መገለጽ አለበት።

በተለይ ደግሞ ሴት ልጅ በሽፍታ እጅ ወድቃ የሚተኛ ማህበረሰብ የለንም። ሴት በሽፍታ እጅ ወድቃ እንቅልፍ ኣይኖረንም። የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችም ሆናችሁ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በተቀናጀ ትግል እነዚህን ሴቶች መታደግ ያስፈልጋል። ይህንን በማድረግ በሃገራችን ቀድሞ የማናውቀውን ይህንን የማገት ጅማሮ ከስሩ መንቀል ኣለብን። ኢትዮጵያችን የቦኮሃራም ዋሻ ልትሆን በምንም ዓይነት ኣንፈቅድም። በመላ ሃገሪቱ የምትገኙ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የብሄር ልዩነትን ጌጥ አድርጋ ሁ ኢትዮጵያ ውስጥ ቦኮሃራም ቦታ የለህም ማለት አለባችሁ። ለአጠቃላይ የሃገራችን የደህንነት ዋስትና ቆርጣችሁ መነሳት አለባችሁ። የትም ዓለም ቢሆን ዴሞክራሲና መልካም ኣስተዳደር የመጣው በትግል ነው። መንግስት በገፋነው ልክ የሚሄድ ነገር ነውና ለውጡ በሰዎች መጉላላትና ደም ላይ ሳይሆን በሰላምና በአንድነት እንዲቀጥል ንቅናቄዎች ያስፈልጋሉ።

ሴት ልጁ የተነካበት ማህበረሰብ ቀፎው እንደተነካበት ንብ ብድግ ብሎ ሊነሳ ይገባል። ለውጥን የሚመራው ህዝብ ነውና በየጊዜው ለውጡን የሚያስቱ ሁኔታዎች ሲፈጠሩ ህዝቡ አቅጣጫ የማሳየትና የመታገል ሃላፊነቱን በንቃት ሊወጣ ይገባል።

እግዚአብሄር ኢትዮጵያን ይባርክ!

ገለታው ዘለቀ (geletawzeleke@gmail.com)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Social Tagged With: bring back our sisters, Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule