• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ክደራና ክየና

August 21, 2014 02:24 am by Editor 1 Comment

አንድ ብልጣብልጥ ባለተራ ፤ ከያኔ ነኝ የሚል ጽፎ

በእሱ ቤት የማላውቅበት ፤ መከደሩን ለንብ ቀፎ

በየሔደበት ያወራል ፤ ጸሐፊያንን ነቃቅፎ

ጋዜጣ መጽሔት ድረ ገጽ ፤ ወደዛ! እያለ ተጸይፎ

አታንብቡ አትስሟቸው ፤ ብሎ ያርቃል አንባቢ

የጌቶቹ ጉድ እንዳይወጣ ፤ እንዳይገለጥ ሸባቢ

እንዴት ምን ነካህ? ለሚሉት ፤ ተገርመው በጭፍን ትችቱ

ችግር መኖሩ መች ጠፋን  ? ይሄ ሀገር የሚሻው በብርቱ

መፍትሔውን ቢነግሩን ነው ፤ ይላል ልሳኑን አስልቶ

መፍትሔው እንዳልተጻፈ ፤ ከችግሮቹ ጋር ጎልቶ፡፡

ይሄው አይደሉ እነሱ? ማደናቆር መተጣጠፍ

ምን እነግራለሁ ለእናንተ ፤ ታውቋቸው የለ ከወደአፍ?

በዐይን የሚታየው በጉልህ ፤ የሚጨበጠው ተይዞ

ካሳበቃቸው ጭራሽ የለም ፤ በቃ የለማ ማን አዞ?

የማይታየው የሌለው ፤ ምናባዊውን ሕልም እንጀራ

ብሉ ጠጡ ጥገቡ ነው ፤ እንዲሁ በባዶ ጉራ

እንዴ! እንዴት ሆኖ? አትሉም ፤ በቃ ይሄ ነዋ ክደራ፡፡

ግድ የለም ይሁን ወዳጀ ፤ ዐይኔ ዐላየም ካልክ መፍትሔ

ተጽፏል ብለህ ያመንከው ፤ ችግሮች ተብሎ ያ ይሄ

ችግርን ማወቅ መረዳት ፤ ያገር ሀብት ከንቱ የሚያስፈጅ

ግማሽ መፍትሔ ነው እንዲሉ ፤ ምዕራባዊያን ሥልጡን ፈረንጅ

ችግሮችህን መንገሩ ፤ ጸሐፊው ውዱን የሀገር ልጅ

ይገባሀል እንጂ ማመስገን ፤ አደግድገህ በመንሣት እጅ

እኮ በል እንዴት ሆኖ ነው? በአንተ ዝርው አፍ በገፈጅ

የሚነቀፍ የሚኮነነው ፤ መስታውቱ ጉድፍ አስወጋጅ ፡፡

የሌለውን አለ ሳልል ፤ ያለውን ግን አውጥቸ

ከነ መፍትሔ መላውም ፤ ጽፌልሐለው አጥርቸ

እኮ በል ልይህ ስትሔደው ፤ በአልኩህ መንገድ ማምለጫ

መፍትሔም አላልክ መድኃኒት? ከችጋር ግፍ አሳር መውጫ

እኮ በል ልይህ አድርገው? ያው እኮ ነገርኩህ ጩሄ

ግፈኞቹ የተውልህን ፤ የቀረህ ብቸኛ መፍትሔ

ደፋኸውሳ አንገትህን ፤ አሄሄ አሄሄ አሄሄ!

ተነቃቅተናል ወዳጀ ፤ ዝም ብለህ ልቀም ከበርሔ

ቡሌ ፍርፋሪህን ፤ የኩሊነትክን ድርሻ

ምን ማዕረግ አለውና ፤ ከዚህ በላይ የደጅ ውሻ?

ከዚያ ውጭ መፍትሔ ካለህ ፤ የሚሆን ያልተሞከረ

በላ ንገረን እንስማው ? ሳንሔድበት የቀረ፡፡

ግን እባክህን ወዳጀ ፤ የምለምንህ በብዙ

ከያኔ ነኝ አትበለን ፤ ቃናውም የለህ ወዙ

እናት ኪነትን ጠይቄያት ፤ ልጅ እንዳላት ብየ እንዳንተ

ኅሊናውን ለሆድ ሸጦ ፤ ቡሌ የሚለቅም የሳተ

እውነትን የሚረጋግጥ ፤ የግፈኛ አገልጋይ ሎሌ

የሞራል(የቅስም) እሴት የሌለው ፤ የማንም ምናምን ኩሊ

ልጀ አይደለም አላውቀውም ፤ እናቴ አይበለኝ አደራ

አደራ አደራ አደራ ፤ ቁጣየ እጅግ ነው መራራ

የእኔ ልጆቸ የታወቁ ፤ የእውነት ጠበቃ ለሐቅ ያደሩ

ኅሊናቸውን አክባሪ ፤ በሕዝብ በሀገር አይቆምሩ

ከዚህች ፈቀቅ የማይሉ ፤ ሞት እንኳን ቢሆን የማይፈሩ

ግፈኞችን ሳይዋጋ ፤ የሰላ ብዕሩን ወድሮ

መራሩን ዋጋ ሳይከፍል ፤ ለእውነት ሲል ወህኒ ተወርውሮ

ወህኒም ባይወርድ ባይጋዝ ፤ ፊት ሳይነፈግ ተገዳድሮ

የግፉአን ልሳን ሆኖ ፤ ለፍትሕ ለእውነት አብሮ

ይሄን ሳያደርግ ሳይተጋ ፤ መንፈሱን እራሱ ሰብሮ

የጨለማው ዓለም መብራቷ ፤ እንደ ድቅድቅ ጨላማ ጠቁሮ

ህዋሳቱን አደንዝዞ ፤ አእምሮውን አደንቁሮ

የጥፋት ኃይሎች ኃይል ሆኖ ፤ የሕዝብን እውነት ቀብሮ

ድንቄም ከያኔ የእኔም ልጅ ፤ የማን ነው ጭንጋፍ ቀበሮ?

ሕዝብና ሀገርን ከድቶ ፤ የእውነት ቀባሪ መደዴ

ይሄ ከያኔ አይደለም ፤ ነው ለሆዱ ያደረ ነጋዴ

ምንም ነገር እንደማያውቁት ፤ ያለሆዳቸው ምንዳ

ወደ እንስሳነት የተቀየረ ፤ ለምን? እንዴት? አይል ዱዳ

ብላሀለችና እናት ኪነት ፤ ደፍረህ ሳታፍር ሳተፈራ

ገጣሚ ደራሲ ሠዓሊ ፤ ተዋናይ ተጫዋች ዳንኪራ

ኪነት የነፍሴ ጥሪ ፤ ብለህ መስሟ እንዳትጠራ!!!

የፈለገኝ ሊያየኝ የሻ ፤ ምንጊዜን ቢሆን አድራሻየ

ከሕዝብ ከእውነት ጋራ ነው ፤ የእኔ መኖሪያ ቦታየ

የተፈጠርኩበት ዓላማ ፤ ሥራና ተግባር ሞያየ

ቃልኪዳኑን ሲያስርልኝ ፤ የጥበብ አምላክ ጌታየ

ሕይዎትን ቀና ማድረግ ነው ፤ ችግር ግፍ አሳር ታግየ

እንጅ ሕይዎትን ለማምረር ፤ አይደለም ለአውሬ ደልየ

ልብ  ያለው ሁሉ ልብ ይበል ፤ ጽኑ ነውና መሐላየ፡፡

ብላለችና ጥበብ ኪነት ፤ መልእክቱ ይድረስ ለሁሉ

የሳተ ቶሎ ይመለስ ፤ ይቅር ይባላል በደሉ፡፡

ነሐሴ 1 2006 ዓ.ም.

መታሰቢያነቷ ለልማታዊ ……በሚሉ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. speaker says

    August 23, 2014 05:20 pm at 5:20 pm

    I am crying.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule