• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በቃ! በለን አምላክ (say us enough! O’ God)

December 8, 2013 10:07 pm by Editor 1 Comment

ያ የምትወደው ፤ ያ የምታሞካሸው

ልጆቸና ሕዝቤ ፤ እያልክ ያከበርከው

መከራ አፈናቅሎት ፤ ከሀገሩ ከቀየው

ከአሕዛብ ደጅ ወድቆ ፤ ግፍ ሰቆቃ ቆላው፡፡

የጭንቅን ልክ ዓየ ፤ ሞት በዓይነት ቆጠረ

የሰቆቃን ጣራ ፤ ከፍ ብሎ በረረ

ሞትን ተላመደ ፤ ንቆም ተዳፈረ

በእሱ እየተበላ ፤ በእሱ ላይ ፎከረ

የአውሮችን አውሬነት ፤ ተበልቶ አጋለጠ

ድብቁን አወጣ ፤ ነፍሱን ለሀቅ ሰጠ፡፡

   ምን ዓይነት ፍጥረቶች ፤ ምን ዓይነት ጉዲራ

   እውን ሰዎች ናቸው ? የሆኑ የእጅህ ሥራ ?

   ወይስ ሰይጤ እንዳለው ፤ እኔ ነኝ ፈጣሪ

   ይሆኑ ይሆን የሱ ፤ የዚያ እርኩስ መሠሪ

   በሁለ ነገሩ ፤ እሱን አስመስሎ

   እንደራሱ አድርጎ ፤ ፈጥሯቸው አንቦልቡሎ ?

   ወይስ ከነገዱ ፤ ከሆኑት እንደሱ

   ሥጋ ለብሰው መጡ ? ሰው መስለው ሊያረክሱ

   ሕዝብህን በመቅጣት ፤ አንተን ለመበቀል

   ልጆች እንዳይኖሩህ ፤ ከርስትህ በመንቀል

   ካልሆነ እንዴት ታዲያ ፤ ሰው ሆነው የአዳም ዘር

   ሰብአዊ ሕሊና ፤ እንዴት አጡ ፍቅር ?

   ጥቂት ሐዘኔታ ፤ ሩኅሩኅ መሆን ገር

   እውን ከዚህ እርጉም ዘር ፤ ከእኩያን ልቡና

   ጽድቅ ይወጣል ብሎ ፤ ሰው ያምናል ሊቀና ?

   ካልሆነ የዋህ ጅል ፤ ዕውቀት የገደፈ

   በሥጋዊ ጥቅም ፤ ልቡ የተነደፈ

   የዝሙት ጥማቱን ፤ ሊያረካ የወደደ

   ያማሩትን ሁሉ ፤ መርጦ እያጠመደ

   በሴት ለመጫወት ፤ በአንድ ቤት አጉሮ

   አንጋግቶ ለመንዳት ፤ በእንስሳ ተፈጥሮ

   ሴት ሰው እንዳልሆነች ፤ እንደ እቃው ቆጥሮ

   የእሱ መጠቀሚያ ፤ ሆና የሱ ቋጠሮ

   የራሷን ፍላጎት ፤ አሳጥቶ ቀብሮ

   እሷም ልክ እንደሱ ፤ ሰው መሆኗ ቀርቶ

   እንደ ሰውነቷም ፤ እኩል መብቷን ነስቶ

   ጨቁኖ ለመግዛት ፤ ለመርገጥ አፍኖ

   የሚሻ ማስበርገግ ፤ እንደ ባሪያ አባክኖ

   ጾም ሳይልም ፍስክ ፤ ለመክተት ጮማ እርጎ

   በቅቤ እንቁላሉ ፤ ለመውዛት መግምጎ

   ገደብ ሳይኖርበት ፤ ለመድለብ ጠራርጎ

   ይሄን ይሄን ምቾት ፤ ኃጢአት ነው ሳይባል

   ማግኘት የፈለገ ፤ ራሱን የሚያታል

   ይሄ ዓይነት ተላላ ፤ አዎ እሱ ይሆናል ፡፡

   ታዲያ እሱ ምን ያርገው ፤ ከአውሬ ቢሆን አቻ

   ሆድ እንዲህ ሲሞላ ፤ ሲፈረጥም ጡንቻ

   ባዶ መሆኑ አይቀር ፤ ጭንቅላት ተራቁቶ

   ለማሰብ ተስኖት ፤ ሰብአዊነት አጥቶ

   ከእጁ የወደቁትን ፤ ከወልደ ሳጥናኤል

   በእስር ቤት አጉሮ ፤ በምድር ላይ ሲዖል

   ሕፃናት አልቀሩ ፤ አሮጊት ሕሙማን

   ሴቷ አልቀረች ወንዱ ፤ ደፍረው አረከሱን

   ብረት እያጋሉ ፤ በአፈ ማኅጸኗ

   በወንዱም ፊንጢጣ ፤ ወዮ ወዮ ቀኗ

   በዘይት መላጡ ፤ በፎቅ መወርወሩ

   የሰው ልጅ እንደ በግ ፤ በሰይፍ መመተሩ

   በረሀብና ጥም ፤ ሲሰቃይ በጠኔ

   ተሰዶ መግባቱ ፤ ሆኖበት ኩነኔ

   ብልቱን ሲቆርጡት ፤ ሲያስጓራው ሰቆቃ

   የስቃዩን ጩኸት ፤ የጣሩን ድምፅ ሲቃ

   መስማት የሚናፍቁ ፤ ሁሌ እንደ ሙዚቃ

   እያዩ የሚያሽካኩ ፤ እንደ አዝናኝ ድለቃ

   ስንቱ ጉድ ተነግሮ ፤ ቢወራ አያበቃ፡፡

ታዲያ እነዚህን ፤ ጭካኔ የተሞሉ

ግእዛነ አእምሮ ፤ ሕሊና አልባ ሁሉ

ትንሽ ከርኅራኄ ፤ ቅንጣት ያልታደሉ

ግብረ-ገብነትን ፤ ጽድቅን የሚጠሉ

እንዴት ብየ ልመን ፤ ሰዎች ናቸው ሲሉ

ሰብአዊ መለያ ፤ ሳይዙ ቢምሉ

ከቶ እንዴት ይሆናል ፤ ነው ሌባ ለአመሉ

ውስጥ የሌላቸውን ፤ እንዲያው ሲያስመስሉ

ግን ሰውን ነው ጌታን ? ማንን ያታልላሉ?

   ራሔል ስታለቅስ ፤ ጩኸት ስታሰማ

   የሰቆቃ እንባዋን ፤ ያየኸው ከራማ

   ምን ነው ጨከንክብን ፤ ፍጹም ድምፅህ ጠፋ

   የረድኤት ክንድህ ፤ ርቆን ቀን ከፋ

   ሽ ራሔሎች ጮኸው ፤ ደም እያመነጩ

   ከዓይን ወደሰማይ ፤ ቀድተው እየረጩ

   አምላከ አበዊነ ፤ እግዚአብሔር አዶናይ

   በእውነት የለህማ ! አንተ በዚህ ሰማይ

   እያሉ አልጮሁም ? በሰቆቃ እንባ ?

   የገባኸውስ ቃል ? ሆነ እንዴ ቁብ አልባ ?

   የሰጠኸን ኪዳን ፤ ምን በላው የት ገባ ?

   አንተም ደሞ እንደሰው ፤ ቃልህን ታጥፋለህ ?

   ወይንስ ወዴት ሔድክ ፤ ምን በላህ ምን ዋጠህ ?

   እንደምን ያለ እንቅልፍ ፤ ያዘና ወሰደህ ?

   ማን ቀርቦ ይቀስቅስህ ፤ ማን ጎትጉቶ ያንቃህ ?

   አቅም አልባ ሆነናል ፤ ጽድቅ ርቋል ከኛ

   አንተኑ ለማንቃት ፤ እንድትሆነን ዳኛ

አንቂልና እመ አምላክ ፤ ቀስቅሽው ልጅሽን

የእናትነት ቁጣሽ ፤ ቶሎ ያሥነሣልን

ንቃሕ እግዚኦን ደግመሽ ፤ ለምንት ትነውም

በእግዚኦ ኩነኔከ ፤ እንዲሰጠን ሰላም

ስለ ዐሥራትነት ፤ ስላለሽ ቃል ኪዳን

ብለሽ አሳስቢልን ፤ ከልጅሽ አማልጅን

ፍረድ በይው ታደግ ፤ ሕዝቤን ከመከራ

በቀልህን ተበቀል ፤ ደማቸውን አጥራ

በይልን ጩሂልን ፤ አታስተኝ አደራ

ይሄው እንላለን ፤ እግዚኦ ቀን አብራ

ማረን ይቅር በለን ፤ ፍቅርህን አድሰው

ምንድን ነው ያስጨከነህ ? አንልም ለምን ነው ?

በደል ኃጢአታችንን ፤ በደንብ ስለምናውቀው

እንዳስተማርክ ሁሉ ፤ በቃልህ እንዳልከው

የምወደውን ነው ፤ እኔ የምቀጣው

አባቱ የማይቀጣው ፤ ልጅ የሆነ ማነው ?

ያለ ቅጣት ብትኖር ፤ ዲቃላ ነህ እንጅ

ከአብራክ የተከፈልክ ፤ አይደለህም ልጅ

ቅጣቱ ለጊዜው ፤ ደስ አያሰኝህም

ዳሩ ግን በኋላ ፤ ፍሬውን የሰላም

ያፈራላቹሀል ፤ ጽድቅን የዘለዓለም

ብለኸናልና ፤ ይሁን  እንዳንተ ፈቃድ

ግን ደሞ በቃ በል ፤ ምሕረትህን አውርድ

አፈፍ አርገህ አንሣን ፤ እግዚኦ ማረን ወልድ

መከራ የምታውቀው ፤ አንተ የኛ ዘመድ

ከዚህስ በኋላ ፤ ሌላ ዓይነት መከራ

ደሞ ሌላ ፍዳ ፤ ሌላ ሕይዎት መራራ

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

የሚሸከም ጉልበት ፤ የሚችል ትክሻ

የሚያስተናግድ ቅስም ፤ ስቃይ መታገሻ

ጨርሶ የለንም ፤ ደቂቃም ማማሻ

በዚሁ ይብቃ በለን ፤ ይሁን መጨረሻ

ትንሣኤያችንን አውጅ ፤ ይምጣ የኛ ድርሻ፡፡

ኅዳር 2006 ዓ.ም.

amsalugkidan@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. alem woldel says

    January 15, 2014 12:53 am at 12:53 am

    Amen! !!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule