• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለ6 የህወሓት ተጧሪዎች በ150 ሚሊዮን ብር የተገነቡት ቤቶች በ1.2 ቢሊዮን ብር ሊሸጡ ነው

October 14, 2020 12:02 am by Editor Leave a Comment

ወሳኔው የተላለፈው በዚያን ጊዜው ህወሓት እንደፈለገ በሚዘውረው ፓርላማ ነበር።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ “የኢህአዴግ ከፍተኛ ሹሞችን ልዩ ልዩ ጥቅማጥቅም የሚያስከብር አዋጅ ጸደቀ” በሚል ርዕስ (February 13, 2017) ባተመው ዜና መረጃውን ሲዘግብ ይህንን ብለን ነበር፤

ከሁለት ዓመት በፊት በጭምጭምታ ደረጃ ወሬዉ ወደ አደባባይ የወጣዉ ባለሥልጣናት “ጡረታ” ሲወጡ የሚከበርላቸዉ ጥቅማጥቅም አሁን “ህጋዊ  ዕዉቅና” አግኝቷል።

ሐሙስ ዕለት በዋለዉ የኢህአዴግ “ፓርላማ” የህወሃት/ኢህአዴግ ከፍተኛ ባለሥልጣናት በልዩ ልዩ ምክንያቶች ከኃለፊነታቸዉ ሲነሱ ጥቅማጥቅማቸዉን የሚያስከብር አዋጅ ተሸሽሎ እንዲጸድቅ ተደርጓል።

የተሻሻለዉ አዋጅ ከኃላፊነታቸዉ የሚነሱ የመንግስት ባለሥልጣናት እንደ የኃላፊነት ደረጃቸዉ የመቋቋሚያ አበል፣ የሥራ ስንብት ክፍያ፣መኖሪያ ቤት፣የቤት ሰራተኞች፣ የምግብ አብሳዮች፣ የቀንና የማታ ቤት ጠባቂዎች፣ የተሸከርካሪ አገልግሎት ከነአሽከርካሪዉና ጠባቂ (body guard) እንዲሟላላቸዉ አዋጁ ያብራራል።

ቀደም ሲል ለኢህአዴግ ነባር ታጋይ ባለሥልጣናት መኖሪያ ቤት በሚል ከመንግስት ካዝና ያለ ፓርላማዉ ይሁንታ (ምንም እንኳን ልዩነት ባይኖረዉም) በአዲስ አበባ ወረገኑ አካባቢ አርሶ አደሮችን በማፈናቀል “ጡረታ ለሚወጡ ስድስት ከፍተኛ የኢህአዴግ ባለስልጣናት በመቶ ሃምሳ አራት ሚሊዮን ብር (እያንዳንዳቸው ከ25 ሚሊዮን ብር በላይ በድምሩ 154 ሚሊዮን ብር) መጦሪያ ቤቶች ተገንብተው እየተጠናቀቁ” መሆናቸውን ጉዳዩን በኃላፊነት የሚመራው ተክለጻዲቅ ተክለአረጋይ (አቡነአረጋይ) ታህሳስ 1፤2008ዓም/November 12, 2015 ለሸገር ሬድዮ መናገሩ በዕለቱ ተዘግቦ ነበር። ተክለጻዲቅ ሲቀጥልም “አገራችን እነዚህን ቤቶች ለባለስልጣኖች መገንባቷ ከአፍሪካ አንደኛ ያደርጋታል” ከማለቱ በተጨማሪ “የመዋኛ ገንዳ (ስዊሚንግ ፑል) ያላቸው እነዚህ ቅንጡ ቤቶች የሚገነባላቸው ባለስልጣኖች ተለይተው መታወቃቸውን” ማስረዳቱ የህወሃት/ኢህአዴግን ዓይነደረቅነት ያሳየ ተግባር ሆኖ ነበር።

ዜናውን አያይዞ “ከጠቅላላ ሕዝቧ ውስጥ ከ2 ፐርሰንት በታች ለሆኑ አዛውንት ዜጎቿ የጡረታና የማህበራዊ ዋስትና የሌላት አገር ብትሆንም በስልጣን ዘመናቸው በሚሊዮን የሚቆጠር ብር ለዘረፉ ሌባ ባለስልጣኖቿ ግን ቅንጡ መጦሪያ ቤት የምትገነባ አገር ሆናለች” በማለት በወቅቱ በተጨማሪ መዘገቡ የሚታወስ ነው።

ሰኞ ዕለት የገንዘብ ሚኒስቴር ባታወቀው መረጃ መሠረት እነዚህ ቅንጡ ቤቶች ሊሸጡ መወሰኑን ገልጾዋል። እንዲህ ይነበባል፤

አገልግሎታቸውን አጠናቅቀው በጡረታ ለሚወጡት የቀድሞ የመንግሥት ከፍተኛ ባለስልጣናት የተገነቡት ቅንጡ መኖርያ ቤቶች ሊሸጡ ነው ተብሏል።

ዘመናዊ የመኖርያ ሕንፃዎቹ ለታለመለት  ዓላማ ስላልዋሉ ገንዘብ ሚኒስቴር ቤቶቹ ተሽጠው ለግንባታ ያወጣሁት ወጪ ይመለስልኝ ማለቱን ሸገር ኤፍኤም 102.1 ዘግቧል።

በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትርን ጨምሮ ለከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ተብለው የተገነቡት ቄንጠኛ መኖርያ ቤቶች 6 ናቸው።

CMC አካባቢ ከተገነቡት 6 እጅግ ዘመናዊ ቤቶች መካከል ትልቁ 2,441 ካሬ ሜትር ላይ አርፏል። ለአንዱ መኖርያ ቤት ብቻ በጨረታ የመሸጫ ዋጋ መነሻ ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ ተጠይቋል። በአጠቃላይ እስከ 1.2 ቢሊዮን ብር ከቤቶቹ ለማግኘት ታስቧል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Left Column, News Tagged With: luxury homes in cmc, tigray, tigray tplf election, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule