• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ጄኔራል” አደም መሐመድ፤ ከሬዲዮ ኦፕሬተርነት እስከ መረጃና ደኅንነት ዳይሬክተርነት

June 14, 2018 11:18 pm by Editor 5 Comments

ወሎ-አምባሰል የተወለደው አደም መሐመድ በ1975 ዓ.ም ኢህዴንን የተቀላቀለ ነባር ታጋይ ነው። በትጥቅ ትግሉ ወቅት በዋናነት የአዲሱ ለገሰ ሬዲዮ ኦፕሬተር ሆኖ ሰርቷል። አንዳንዶች በሰውየው ላይ ሲቀልዱ “የአዲሱ ለገሰ ሻሂ አፍይ” ይሉት ነበር። አደም መሐመድ ለአዲሱ ለገሰ ለአምልኮ የቀረበ ፍቅር ያለው በመሆኑ በሬዲዮ የሚተላለፉ መልዕክቶችን በጽሁፍ ከመገልበጥና መረጃዎችን ከማድረስ ባሻገር ለሰውየው ማሸርገድ ይወድ ነበር የሚሉት የእርሱ ዘመን ጓዶች፣ አድርባይነቱን ያለ ልዩነት ይስማሙበታል። ከኢህአዴግ ምስረታ በኋላ በነበሩ አውደ ውጊያዎች በ“ዘመቻ ዋለልኝ” እና “ኢህአዴግ ፋና” በተሰኙ ዘመቻዎች ላይ ተሳትፏል።

በትጥቅ ትግሉ ወቅት እንደ ድርጅት “መስመር ማጥራት” በሚል በተለያዩ ጊዜያት በተካሄዱ ሴሚናሮች፣ ኮንፍረንሶች እና በሁለቱም ድርጅታዊ ጉባዔዎች (1976 እና 1981ዓ.ም) ላይ ታጋዩ በድርጅታዊ ነፃነትና በህወሓት ጣልቃ ገብነት ዙሪያ ሲከራከርና ሲጨቃጨቅ ድምጹን አጥፍቶ፣ አጨብጭቦ የሚወጣ ሰው ነበር። በተለይም ከኃይልና ከዚያ በላይ ላሉ የግንባርና የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት መሽቆጥቆጥ የሚያበዛ ሰው እንደነበር የትግል ጓዶቹ ይመሰክራሉ። ይህ ባህሪው አድጎ የጄኔራልነት ማዕረግ ካገኘ በኋላም በተለያዩ ወታደራዊ ኮንፍረንሶችና ስብሰባዎች ላይ “እከሌ እንዳለው፣ እሱ ከተናገረው ላይ የምጨምረው ነገር ቢኖር፣…” እያለ ሰግዶ የሚኖር ሰው መሆኑን የጎልጉል ምንጮች ይናገራሉ።

በድህረ-ደርግ የሠራዊት አደረጃጀት ወቅት ወደ አየር ኃይል የተመደበው አደም መሐመድ፣ አየር ኃይል ውስጥ ከበረራ እስከ ጥገና፣ ከአየር ወለድ እስከ አየር ላይ የመጀመሪያ ህክምና እርዳታ አሰጣጥ ድረስ የደረሱ ልዩ ልዩ ሥልጠናዎችን ወስዷል። በውል የተመዘገበ የጦር አየር በረራ ቆይታ ባይኖረውም፣ ስንቅና ቁስለኛ አመላላሽ የሆኑ ሂልኮፕተሮችን ያበርር ነበር። በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ጊዜ በሂልኮፕተር ስንቅ አመላላሽ በመሆን እንዳለገለገለ የሚያስታውሱት የቅርብ ጓዶቹ፣ ዛሬ ላይ በህይወት በሌለው የኢህዴን መስራች በነበረው ሜ/ጀኔራል ኃይሌ ጥላሁን አጋዥነት በአየር ኃይል ውስጥ የቀጠና ስምሪት አዛዥ በመሆን ሲሰራ ቆይቷል። በባድመ ጦርነት ወቅት ሻላቃ የነበረው አደም መሐመድ በአስራ ሰባት አመት ውስጥ ሙሉ ጀኔራል ማዕረግ ላይ ደርሷል። በዚህ ጊዜ ሂደት ሰውየው ይህ ነው የሚባል የውጭ አገር ትምህርት አልወሰደም። በርግጥ አሜሪካ ሁለት ጊዜ፣ እስራኤል አንድ ጊዜ ለሥራ ጉብኝት እንደሄደ የሚገልጹት የጎልጉል የመረጃ ምንጮች እነዚህ ጉዞዎች ግን ለጀኔራልነት ማዕረግ ያበቃሉ ማለት እንዳልሆነ አክለው ይገልፃሉ።

ድህረ-ደርግ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ በመሆን በተከታታይ ከሰሩት፡- ሜ/ጀኔራል አበበ ተ/ኃይማኖት፣ ሜ/ጀኔራል ኃይሌ ጥላሁን፣ ሜ/ጀኔራል ዓለምሸት ደግፌ ቀጥሎ የአየር ኃይል ዋና አዛዥ የሆነው ጀኔራል አደም መሐመድ በስታፉ ውስጥ እንደቀደሙት አዛዦች የሚከበር ሰው አልነበረም።ሰውየው ራሱን ችሎ ውሳኔ ለመስጠት የሚቸገርና የአድርባይነት ዝንባሌ የተጫነው ህወሓት አምላኪ ነው የሚሉት የጎልጉል ምንጮች፣ ውሃ በማይቋጥሩ ምክንያቶች 13 ጄኔራሎች፣ 45 ኮሎኔሎች፣ 250 ሻለቆች፣ ከ41000 በላይ የመስመር መኮንኖችና ተራ ወታደሮች አማራ በመሆናቸው ብቻ ሰበብ እየተፈለገ ከሠራዊቱ ሲሰናበቱ “ለምን?” የሚል ጥያቄ ማንሳት ቀርቶ “የትምክህት ሰለባዎች” እያለ ከነአዲሱ ለገሰ ጋር ሆኖ ሲያንቋርር የኖረ አድርባይ ሰው ለመሆኑ አስረጅ ምሳሌ አድርገው ያቀርቡታል።

በጥር 2010ዓ.ም ወልድያ ከተማ በጥምቀት በዓል ላይ በታቦታቱ ፊት በአጋዚ ወታደሮች በርካታ ምዕመናን መረሸናቸው የሚታወስ ነው። ይህንን መንግሥታዊ ፍጅት ተከትሎ በተከታዩ ሳምንት በቆቦ ከተማ በተካሄደው ህዝባዊ ተቃውሞ ላይ ያለ አየር ኃይሉ ዋና አዛዥ (“ጀኔራል” አደም መሐመድ) ዕውቅናና ፍቃድ የሰሜን ዕዝ የአየር ኃይል ቤዝ በከተማው ላይ መትረየስ የጫነ ሂሊኮፕተር አሰማርቶ ህዝብ ሲያሸብር የዋለበት ሁነት ስለሰውየው የአመራር አቅምና ተደማጭነት መጠን የሚናገረው እንዳለ ብዙዎች የሚስማሙበት ነው።

አደም መሃመድ ከወታደራዊ ፕሮቶል ውጪ መለዮ እንዳደረገ ለመለሰ ሞት ሲያለቅስ

በሚያዚያ 2001ዓ.ም “የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ አድርጋችኋል” በሚል ከታሰሩት የኢህዴን/ብአዴን ነባር ታጋዮች ውስጥ አንድ ቤት አብረው ያደጉት፣ በ1975 ዓ.ም ወደትግል አብረው የወጡት የእህቱ ልጅ ኮሎኔል ፋንታሁን ሙሓባ ዘጠኝ ዓመት በዝዋይ እስር ቤት ውስጥ ሲማቅቅ አንድ ቀን እንኳ ማረሚያ ቤቱ መጥቶ ያልጠየቀው መሆኑ፣ ስለሰውየው አድርባይነትና ፍርሃት የሚነገርን ብዙ ነገር አለ የሚሉት የቀድሞ ጓዶቹ “ሰውየው ራሱን ችሎ መቆም የማይችል የአዲሱ ለገሠ የእጅ ሥራ ውጤት ነው” ሲሉ አስተያየታቸውን ይሰጣሉ።

ህወሓትን እንደ ብቸኛ ነፃ አውጪ ድርጅት፣ መሪዎቹን ደግሞ እንደ ፈጣሪ የሚያየው አደም መሐመድ፤ይሄ ባህሪው በአንድ ጀንበር የያዘው እንዳልሆነ የቀድሞ ጓዶቹ አስተያየታቸውን ይሰጣሉ። “የአዲሱ ለገሰ የቅርብ አሸርጋጅ ሆኖ ለዓመታት የኖረ ሰው ከመሆኑ ጋር ይያያዛል” የሚሉት የጎልጉል መረጃ ምንጮቻችን የአየር ኃይል ዋና አዛዥ ሆኖ እየሠራ እንኳ የሳምንቱን የዕረፍት ቀናት ጠመንጃ ያዥ አካባቢ ባለው የአዲሱ ለገሰ ቤት እንደሚያሳልፍና ምክር ሲቀበል እንደሚውል ይናገራሉ። አዲሱ ለገሰ ከህወሓት ሰዎች በላይ ለህወሓት ድርጅታዊ ህልውና የሚጨነቅ ብአዴንን እንደ አማራ “ጠባይ ማረሚያ” የሚገለገልበትን የድርጅቱን ብአዴንን መነቃቃትና የአማራን ሕዝብ ቀና ብሎ መሄድ የማይወድ ሰው ከመሆኑ ጋር በተያያዘ የበረሃ ሻይ አፊይው አደም መሐመድ አሁን የያዘውን ቁልፍ ቦታ በእነ አዲሱ ለገሰ “የቅዳሜ ምክር” ለህወሓት ፖለቲካል-ኢኮኖሚ ጥቅም መገልገያ ማስጠበቂያ ከማድረግ ወደ ኋላ የሚል አይመስልም።

“ለራሱ ተገቢ የሆነ ክብር መስጠትና መብቱን ማስጠበቅ አይችልበትም” እየተባለ የሚብጠለጠለው አዲሱ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት ዳይሬክተር አደም መሐመድ፤ ብርጋዴል ጄኔራል እያለ አዲስ አበባ ሳሪስ አካባቢ በተሰጠው አነስተኛ ቪላ ቤት ዛሬም ሙሉ ጀኔራል ሆኖ እዛው ጠባብ ቪላ ቤት ውስጥ እንደሚኖር የመረጃ ምንጮቻችን ዘገባ ያመለክታል። የህወሓት ጄኔራሎች በምን ዓይነት የቅንጦት ህይወት እንደሚኖሩ ልብ ይሏል። በጠባብ ቪላ ቤት ውስጥ ኑሮውን ለመኖር መምረጡ ሰውየውን ራሱን የካደ አብዮተኛ ወታደር አያስብለውም (ላለመሆኑ ብዙ ማሳያዎችን ማቅረብ ይቻላል) የሚሉት የቀድሞ ጓዶቹ “እንደ ጄኔራልነቱ ሊያገኝ የሚገባውን መብቱን የዘነጋ፣ ራሱን በፍርሃት የቀበረ ጄኔራል ብንለው የሚያንስበት እንጅ የሚበዛበት አይደለም” ሲሉ የከረረ አስተያየታቸውን ለጎልጉል ሰጥተዋል።

የብሔራዊ መረጃና ደህንነት ዋና ዳይሬክተር ሆኖ ለአስራ ስምንት ዓመታት ሲሰራ ከነበረው ጌታቸው አሰፋ ጋር አዲሱን ተሿሚ ማወዳደር ተገቢ ባይሆንም በራስ የመተማመንና የውሳኔ ሰጪነት አቅማቸው ግን ለንጽጽር የሚቀርብ አይደለም። በመረጃ እገታ እና በአፈና መዋቅሩ ራሱን ስውር ጠቅላይ ሚኒስትር አድርጎ ከኖረው ጌታቸው አሰፋ በራስ የመተማመን አቅምም ሆነ የመረጃ ትንተና ችሎታ ጋር ማወዳደር ፍርደ ገምድልነት ይሆናል የሚሉት የመረጃ ምንጮቻችን፤ ከመረጃና ደኅንነት ጉዳዮች አኳያ በአገር ውስጥ፣ በቀጠናው፣ በመካከለኛው ምስራቅ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ላይ ያለውን ፈጣን ለውጥና የመረጃ ልውውጥ በብቃት መምራት የአዲሱ ተሿሚ ቀጣይ የቤት ሥራዎች ይሆናሉ። በተለይም ከዓለምአቀፎቹ የመረጃና ደኅንነት ተቋማት ጋር የሚኖረውን አጋርነት ማስቀጠል የሬዲዮ መልዕክት የመቀበል ያህል ቀላል እንደማይሆን ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ ይናገራሉ።

ከጌታቸው አሰፋ መነሳት በኋላ በደህንነት መስሪያ ቤቱ ውስጥ የአደረጃጀት እና በየዘርፉ ያሉ አመራሮች ለውጦች ሊደረጉ እንደሆነ ለጎልጉል የደረሱት መረጃዎች ያመለክታሉ። በተለየ መልኩ የአገር ውስጥ ጉዳዮች እና የቀጠናው የመረጃ መረብ ትስስር መጠናከር ትኩረት የተሰጠው በመሆኑ፤ ህወሓት ለረዥም ዓመታት በብቸኝነት ይዞት የቆየ መስሪያ ቤት እንደመሆኑ መጠን ትምህርትና ሥልጠና ከልምድ ጋር ተጣምረው ከሚፈጥሩት የኤጀንትነት ብቃት አኳያም ቢሆን የህወሓት ሰዎች በታኮነት ቦታ የሚያጡ አይመስልም። ከሬዲዮ ኦፕሬተርነት ተነስቶ አድርባይ ባህሪውን ተሞርክዞ የመረጃና ደኅንነት ዳይሬክተር ለመሆን የበቃው “ጀኔራል” አደም መሐመድ ኢትዮጵያን ወይም ሕወሓትን ለመምረጥ ግድ የሚለው ጊዜና ወንበር ላይ ተቀምጧል። እንደቀደመው የሥራ ዘመኑ በአድርባይነት ለጌታቸው አሰፋ የስልክ ጥሪዎች ታዛዥ ሆኖ መቀጠል ወይም ህዝባዊ ውግንና ይዞ የአፓርታይድ አገዛዝ ማስፈጸሚያ ሆኖ የቆየውን መስሪያ ቤት ለታሪክ የሚበቃ ሥር-ነቀል ለውጥ ማምጣት። ምርጫው በእጁ ላይ ነው። (የፊት ፎቶ የተወሰደው ከሪፖርተር ጋዜጣ ነው)

(በቀጣይ ዕትም የጌታቸው አሰፋን ሌጋሲ በተመለከተ ዘገባ እናቀርባለን)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: adem mohammed, Full Width Top, Middle Column, NISS

Reader Interactions

Comments

  1. abe says

    June 16, 2018 11:22 am at 11:22 am

    Too much talk, time to deliver.

    Reply
  2. Ezira says

    June 16, 2018 02:57 pm at 2:57 pm

    የሰው ልጅ ከክበሩ ወረዶ 2 እግር ያለው እንሥሣ መሆን እንደሚችል ማሳያው የትግሬ ወያኔ የማፊያ ቡድን አንዱ ነው። (ክቡሩ ሰው) የተባለው ፍጡር ሣር የማይበሉ ባለ 2 እግሮች የእንስሳዎቹ ጉሮኖ የሆነው የትግሬ ወያኔ የወንበዴው ቡድን ፤ ደረጃቸው ይለያይ እንደሆን እንጅ ተቋሙ እንዳለ ከሰውነት የወጡ ባለ 2 እግር እንሰሶች መሆናቸው ለአደባባይ ተጋልጧል። ለምሳሌ አያቱ እንግሊዛዊ የሆነው ሰካራሙ ስብሃት ነጋ እጅግ እጅግ የወጣለት አፍሪካዊነቱን የሚጠላ፤ ኢትዮጵያዊነቱ የሚያንገሸግሸው፤ ትግሬነቱ ደግሞ ይበለጥ እከከ የሆነበት ለመሆኑ ለ 1 ቀን ጠጋ ብሎ ከእንስሳው ጋር ለቆዬ ሰው፤ ባለ 2 እግሩ እንስሳ ከእንስሳዎቹ የትኛው ጋ እንደሚመደብ ይቸግር ይሆናል እንጅ በስዉነቱ የሚያፈር፡ የማነነት ቀውስ ያለበት አሳማ መሆኑን ትረዱታላችሁ። ይሄን የማንነት ቀውሱን በገንዝብና በሃብትም እንኳ ሊሸፍነው አልቻለም። ሁልግዜ ይደባደባል። ሚስቱን በስከረ ቁጥር በዱላ እየነረተ በማሰቃየት የሚረካ ወዘተ….ፍጡር ነው። አያድርስ ነው የእርሱማ መላ ቤተሰቦቹ ፀረ፡ ሰው ማለት ናቸው ማለት ይቻላል። ፀረ ሰው መሆን ማለት ምን ማለት እንደሆነ እንግዲህ .ማብራሪያ የሚያስፈልገው አይመስለኝም። በነገራችን ላይ ሚስቱም የጣሊያን ክልስ ናት። አባቱ ደግሞ ትሩንቡሌ እንደነበር፣ ሳይዘነጋ

    Reply
  3. Bek says

    June 23, 2018 02:13 pm at 2:13 pm

    Bravo Ezira, Tell them the truth. God bless you brother.

    Reply
  4. Abay Big says

    July 12, 2018 06:06 pm at 6:06 pm

    ላም ያል ዋለበት ኩበት ለቀማ፡
    ስለ ጄኔራሉ እየ ተቦኘቀ፡
    Ezira ድግሞ ህወሓት, ትግራዋይ, እንስሳ, ኣቦይ ስብሓት, ምናምን ትላለህ ሙትቻ !!!
    ወንዳወንድ የሆነ ሃሳብ ማስቀመጥ ካልቻልክ ዝምታ ክብር ኣለው።

    Reply
  5. seyaw love says

    September 12, 2018 11:45 pm at 11:45 pm

    ጀኔራል አደም መሀመድ የተወለደው በደቡብ ወሎ ዞን ወርባቦ ወርዳ ነው፡

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule