• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በቃ! በለን አምላክ (say us enough! O’ God)

December 8, 2013 10:07 pm by Editor 1 Comment

ያ የምትወደው ፤ ያ የምታሞካሸው

ልጆቸና ሕዝቤ ፤ እያልክ ያከበርከው

መከራ አፈናቅሎት ፤ ከሀገሩ ከቀየው

ከአሕዛብ ደጅ ወድቆ ፤ ግፍ ሰቆቃ ቆላው፡፡

የጭንቅን ልክ ዓየ ፤ ሞት በዓይነት ቆጠረ

የሰቆቃን ጣራ ፤ ከፍ ብሎ በረረ

ሞትን ተላመደ ፤ ንቆም ተዳፈረ

በእሱ እየተበላ ፤ በእሱ ላይ ፎከረ

የአውሮችን አውሬነት ፤ ተበልቶ አጋለጠ

ድብቁን አወጣ ፤ ነፍሱን ለሀቅ ሰጠ፡፡

   ምን ዓይነት ፍጥረቶች ፤ ምን ዓይነት ጉዲራ

   እውን ሰዎች ናቸው ? የሆኑ የእጅህ ሥራ ?

   ወይስ ሰይጤ እንዳለው ፤ እኔ ነኝ ፈጣሪ

   ይሆኑ ይሆን የሱ ፤ የዚያ እርኩስ መሠሪ

   በሁለ ነገሩ ፤ እሱን አስመስሎ

   እንደራሱ አድርጎ ፤ ፈጥሯቸው አንቦልቡሎ ?

   ወይስ ከነገዱ ፤ ከሆኑት እንደሱ

   ሥጋ ለብሰው መጡ ? ሰው መስለው ሊያረክሱ

   ሕዝብህን በመቅጣት ፤ አንተን ለመበቀል

   ልጆች እንዳይኖሩህ ፤ ከርስትህ በመንቀል

   ካልሆነ እንዴት ታዲያ ፤ ሰው ሆነው የአዳም ዘር

   ሰብአዊ ሕሊና ፤ እንዴት አጡ ፍቅር ?

   ጥቂት ሐዘኔታ ፤ ሩኅሩኅ መሆን ገር

   እውን ከዚህ እርጉም ዘር ፤ ከእኩያን ልቡና

   ጽድቅ ይወጣል ብሎ ፤ ሰው ያምናል ሊቀና ?

   ካልሆነ የዋህ ጅል ፤ ዕውቀት የገደፈ

   በሥጋዊ ጥቅም ፤ ልቡ የተነደፈ

   የዝሙት ጥማቱን ፤ ሊያረካ የወደደ

   ያማሩትን ሁሉ ፤ መርጦ እያጠመደ

   በሴት ለመጫወት ፤ በአንድ ቤት አጉሮ

   አንጋግቶ ለመንዳት ፤ በእንስሳ ተፈጥሮ

   ሴት ሰው እንዳልሆነች ፤ እንደ እቃው ቆጥሮ

   የእሱ መጠቀሚያ ፤ ሆና የሱ ቋጠሮ

   የራሷን ፍላጎት ፤ አሳጥቶ ቀብሮ

   እሷም ልክ እንደሱ ፤ ሰው መሆኗ ቀርቶ

   እንደ ሰውነቷም ፤ እኩል መብቷን ነስቶ

   ጨቁኖ ለመግዛት ፤ ለመርገጥ አፍኖ

   የሚሻ ማስበርገግ ፤ እንደ ባሪያ አባክኖ

   ጾም ሳይልም ፍስክ ፤ ለመክተት ጮማ እርጎ

   በቅቤ እንቁላሉ ፤ ለመውዛት መግምጎ

   ገደብ ሳይኖርበት ፤ ለመድለብ ጠራርጎ

   ይሄን ይሄን ምቾት ፤ ኃጢአት ነው ሳይባል

   ማግኘት የፈለገ ፤ ራሱን የሚያታል

   ይሄ ዓይነት ተላላ ፤ አዎ እሱ ይሆናል ፡፡

   ታዲያ እሱ ምን ያርገው ፤ ከአውሬ ቢሆን አቻ

   ሆድ እንዲህ ሲሞላ ፤ ሲፈረጥም ጡንቻ

   ባዶ መሆኑ አይቀር ፤ ጭንቅላት ተራቁቶ

   ለማሰብ ተስኖት ፤ ሰብአዊነት አጥቶ

   ከእጁ የወደቁትን ፤ ከወልደ ሳጥናኤል

   በእስር ቤት አጉሮ ፤ በምድር ላይ ሲዖል

   ሕፃናት አልቀሩ ፤ አሮጊት ሕሙማን

   ሴቷ አልቀረች ወንዱ ፤ ደፍረው አረከሱን

   ብረት እያጋሉ ፤ በአፈ ማኅጸኗ

   በወንዱም ፊንጢጣ ፤ ወዮ ወዮ ቀኗ

   በዘይት መላጡ ፤ በፎቅ መወርወሩ

   የሰው ልጅ እንደ በግ ፤ በሰይፍ መመተሩ

   በረሀብና ጥም ፤ ሲሰቃይ በጠኔ

   ተሰዶ መግባቱ ፤ ሆኖበት ኩነኔ

   ብልቱን ሲቆርጡት ፤ ሲያስጓራው ሰቆቃ

   የስቃዩን ጩኸት ፤ የጣሩን ድምፅ ሲቃ

   መስማት የሚናፍቁ ፤ ሁሌ እንደ ሙዚቃ

   እያዩ የሚያሽካኩ ፤ እንደ አዝናኝ ድለቃ

   ስንቱ ጉድ ተነግሮ ፤ ቢወራ አያበቃ፡፡

ታዲያ እነዚህን ፤ ጭካኔ የተሞሉ

ግእዛነ አእምሮ ፤ ሕሊና አልባ ሁሉ

ትንሽ ከርኅራኄ ፤ ቅንጣት ያልታደሉ

ግብረ-ገብነትን ፤ ጽድቅን የሚጠሉ

እንዴት ብየ ልመን ፤ ሰዎች ናቸው ሲሉ

ሰብአዊ መለያ ፤ ሳይዙ ቢምሉ

ከቶ እንዴት ይሆናል ፤ ነው ሌባ ለአመሉ

ውስጥ የሌላቸውን ፤ እንዲያው ሲያስመስሉ

ግን ሰውን ነው ጌታን ? ማንን ያታልላሉ?

   ራሔል ስታለቅስ ፤ ጩኸት ስታሰማ

   የሰቆቃ እንባዋን ፤ ያየኸው ከራማ

   ምን ነው ጨከንክብን ፤ ፍጹም ድምፅህ ጠፋ

   የረድኤት ክንድህ ፤ ርቆን ቀን ከፋ

   ሽ ራሔሎች ጮኸው ፤ ደም እያመነጩ

   ከዓይን ወደሰማይ ፤ ቀድተው እየረጩ

   አምላከ አበዊነ ፤ እግዚአብሔር አዶናይ

   በእውነት የለህማ ! አንተ በዚህ ሰማይ

   እያሉ አልጮሁም ? በሰቆቃ እንባ ?

   የገባኸውስ ቃል ? ሆነ እንዴ ቁብ አልባ ?

   የሰጠኸን ኪዳን ፤ ምን በላው የት ገባ ?

   አንተም ደሞ እንደሰው ፤ ቃልህን ታጥፋለህ ?

   ወይንስ ወዴት ሔድክ ፤ ምን በላህ ምን ዋጠህ ?

   እንደምን ያለ እንቅልፍ ፤ ያዘና ወሰደህ ?

   ማን ቀርቦ ይቀስቅስህ ፤ ማን ጎትጉቶ ያንቃህ ?

   አቅም አልባ ሆነናል ፤ ጽድቅ ርቋል ከኛ

   አንተኑ ለማንቃት ፤ እንድትሆነን ዳኛ

አንቂልና እመ አምላክ ፤ ቀስቅሽው ልጅሽን

የእናትነት ቁጣሽ ፤ ቶሎ ያሥነሣልን

ንቃሕ እግዚኦን ደግመሽ ፤ ለምንት ትነውም

በእግዚኦ ኩነኔከ ፤ እንዲሰጠን ሰላም

ስለ ዐሥራትነት ፤ ስላለሽ ቃል ኪዳን

ብለሽ አሳስቢልን ፤ ከልጅሽ አማልጅን

ፍረድ በይው ታደግ ፤ ሕዝቤን ከመከራ

በቀልህን ተበቀል ፤ ደማቸውን አጥራ

በይልን ጩሂልን ፤ አታስተኝ አደራ

ይሄው እንላለን ፤ እግዚኦ ቀን አብራ

ማረን ይቅር በለን ፤ ፍቅርህን አድሰው

ምንድን ነው ያስጨከነህ ? አንልም ለምን ነው ?

በደል ኃጢአታችንን ፤ በደንብ ስለምናውቀው

እንዳስተማርክ ሁሉ ፤ በቃልህ እንዳልከው

የምወደውን ነው ፤ እኔ የምቀጣው

አባቱ የማይቀጣው ፤ ልጅ የሆነ ማነው ?

ያለ ቅጣት ብትኖር ፤ ዲቃላ ነህ እንጅ

ከአብራክ የተከፈልክ ፤ አይደለህም ልጅ

ቅጣቱ ለጊዜው ፤ ደስ አያሰኝህም

ዳሩ ግን በኋላ ፤ ፍሬውን የሰላም

ያፈራላቹሀል ፤ ጽድቅን የዘለዓለም

ብለኸናልና ፤ ይሁን  እንዳንተ ፈቃድ

ግን ደሞ በቃ በል ፤ ምሕረትህን አውርድ

አፈፍ አርገህ አንሣን ፤ እግዚኦ ማረን ወልድ

መከራ የምታውቀው ፤ አንተ የኛ ዘመድ

ከዚህስ በኋላ ፤ ሌላ ዓይነት መከራ

ደሞ ሌላ ፍዳ ፤ ሌላ ሕይዎት መራራ

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

የሚሸከም ጉልበት ፤ የሚችል ትክሻ

የሚያስተናግድ ቅስም ፤ ስቃይ መታገሻ

ጨርሶ የለንም ፤ ደቂቃም ማማሻ

በዚሁ ይብቃ በለን ፤ ይሁን መጨረሻ

ትንሣኤያችንን አውጅ ፤ ይምጣ የኛ ድርሻ፡፡

ኅዳር 2006 ዓ.ም.

amsalugkidan@gmail.com

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. alem woldel says

    January 15, 2014 12:53 am at 12:53 am

    Amen! !!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
Copyright © 2026 · Goolgule