• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ክደራና ክየና

August 21, 2014 02:24 am by Editor 1 Comment

አንድ ብልጣብልጥ ባለተራ ፤ ከያኔ ነኝ የሚል ጽፎ

በእሱ ቤት የማላውቅበት ፤ መከደሩን ለንብ ቀፎ

በየሔደበት ያወራል ፤ ጸሐፊያንን ነቃቅፎ

ጋዜጣ መጽሔት ድረ ገጽ ፤ ወደዛ! እያለ ተጸይፎ

አታንብቡ አትስሟቸው ፤ ብሎ ያርቃል አንባቢ

የጌቶቹ ጉድ እንዳይወጣ ፤ እንዳይገለጥ ሸባቢ

እንዴት ምን ነካህ? ለሚሉት ፤ ተገርመው በጭፍን ትችቱ

ችግር መኖሩ መች ጠፋን  ? ይሄ ሀገር የሚሻው በብርቱ

መፍትሔውን ቢነግሩን ነው ፤ ይላል ልሳኑን አስልቶ

መፍትሔው እንዳልተጻፈ ፤ ከችግሮቹ ጋር ጎልቶ፡፡

ይሄው አይደሉ እነሱ? ማደናቆር መተጣጠፍ

ምን እነግራለሁ ለእናንተ ፤ ታውቋቸው የለ ከወደአፍ?

በዐይን የሚታየው በጉልህ ፤ የሚጨበጠው ተይዞ

ካሳበቃቸው ጭራሽ የለም ፤ በቃ የለማ ማን አዞ?

የማይታየው የሌለው ፤ ምናባዊውን ሕልም እንጀራ

ብሉ ጠጡ ጥገቡ ነው ፤ እንዲሁ በባዶ ጉራ

እንዴ! እንዴት ሆኖ? አትሉም ፤ በቃ ይሄ ነዋ ክደራ፡፡

ግድ የለም ይሁን ወዳጀ ፤ ዐይኔ ዐላየም ካልክ መፍትሔ

ተጽፏል ብለህ ያመንከው ፤ ችግሮች ተብሎ ያ ይሄ

ችግርን ማወቅ መረዳት ፤ ያገር ሀብት ከንቱ የሚያስፈጅ

ግማሽ መፍትሔ ነው እንዲሉ ፤ ምዕራባዊያን ሥልጡን ፈረንጅ

ችግሮችህን መንገሩ ፤ ጸሐፊው ውዱን የሀገር ልጅ

ይገባሀል እንጂ ማመስገን ፤ አደግድገህ በመንሣት እጅ

እኮ በል እንዴት ሆኖ ነው? በአንተ ዝርው አፍ በገፈጅ

የሚነቀፍ የሚኮነነው ፤ መስታውቱ ጉድፍ አስወጋጅ ፡፡

የሌለውን አለ ሳልል ፤ ያለውን ግን አውጥቸ

ከነ መፍትሔ መላውም ፤ ጽፌልሐለው አጥርቸ

እኮ በል ልይህ ስትሔደው ፤ በአልኩህ መንገድ ማምለጫ

መፍትሔም አላልክ መድኃኒት? ከችጋር ግፍ አሳር መውጫ

እኮ በል ልይህ አድርገው? ያው እኮ ነገርኩህ ጩሄ

ግፈኞቹ የተውልህን ፤ የቀረህ ብቸኛ መፍትሔ

ደፋኸውሳ አንገትህን ፤ አሄሄ አሄሄ አሄሄ!

ተነቃቅተናል ወዳጀ ፤ ዝም ብለህ ልቀም ከበርሔ

ቡሌ ፍርፋሪህን ፤ የኩሊነትክን ድርሻ

ምን ማዕረግ አለውና ፤ ከዚህ በላይ የደጅ ውሻ?

ከዚያ ውጭ መፍትሔ ካለህ ፤ የሚሆን ያልተሞከረ

በላ ንገረን እንስማው ? ሳንሔድበት የቀረ፡፡

ግን እባክህን ወዳጀ ፤ የምለምንህ በብዙ

ከያኔ ነኝ አትበለን ፤ ቃናውም የለህ ወዙ

እናት ኪነትን ጠይቄያት ፤ ልጅ እንዳላት ብየ እንዳንተ

ኅሊናውን ለሆድ ሸጦ ፤ ቡሌ የሚለቅም የሳተ

እውነትን የሚረጋግጥ ፤ የግፈኛ አገልጋይ ሎሌ

የሞራል(የቅስም) እሴት የሌለው ፤ የማንም ምናምን ኩሊ

ልጀ አይደለም አላውቀውም ፤ እናቴ አይበለኝ አደራ

አደራ አደራ አደራ ፤ ቁጣየ እጅግ ነው መራራ

የእኔ ልጆቸ የታወቁ ፤ የእውነት ጠበቃ ለሐቅ ያደሩ

ኅሊናቸውን አክባሪ ፤ በሕዝብ በሀገር አይቆምሩ

ከዚህች ፈቀቅ የማይሉ ፤ ሞት እንኳን ቢሆን የማይፈሩ

ግፈኞችን ሳይዋጋ ፤ የሰላ ብዕሩን ወድሮ

መራሩን ዋጋ ሳይከፍል ፤ ለእውነት ሲል ወህኒ ተወርውሮ

ወህኒም ባይወርድ ባይጋዝ ፤ ፊት ሳይነፈግ ተገዳድሮ

የግፉአን ልሳን ሆኖ ፤ ለፍትሕ ለእውነት አብሮ

ይሄን ሳያደርግ ሳይተጋ ፤ መንፈሱን እራሱ ሰብሮ

የጨለማው ዓለም መብራቷ ፤ እንደ ድቅድቅ ጨላማ ጠቁሮ

ህዋሳቱን አደንዝዞ ፤ አእምሮውን አደንቁሮ

የጥፋት ኃይሎች ኃይል ሆኖ ፤ የሕዝብን እውነት ቀብሮ

ድንቄም ከያኔ የእኔም ልጅ ፤ የማን ነው ጭንጋፍ ቀበሮ?

ሕዝብና ሀገርን ከድቶ ፤ የእውነት ቀባሪ መደዴ

ይሄ ከያኔ አይደለም ፤ ነው ለሆዱ ያደረ ነጋዴ

ምንም ነገር እንደማያውቁት ፤ ያለሆዳቸው ምንዳ

ወደ እንስሳነት የተቀየረ ፤ ለምን? እንዴት? አይል ዱዳ

ብላሀለችና እናት ኪነት ፤ ደፍረህ ሳታፍር ሳተፈራ

ገጣሚ ደራሲ ሠዓሊ ፤ ተዋናይ ተጫዋች ዳንኪራ

ኪነት የነፍሴ ጥሪ ፤ ብለህ መስሟ እንዳትጠራ!!!

የፈለገኝ ሊያየኝ የሻ ፤ ምንጊዜን ቢሆን አድራሻየ

ከሕዝብ ከእውነት ጋራ ነው ፤ የእኔ መኖሪያ ቦታየ

የተፈጠርኩበት ዓላማ ፤ ሥራና ተግባር ሞያየ

ቃልኪዳኑን ሲያስርልኝ ፤ የጥበብ አምላክ ጌታየ

ሕይዎትን ቀና ማድረግ ነው ፤ ችግር ግፍ አሳር ታግየ

እንጅ ሕይዎትን ለማምረር ፤ አይደለም ለአውሬ ደልየ

ልብ  ያለው ሁሉ ልብ ይበል ፤ ጽኑ ነውና መሐላየ፡፡

ብላለችና ጥበብ ኪነት ፤ መልእክቱ ይድረስ ለሁሉ

የሳተ ቶሎ ይመለስ ፤ ይቅር ይባላል በደሉ፡፡

ነሐሴ 1 2006 ዓ.ም.

መታሰቢያነቷ ለልማታዊ ……በሚሉ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. speaker says

    August 23, 2014 05:20 pm at 5:20 pm

    I am crying.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule