• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በቃ! በለን አምላክ (say us enough! O’ God)

December 8, 2013 10:07 pm by Editor 1 Comment

ያ የምትወደው ፤ ያ የምታሞካሸው

ልጆቸና ሕዝቤ ፤ እያልክ ያከበርከው

መከራ አፈናቅሎት ፤ ከሀገሩ ከቀየው

ከአሕዛብ ደጅ ወድቆ ፤ ግፍ ሰቆቃ ቆላው፡፡

የጭንቅን ልክ ዓየ ፤ ሞት በዓይነት ቆጠረ

የሰቆቃን ጣራ ፤ ከፍ ብሎ በረረ

ሞትን ተላመደ ፤ ንቆም ተዳፈረ

በእሱ እየተበላ ፤ በእሱ ላይ ፎከረ

የአውሮችን አውሬነት ፤ ተበልቶ አጋለጠ

ድብቁን አወጣ ፤ ነፍሱን ለሀቅ ሰጠ፡፡

   ምን ዓይነት ፍጥረቶች ፤ ምን ዓይነት ጉዲራ

   እውን ሰዎች ናቸው ? የሆኑ የእጅህ ሥራ ?

   ወይስ ሰይጤ እንዳለው ፤ እኔ ነኝ ፈጣሪ

   ይሆኑ ይሆን የሱ ፤ የዚያ እርኩስ መሠሪ

   በሁለ ነገሩ ፤ እሱን አስመስሎ

   እንደራሱ አድርጎ ፤ ፈጥሯቸው አንቦልቡሎ ?

   ወይስ ከነገዱ ፤ ከሆኑት እንደሱ

   ሥጋ ለብሰው መጡ ? ሰው መስለው ሊያረክሱ

   ሕዝብህን በመቅጣት ፤ አንተን ለመበቀል

   ልጆች እንዳይኖሩህ ፤ ከርስትህ በመንቀል

   ካልሆነ እንዴት ታዲያ ፤ ሰው ሆነው የአዳም ዘር

   ሰብአዊ ሕሊና ፤ እንዴት አጡ ፍቅር ?

   ጥቂት ሐዘኔታ ፤ ሩኅሩኅ መሆን ገር

   እውን ከዚህ እርጉም ዘር ፤ ከእኩያን ልቡና

   ጽድቅ ይወጣል ብሎ ፤ ሰው ያምናል ሊቀና ?

   ካልሆነ የዋህ ጅል ፤ ዕውቀት የገደፈ

   በሥጋዊ ጥቅም ፤ ልቡ የተነደፈ

   የዝሙት ጥማቱን ፤ ሊያረካ የወደደ

   ያማሩትን ሁሉ ፤ መርጦ እያጠመደ

   በሴት ለመጫወት ፤ በአንድ ቤት አጉሮ

   አንጋግቶ ለመንዳት ፤ በእንስሳ ተፈጥሮ

   ሴት ሰው እንዳልሆነች ፤ እንደ እቃው ቆጥሮ

   የእሱ መጠቀሚያ ፤ ሆና የሱ ቋጠሮ

   የራሷን ፍላጎት ፤ አሳጥቶ ቀብሮ

   እሷም ልክ እንደሱ ፤ ሰው መሆኗ ቀርቶ

   እንደ ሰውነቷም ፤ እኩል መብቷን ነስቶ

   ጨቁኖ ለመግዛት ፤ ለመርገጥ አፍኖ

   የሚሻ ማስበርገግ ፤ እንደ ባሪያ አባክኖ

   ጾም ሳይልም ፍስክ ፤ ለመክተት ጮማ እርጎ

   በቅቤ እንቁላሉ ፤ ለመውዛት መግምጎ

   ገደብ ሳይኖርበት ፤ ለመድለብ ጠራርጎ

   ይሄን ይሄን ምቾት ፤ ኃጢአት ነው ሳይባል

   ማግኘት የፈለገ ፤ ራሱን የሚያታል

   ይሄ ዓይነት ተላላ ፤ አዎ እሱ ይሆናል ፡፡

   ታዲያ እሱ ምን ያርገው ፤ ከአውሬ ቢሆን አቻ

   ሆድ እንዲህ ሲሞላ ፤ ሲፈረጥም ጡንቻ

   ባዶ መሆኑ አይቀር ፤ ጭንቅላት ተራቁቶ

   ለማሰብ ተስኖት ፤ ሰብአዊነት አጥቶ

   ከእጁ የወደቁትን ፤ ከወልደ ሳጥናኤል

   በእስር ቤት አጉሮ ፤ በምድር ላይ ሲዖል

   ሕፃናት አልቀሩ ፤ አሮጊት ሕሙማን

   ሴቷ አልቀረች ወንዱ ፤ ደፍረው አረከሱን

   ብረት እያጋሉ ፤ በአፈ ማኅጸኗ

   በወንዱም ፊንጢጣ ፤ ወዮ ወዮ ቀኗ

   በዘይት መላጡ ፤ በፎቅ መወርወሩ

   የሰው ልጅ እንደ በግ ፤ በሰይፍ መመተሩ

   በረሀብና ጥም ፤ ሲሰቃይ በጠኔ

   ተሰዶ መግባቱ ፤ ሆኖበት ኩነኔ

   ብልቱን ሲቆርጡት ፤ ሲያስጓራው ሰቆቃ

   የስቃዩን ጩኸት ፤ የጣሩን ድምፅ ሲቃ

   መስማት የሚናፍቁ ፤ ሁሌ እንደ ሙዚቃ

   እያዩ የሚያሽካኩ ፤ እንደ አዝናኝ ድለቃ

   ስንቱ ጉድ ተነግሮ ፤ ቢወራ አያበቃ፡፡

ታዲያ እነዚህን ፤ ጭካኔ የተሞሉ

ግእዛነ አእምሮ ፤ ሕሊና አልባ ሁሉ

ትንሽ ከርኅራኄ ፤ ቅንጣት ያልታደሉ

ግብረ-ገብነትን ፤ ጽድቅን የሚጠሉ

እንዴት ብየ ልመን ፤ ሰዎች ናቸው ሲሉ

ሰብአዊ መለያ ፤ ሳይዙ ቢምሉ

ከቶ እንዴት ይሆናል ፤ ነው ሌባ ለአመሉ

ውስጥ የሌላቸውን ፤ እንዲያው ሲያስመስሉ

ግን ሰውን ነው ጌታን ? ማንን ያታልላሉ?

   ራሔል ስታለቅስ ፤ ጩኸት ስታሰማ

   የሰቆቃ እንባዋን ፤ ያየኸው ከራማ

   ምን ነው ጨከንክብን ፤ ፍጹም ድምፅህ ጠፋ

   የረድኤት ክንድህ ፤ ርቆን ቀን ከፋ

   ሽ ራሔሎች ጮኸው ፤ ደም እያመነጩ

   ከዓይን ወደሰማይ ፤ ቀድተው እየረጩ

   አምላከ አበዊነ ፤ እግዚአብሔር አዶናይ

   በእውነት የለህማ ! አንተ በዚህ ሰማይ

   እያሉ አልጮሁም ? በሰቆቃ እንባ ?

   የገባኸውስ ቃል ? ሆነ እንዴ ቁብ አልባ ?

   የሰጠኸን ኪዳን ፤ ምን በላው የት ገባ ?

   አንተም ደሞ እንደሰው ፤ ቃልህን ታጥፋለህ ?

   ወይንስ ወዴት ሔድክ ፤ ምን በላህ ምን ዋጠህ ?

   እንደምን ያለ እንቅልፍ ፤ ያዘና ወሰደህ ?

   ማን ቀርቦ ይቀስቅስህ ፤ ማን ጎትጉቶ ያንቃህ ?

   አቅም አልባ ሆነናል ፤ ጽድቅ ርቋል ከኛ

   አንተኑ ለማንቃት ፤ እንድትሆነን ዳኛ

አንቂልና እመ አምላክ ፤ ቀስቅሽው ልጅሽን

የእናትነት ቁጣሽ ፤ ቶሎ ያሥነሣልን

ንቃሕ እግዚኦን ደግመሽ ፤ ለምንት ትነውም

በእግዚኦ ኩነኔከ ፤ እንዲሰጠን ሰላም

ስለ ዐሥራትነት ፤ ስላለሽ ቃል ኪዳን

ብለሽ አሳስቢልን ፤ ከልጅሽ አማልጅን

ፍረድ በይው ታደግ ፤ ሕዝቤን ከመከራ

በቀልህን ተበቀል ፤ ደማቸውን አጥራ

በይልን ጩሂልን ፤ አታስተኝ አደራ

ይሄው እንላለን ፤ እግዚኦ ቀን አብራ

ማረን ይቅር በለን ፤ ፍቅርህን አድሰው

ምንድን ነው ያስጨከነህ ? አንልም ለምን ነው ?

በደል ኃጢአታችንን ፤ በደንብ ስለምናውቀው

እንዳስተማርክ ሁሉ ፤ በቃልህ እንዳልከው

የምወደውን ነው ፤ እኔ የምቀጣው

አባቱ የማይቀጣው ፤ ልጅ የሆነ ማነው ?

ያለ ቅጣት ብትኖር ፤ ዲቃላ ነህ እንጅ

ከአብራክ የተከፈልክ ፤ አይደለህም ልጅ

ቅጣቱ ለጊዜው ፤ ደስ አያሰኝህም

ዳሩ ግን በኋላ ፤ ፍሬውን የሰላም

ያፈራላቹሀል ፤ ጽድቅን የዘለዓለም

ብለኸናልና ፤ ይሁን  እንዳንተ ፈቃድ

ግን ደሞ በቃ በል ፤ ምሕረትህን አውርድ

አፈፍ አርገህ አንሣን ፤ እግዚኦ ማረን ወልድ

መከራ የምታውቀው ፤ አንተ የኛ ዘመድ

ከዚህስ በኋላ ፤ ሌላ ዓይነት መከራ

ደሞ ሌላ ፍዳ ፤ ሌላ ሕይዎት መራራ

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

የሚሸከም ጉልበት ፤ የሚችል ትክሻ

የሚያስተናግድ ቅስም ፤ ስቃይ መታገሻ

ጨርሶ የለንም ፤ ደቂቃም ማማሻ

በዚሁ ይብቃ በለን ፤ ይሁን መጨረሻ

ትንሣኤያችንን አውጅ ፤ ይምጣ የኛ ድርሻ፡፡

ኅዳር 2006 ዓ.ም.

amsalugkidan@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. alem woldel says

    January 15, 2014 12:53 am at 12:53 am

    Amen! !!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule