አዲሱ ዓመት መጣና ፤ ጎረቤቴን የሰፈሬን ልጅ እንኳን አደረሽ ብላት ፤ መልካም ምኞቴን ሳውጅ እኛን አያገባንi ብትለኝ ፤ እንዴት? ለምን? ብየ ጠየኳት አታውቅም ? በእኛ ሃይማኖት ፤ ጃንዋሪ ላይ ነው አዲስ ዓመት ብላ ብትለኝ ደንግጨ ፤ ሆኘ ቅርት የጨው ሀውልት አየ አዲስ ዓመት እንቁጣጣሽ ፤ በምድሪቱ ሳይቀር ተበሳሪ ተፈጥሮ አጅቦ የሚያመጣት ፤ በአበባ ልምላሜው ከባሪ የእኛ አይደለሽም ተባልሽ ? እዚሁ በምድርሽ በቅሎ ማዛሽ ማዛው ላይ እየናኘ ፤ ከአፈር አየርሽ ኮብልሎ ምን ሳይሰማ እንዲሉ ፤ እንዲህም መቷላ ጉድ ፈጦ መለያን ከስሩ ነቃቅሎ ፤ ልብን ከልብ ላይ ቆርጦ አሁን ይህችን ልጅ እኅቴን ፤ ማን ናት ምን ብየስ ልጥራት እነሱስ ሰባኪዎቿ ፤ ሰላዮቹ የቅኝ ግዛት ማን ብለው ይሆን ትውልዷን ፤ የሷን ዜግነት … [Read more...] about ማንነት (identity)
Literature
ጽፈኪን
የነፃነት አባት
ታ ሪኩ ገናና፤ ስራው የለው አቻ ላ ሰበበት ጉዳይ፤ የሌለው ፍራቻ ቁ ጣን ቂም በቀልን፤ ያጠፋ ጥላቻ ማ ንዴላ ታላቁ፤ የነፃነት ጮራ ን ጥረ መብረቅ ሆኖ፤ አፍሪካን ያስጠራ ዴ ሞክራሲ እንዲያብብ፤ ተስፋውን ሰንቆ ላ ሰበው አላማ፤ ቆሞ ነበር ታጥቆ የ ህይወት ዘመኑ፤ ቢሆንም መራራ ነ ፃነት አላብሷል፤ ስሙን የሚያስጠራ ፃ ድቅ የሆነ ሰው፤ እያለ በሕይወት ነ ውና ተግባሩ፤ መልካም ነገር መስራት ት ዕዛዙን ፈጽሟል፤ በእድሜው ዘመናት ዓ ለም መቆያ ናት፤ ተቀባይ እንግዳ ባ ህሪዋ መራር፤ ወሳጅ በሞት እዳ ት ልቅ ትንሽ ሳትል፤ ድንገት የምትከዳ ና ልን አይባልም፤ ማንዴላም ተመለስ ቸ ሩ ፈጣሪያችን፤ የታላቁን ሰው ነፍስ ው ለታ ይክፈላት፤ ወደሱ ስትደርስ … [Read more...] about የነፃነት አባት
በቃ! በለን አምላክ (say us enough! O’ God)
ያ የምትወደው ፤ ያ የምታሞካሸው ልጆቸና ሕዝቤ ፤ እያልክ ያከበርከው መከራ አፈናቅሎት ፤ ከሀገሩ ከቀየው ከአሕዛብ ደጅ ወድቆ ፤ ግፍ ሰቆቃ ቆላው፡፡ የጭንቅን ልክ ዓየ ፤ ሞት በዓይነት ቆጠረ የሰቆቃን ጣራ ፤ ከፍ ብሎ በረረ ሞትን ተላመደ ፤ ንቆም ተዳፈረ በእሱ እየተበላ ፤ በእሱ ላይ ፎከረ የአውሮችን አውሬነት ፤ ተበልቶ አጋለጠ ድብቁን አወጣ ፤ ነፍሱን ለሀቅ ሰጠ፡፡ ምን ዓይነት ፍጥረቶች ፤ ምን ዓይነት ጉዲራ እውን ሰዎች ናቸው ? የሆኑ የእጅህ ሥራ ? ወይስ ሰይጤ እንዳለው ፤ እኔ ነኝ ፈጣሪ ይሆኑ ይሆን የሱ ፤ የዚያ እርኩስ መሠሪ በሁለ ነገሩ ፤ እሱን አስመስሎ እንደራሱ አድርጎ ፤ ፈጥሯቸው አንቦልቡሎ ? ወይስ ከነገዱ ፤ ከሆኑት እንደሱ ሥጋ ለብሰው መጡ ? ሰው መስለው … [Read more...] about በቃ! በለን አምላክ (say us enough! O’ God)
አፍሪካዊው ኮከብ
ጀግናው አሸለበ፣ ደከመው ተረታ ሞት አይቀርምና፣ የማታ የማታ፤ ምን ብርቱ ቢሆኑ፣ ሺ መካች ቢሆኑ ሰው አያልፍ አይገደፍ፣ ተዛቹ ተቀኑ፤ አፍሪካ ሆይ መጥኔ፣ አንድ ወልደሽ ላጣሽው ተንግዴ መሸበሽ፣ በማን ትዘከሪው? በማንስ ትጠሪው? ማንዴላ ብረቱ፣ የሮቢን ደሴቱ የዘረኞች ዋግምት፣ የጥቁር ኩራቱ- ተንግዲህ የለህም፣ ታሪክ ነበርክና ታሪክ ነህ ተንግዴ፣ ላትመጣ እንደገና፤ ዓለም አሸርግጂ፣ ቱቢት አስመቺና ደረት እየመታሽ፣ ”ወይ ልጄን...” በዪና፤ አንበሳሽ ቀን ጣለው፣ ይውጣልሽ ሀዘንሽ ሙሾሽን ደርድሪ፣ ማቅ ልበሽ እባክሽ ማንዴ እኮ ነው ሃጁ፣ ሌላው እንዳይመስልሽ፤ ባፍሪካ ሰማይ ላይ፣ የበራው ኮከብ ተወርዋሪ ነበር፣ ዐይንን የሚስብ፤ ባፍሪካ ሰማይ ላይ፣ የነጋው ጀምበር ለወገኑ ነበር፣ ብርሃንና አድባር ለጠላቱ ነበር፣ መራር እንደ ኮሶ ገፍናኝ … [Read more...] about አፍሪካዊው ኮከብ
ላምበሎቼ
በሕይወት እያላችሁ... ላለመዋደድ ተፋቅዳችሁ የኋላ ኋላ ኋላ... ባንዲት ጉድጓድ ታድማችሁ የኋላ ኋላ ኋላ... ምስጥና አፈር ላስማማችሁ የኋላ ኋላ ኋላ... ማንም ምንም ላይለያችሁ የኋላ ኋላ ኋላ... ተቃቅፋችሁ የኋላ ኋላ ኋላ... ላሸለባችሁ... ለናንተ... ላምበሎቼ ለጋሼ ኃይሌ ፊዳ ለጋሼ ብርሃነ መስቀል ረዳ እነሆኝ እላለሁ... ይህን ያገር እዳ፡፡ (በአበራ ለማ) “ጥሎ ማለፍ” ለተባለው የታሪካዊ ልቦለድ መጽሐፌ መታሰቢያ ቋጥሬው የነበረ - 2003 ዓ.ም. … [Read more...] about ላምበሎቼ
እጅ-ለጅ!
የፊት ጉዱን ረስቶ፣ ከረሀብ መትረፉን፣ የሙሴን ውለታ የእናት ጡት ነካሽ ልጅ፣ ፈርዖን በእስራኤል፣ ክንዱን አበረታ! መሄጃ ያጣህ ዕለት፣ ኢትዮጵያ አትርፋልህ፣ ዕምነትህ እንዳትጠፋ! ስማን እንጂ ሳውዲ፣ አንተም እንደፈርዖን፣ ታዋርዳት ገባህ፣ አገሬን በይፋ? ደግ እናት ነበረች፣ አንጀቷ የሚራራ፣ እግዚአብሔርን ፈሪ ኢትዮጵያ አገሬ፣ እንግዳ ተቀባይ፣ የሰው ልጅ አፍቅሪ አቅፋ የምትደብቅ፣ የተሰደደውን፣ ላትሰጥ ላባራሪ “ዕድሜ” ለወያኔ፣ ዛሬ ግን ቀን ጥሏት፣ ለጆቿ ተርበው፣ ሆኑ ጦም አዳሪ። አይ ስምንተኛው ሺ፣ የዘመን ጎዶሎ፣ ያመጣብን ጣጣ አንተም ቀን አልፎልህ፣ አሽከርና ገረድ፣ ከኢትዮጵያ ታስመጣ? እሱስ እሺ ይሁን፣ ምነዋ መርሳትህ፣ ያቺን ክፉ ዘመን ጌዜው ተለዋውጦ፣ እኛም ለአንድ እንጀራ፣ በእጅህ ላይ ሲጥለን። ዕምነትክን ረስተኸው፣ ትዕዛዙን ጥሰህ፣ … [Read more...] about እጅ-ለጅ!
ሕገ ወጥ ስደተኛ (illegal immigrant)
ምን ማለት ነው እሱ ወዳጀ፤ ይሄ ሕገ ወጥ ስደተኛ ወዶ የሚሰደድ ከሌለ፤ ከሀገሩ የሚርቅ መከረኛ ነፍሱን ለማትረፍ የሻ ሰው፤ ይሸሻል እንጅ ባመራው እንግዳ አይደለ ወይ ጎብኚ፤ ፈቃድ ጠይቆ የሚገባው እስኪ ንገረኝ እባክህ፤ ለእናንተው መሐመድ ሰዎች ተቸግረው ለተሰደዱት፤ ከሀገራቸው ላለመሆን ሟች ቪዛ ተመቶላቸው ነበረ? ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ? አሳልፋቹህ ስጡን ብለው፤ በጠላት ለሰይፍ ሲታሰቡ ውሰዷቸው ተብለው ነበር? ወይስ ቤዛ ሆነ እርግቡ? ውጡልን ተብለውስ ነበር? ፊቱን ነስቷቸው ሕዝቡ? አንተ ግን ውለታ ቢሱ፤ አምላክ የማታውቅ የማትፈራ የነፍስ ብለው የተጠጉትን፤ ለማምለጥ ከአጋንንት ጭፍራ እያረድክ ፈነገልካቸው፤ ደፍረህ አርክሰህ በጠራራ ይሄ ነው ላንተ ጽድቅ ማለት፤ ደም ጠጥቶ መስከር ግፍ ሥራ ከሰይፍህ … [Read more...] about ሕገ ወጥ ስደተኛ (illegal immigrant)
ዕንባሽ ተናገረ!
ዘለላ ዘለላ ዱብ ዱብ በሚለው፤ ጉንጭሽን ሸርሽሮ ቁልቁል በሚፈሰው፤ ሳግ እንቅ እድርጎ በሚተናነቅሽ፤ በ’ንባሽ እያጠቀስኩ ስንኝ ቋጠርኩልሽ፤ ቃል ኪዳን ነውና አንብቢው አደራሽ:: (ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about ዕንባሽ ተናገረ!
የወገኔ ቅኔ
እንዲህ እንዲያ ብለው አሙን ፤ ተጠይቀው ሲመልሱ የወገኖቻችንን ደም ፤ በእብደት ግፍ ያፈሰሱ የኢትዮጵያ ስደተኞች ፤ ባሕላችንን ተቃረኑ ንጽሐችንን አረከሱ ፤ ነፍሳችንን አስኮነኑ መጠጥ በማዘዋወር ፤ በስርቆት ወንጀል በምኑ አንተ አረመኔ እንስሳ ፤ ምኑን ብየ ላውጣልህ ስም መጠጥ ምንህ ነውና ፤ ስካርህ የአንተ በሰው ደም አስገድዳ አልደፈረችህ ፤ ደፈርካት እንጅ በማደም መድፈርህ ሳያንስ ሳይበቃ ፤ አርደህ በላሃት ርጉም አንተ ውሉደ አጋንንት ፤ አረመኔ ዘረ ሰዶም ፡፡ ሌቦች ነበረ ያልካቸው ? እሰይ እንኳንም ሰረቁ ፈልገውት እንዳይመስልህ ፤ ምንም ነገር አይደል ድንቁ እባክህ ለከት ይኑርህ ፤ በዚህ አይታማም ወገኔ ነቢይህ ያውራህ ታሪኩን ፤ ያበሻን ማንነት ብያኔ የፍትሕ ደግነት ባለቤት ፤ ሕዝብ … [Read more...] about የወገኔ ቅኔ
እንደማያልፍ የለም
አዎ፤ የኔም እምባ ፈሷል እምነቴ ደፍርሷል ሰበዕናየ አንሷል ምክንያት ፍለጋ - መፍትሄ ፍለጋ ቀኑ እስከሚጨልም - ሌሊቱ እስቲነጋ ብቆርጥ ብቀጥል - ባነሳ ብጥለው ዘላለም ሆነብኝ - ማለቂያ የሌለው ሕመምሽ አሞኛል ድካምሽ ደክሞኛል እምባሽን ለመጥረግ - አቅም በማጣቴ ሕሊናየ ቆስሏል - ተቃጥሏል አንጀቴ እና….ጠንክሪ እህት ዓለም ይሄም ቀን ይረሳል - እንደማያልፍ የለም … [Read more...] about እንደማያልፍ የለም