• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በቃ! በለን አምላክ (say us enough! O’ God)

December 8, 2013 10:07 pm by Editor 1 Comment

ያ የምትወደው ፤ ያ የምታሞካሸው

ልጆቸና ሕዝቤ ፤ እያልክ ያከበርከው

መከራ አፈናቅሎት ፤ ከሀገሩ ከቀየው

ከአሕዛብ ደጅ ወድቆ ፤ ግፍ ሰቆቃ ቆላው፡፡

የጭንቅን ልክ ዓየ ፤ ሞት በዓይነት ቆጠረ

የሰቆቃን ጣራ ፤ ከፍ ብሎ በረረ

ሞትን ተላመደ ፤ ንቆም ተዳፈረ

በእሱ እየተበላ ፤ በእሱ ላይ ፎከረ

የአውሮችን አውሬነት ፤ ተበልቶ አጋለጠ

ድብቁን አወጣ ፤ ነፍሱን ለሀቅ ሰጠ፡፡

   ምን ዓይነት ፍጥረቶች ፤ ምን ዓይነት ጉዲራ

   እውን ሰዎች ናቸው ? የሆኑ የእጅህ ሥራ ?

   ወይስ ሰይጤ እንዳለው ፤ እኔ ነኝ ፈጣሪ

   ይሆኑ ይሆን የሱ ፤ የዚያ እርኩስ መሠሪ

   በሁለ ነገሩ ፤ እሱን አስመስሎ

   እንደራሱ አድርጎ ፤ ፈጥሯቸው አንቦልቡሎ ?

   ወይስ ከነገዱ ፤ ከሆኑት እንደሱ

   ሥጋ ለብሰው መጡ ? ሰው መስለው ሊያረክሱ

   ሕዝብህን በመቅጣት ፤ አንተን ለመበቀል

   ልጆች እንዳይኖሩህ ፤ ከርስትህ በመንቀል

   ካልሆነ እንዴት ታዲያ ፤ ሰው ሆነው የአዳም ዘር

   ሰብአዊ ሕሊና ፤ እንዴት አጡ ፍቅር ?

   ጥቂት ሐዘኔታ ፤ ሩኅሩኅ መሆን ገር

   እውን ከዚህ እርጉም ዘር ፤ ከእኩያን ልቡና

   ጽድቅ ይወጣል ብሎ ፤ ሰው ያምናል ሊቀና ?

   ካልሆነ የዋህ ጅል ፤ ዕውቀት የገደፈ

   በሥጋዊ ጥቅም ፤ ልቡ የተነደፈ

   የዝሙት ጥማቱን ፤ ሊያረካ የወደደ

   ያማሩትን ሁሉ ፤ መርጦ እያጠመደ

   በሴት ለመጫወት ፤ በአንድ ቤት አጉሮ

   አንጋግቶ ለመንዳት ፤ በእንስሳ ተፈጥሮ

   ሴት ሰው እንዳልሆነች ፤ እንደ እቃው ቆጥሮ

   የእሱ መጠቀሚያ ፤ ሆና የሱ ቋጠሮ

   የራሷን ፍላጎት ፤ አሳጥቶ ቀብሮ

   እሷም ልክ እንደሱ ፤ ሰው መሆኗ ቀርቶ

   እንደ ሰውነቷም ፤ እኩል መብቷን ነስቶ

   ጨቁኖ ለመግዛት ፤ ለመርገጥ አፍኖ

   የሚሻ ማስበርገግ ፤ እንደ ባሪያ አባክኖ

   ጾም ሳይልም ፍስክ ፤ ለመክተት ጮማ እርጎ

   በቅቤ እንቁላሉ ፤ ለመውዛት መግምጎ

   ገደብ ሳይኖርበት ፤ ለመድለብ ጠራርጎ

   ይሄን ይሄን ምቾት ፤ ኃጢአት ነው ሳይባል

   ማግኘት የፈለገ ፤ ራሱን የሚያታል

   ይሄ ዓይነት ተላላ ፤ አዎ እሱ ይሆናል ፡፡

   ታዲያ እሱ ምን ያርገው ፤ ከአውሬ ቢሆን አቻ

   ሆድ እንዲህ ሲሞላ ፤ ሲፈረጥም ጡንቻ

   ባዶ መሆኑ አይቀር ፤ ጭንቅላት ተራቁቶ

   ለማሰብ ተስኖት ፤ ሰብአዊነት አጥቶ

   ከእጁ የወደቁትን ፤ ከወልደ ሳጥናኤል

   በእስር ቤት አጉሮ ፤ በምድር ላይ ሲዖል

   ሕፃናት አልቀሩ ፤ አሮጊት ሕሙማን

   ሴቷ አልቀረች ወንዱ ፤ ደፍረው አረከሱን

   ብረት እያጋሉ ፤ በአፈ ማኅጸኗ

   በወንዱም ፊንጢጣ ፤ ወዮ ወዮ ቀኗ

   በዘይት መላጡ ፤ በፎቅ መወርወሩ

   የሰው ልጅ እንደ በግ ፤ በሰይፍ መመተሩ

   በረሀብና ጥም ፤ ሲሰቃይ በጠኔ

   ተሰዶ መግባቱ ፤ ሆኖበት ኩነኔ

   ብልቱን ሲቆርጡት ፤ ሲያስጓራው ሰቆቃ

   የስቃዩን ጩኸት ፤ የጣሩን ድምፅ ሲቃ

   መስማት የሚናፍቁ ፤ ሁሌ እንደ ሙዚቃ

   እያዩ የሚያሽካኩ ፤ እንደ አዝናኝ ድለቃ

   ስንቱ ጉድ ተነግሮ ፤ ቢወራ አያበቃ፡፡

ታዲያ እነዚህን ፤ ጭካኔ የተሞሉ

ግእዛነ አእምሮ ፤ ሕሊና አልባ ሁሉ

ትንሽ ከርኅራኄ ፤ ቅንጣት ያልታደሉ

ግብረ-ገብነትን ፤ ጽድቅን የሚጠሉ

እንዴት ብየ ልመን ፤ ሰዎች ናቸው ሲሉ

ሰብአዊ መለያ ፤ ሳይዙ ቢምሉ

ከቶ እንዴት ይሆናል ፤ ነው ሌባ ለአመሉ

ውስጥ የሌላቸውን ፤ እንዲያው ሲያስመስሉ

ግን ሰውን ነው ጌታን ? ማንን ያታልላሉ?

   ራሔል ስታለቅስ ፤ ጩኸት ስታሰማ

   የሰቆቃ እንባዋን ፤ ያየኸው ከራማ

   ምን ነው ጨከንክብን ፤ ፍጹም ድምፅህ ጠፋ

   የረድኤት ክንድህ ፤ ርቆን ቀን ከፋ

   ሽ ራሔሎች ጮኸው ፤ ደም እያመነጩ

   ከዓይን ወደሰማይ ፤ ቀድተው እየረጩ

   አምላከ አበዊነ ፤ እግዚአብሔር አዶናይ

   በእውነት የለህማ ! አንተ በዚህ ሰማይ

   እያሉ አልጮሁም ? በሰቆቃ እንባ ?

   የገባኸውስ ቃል ? ሆነ እንዴ ቁብ አልባ ?

   የሰጠኸን ኪዳን ፤ ምን በላው የት ገባ ?

   አንተም ደሞ እንደሰው ፤ ቃልህን ታጥፋለህ ?

   ወይንስ ወዴት ሔድክ ፤ ምን በላህ ምን ዋጠህ ?

   እንደምን ያለ እንቅልፍ ፤ ያዘና ወሰደህ ?

   ማን ቀርቦ ይቀስቅስህ ፤ ማን ጎትጉቶ ያንቃህ ?

   አቅም አልባ ሆነናል ፤ ጽድቅ ርቋል ከኛ

   አንተኑ ለማንቃት ፤ እንድትሆነን ዳኛ

አንቂልና እመ አምላክ ፤ ቀስቅሽው ልጅሽን

የእናትነት ቁጣሽ ፤ ቶሎ ያሥነሣልን

ንቃሕ እግዚኦን ደግመሽ ፤ ለምንት ትነውም

በእግዚኦ ኩነኔከ ፤ እንዲሰጠን ሰላም

ስለ ዐሥራትነት ፤ ስላለሽ ቃል ኪዳን

ብለሽ አሳስቢልን ፤ ከልጅሽ አማልጅን

ፍረድ በይው ታደግ ፤ ሕዝቤን ከመከራ

በቀልህን ተበቀል ፤ ደማቸውን አጥራ

በይልን ጩሂልን ፤ አታስተኝ አደራ

ይሄው እንላለን ፤ እግዚኦ ቀን አብራ

ማረን ይቅር በለን ፤ ፍቅርህን አድሰው

ምንድን ነው ያስጨከነህ ? አንልም ለምን ነው ?

በደል ኃጢአታችንን ፤ በደንብ ስለምናውቀው

እንዳስተማርክ ሁሉ ፤ በቃልህ እንዳልከው

የምወደውን ነው ፤ እኔ የምቀጣው

አባቱ የማይቀጣው ፤ ልጅ የሆነ ማነው ?

ያለ ቅጣት ብትኖር ፤ ዲቃላ ነህ እንጅ

ከአብራክ የተከፈልክ ፤ አይደለህም ልጅ

ቅጣቱ ለጊዜው ፤ ደስ አያሰኝህም

ዳሩ ግን በኋላ ፤ ፍሬውን የሰላም

ያፈራላቹሀል ፤ ጽድቅን የዘለዓለም

ብለኸናልና ፤ ይሁን  እንዳንተ ፈቃድ

ግን ደሞ በቃ በል ፤ ምሕረትህን አውርድ

አፈፍ አርገህ አንሣን ፤ እግዚኦ ማረን ወልድ

መከራ የምታውቀው ፤ አንተ የኛ ዘመድ

ከዚህስ በኋላ ፤ ሌላ ዓይነት መከራ

ደሞ ሌላ ፍዳ ፤ ሌላ ሕይዎት መራራ

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

የሚሸከም ጉልበት ፤ የሚችል ትክሻ

የሚያስተናግድ ቅስም ፤ ስቃይ መታገሻ

ጨርሶ የለንም ፤ ደቂቃም ማማሻ

በዚሁ ይብቃ በለን ፤ ይሁን መጨረሻ

ትንሣኤያችንን አውጅ ፤ ይምጣ የኛ ድርሻ፡፡

ኅዳር 2006 ዓ.ም.

amsalugkidan@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. alem woldel says

    January 15, 2014 12:53 am at 12:53 am

    Amen! !!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule