• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሴት ልጅ በሽፍታ እጅ ወድቃ የሚተኛ ጎን የለኝም

January 28, 2020 05:45 am by Editor Leave a Comment

ከሃምሳ ቀናት በላይ በአጋቾች እጅ ያሉት እህቶቻችን ጉዳይ እጅግ አሳሳቢ ሆኖብናል። የአንድ ሃገር ህዝብ ከሁሉ በፊት የሚፈልገው ነገር ዋስትና ነው። ተማሪው፣ ነጋዴው፣ ገበሬው፣ ሰራተኛው ሁሉ ከመንግስት የሚጠብቀው ዋና ነገር ደህንነቱ እንዲረጋገጥለት ነው። የመንግስት ተቀዳሚ ተግባርም ይሄ ነው።

ለውጥ በሃገራችን ጀመረ ካልንበት ማግስት ጀምሮ ከፍተኛ መፈናቀልና አለመረጋጋት ሃገራችንን እየናጣት ነው። ይህንን ችግር የለውጥ ባህርይ ኣድርገን የምናይ ካለን ስህተት ነው። የሰው ደም ሳንገብር ወደ ለውጥ የምናልፍበትን መንገድ ነው የምንሻው እንጂ ከዚህ በፊት በየለውጡ ያየነውን ኣይነት የኢትዮጵያውያን ስቃይ እንዲደገም አንሻም። በመሆኑም የለውጥ መሪዎች ቁጥር አንድ ስራ የህዝቡን ሰላምና ደህንነት ማስጠበቅ መሆን ኣለበት።

ከሃምሳ ቀናት በላይ በእገታ ላይ የሚገኙት የሃገር ተስፋ የሆኑ እህቶቼና ወንድሞቼ ህይወት በአንድም በሌላም መልኩ ከመንግስት የጸጥታ አመራር ጋር በቀጥታ የተገናኘ ችግር ነው። ስለሆነም መንግስት ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ እነዚህን ወጣቶች የማዳን ስራ መስራት አለበት። ወታደራዊ ጥበቦችና የአመራር ጥበቦች ሁሉ ወደነዚህ ወገኖች ሊያዘነብሉ ይገባል። እኔ እንደገባኝ አጋቹ ታውቋል። ምክንያቱም የጠቅላይ ሚንስትሩ ጽህፈት ቤት ሰክሬታሪያት አቶ ንጉሱ ጥላሁን ሲናገሩ እንደሰማሁት የተለቀቁ ተማሪዎች እንዳሉና ለቀሩት ድርድር እየተደረገ እንደሆነ ገልጸዋል። ይህ ማለት መንግስት ኣጋቹን ኣውቋል ማለት ነው። ስለዚህ እነዚህ እህቶቻችንና ወንድሞቻችንን የማትረፍ ኦፐሬሽን መደረግ ኣለበት። ይህ ኦፐሬሽን በከፍተኛ የሰኪዩሪቲና ወታደራዊ ጥበብ የታገዘ መሆንም አለበት። መረጃዎች ለህብረተሰቡ መገለጽ አለበት።

በተለይ ደግሞ ሴት ልጅ በሽፍታ እጅ ወድቃ የሚተኛ ማህበረሰብ የለንም። ሴት በሽፍታ እጅ ወድቃ እንቅልፍ ኣይኖረንም። የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችም ሆናችሁ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በተቀናጀ ትግል እነዚህን ሴቶች መታደግ ያስፈልጋል። ይህንን በማድረግ በሃገራችን ቀድሞ የማናውቀውን ይህንን የማገት ጅማሮ ከስሩ መንቀል ኣለብን። ኢትዮጵያችን የቦኮሃራም ዋሻ ልትሆን በምንም ዓይነት ኣንፈቅድም። በመላ ሃገሪቱ የምትገኙ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የብሄር ልዩነትን ጌጥ አድርጋ ሁ ኢትዮጵያ ውስጥ ቦኮሃራም ቦታ የለህም ማለት አለባችሁ። ለአጠቃላይ የሃገራችን የደህንነት ዋስትና ቆርጣችሁ መነሳት አለባችሁ። የትም ዓለም ቢሆን ዴሞክራሲና መልካም ኣስተዳደር የመጣው በትግል ነው። መንግስት በገፋነው ልክ የሚሄድ ነገር ነውና ለውጡ በሰዎች መጉላላትና ደም ላይ ሳይሆን በሰላምና በአንድነት እንዲቀጥል ንቅናቄዎች ያስፈልጋሉ።

ሴት ልጁ የተነካበት ማህበረሰብ ቀፎው እንደተነካበት ንብ ብድግ ብሎ ሊነሳ ይገባል። ለውጥን የሚመራው ህዝብ ነውና በየጊዜው ለውጡን የሚያስቱ ሁኔታዎች ሲፈጠሩ ህዝቡ አቅጣጫ የማሳየትና የመታገል ሃላፊነቱን በንቃት ሊወጣ ይገባል።

እግዚአብሄር ኢትዮጵያን ይባርክ!

ገለታው ዘለቀ (geletawzeleke@gmail.com)

Filed Under: Opinions, Social Tagged With: bring back our sisters, Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule