• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ክደራና ክየና

August 21, 2014 02:24 am by Editor 1 Comment

አንድ ብልጣብልጥ ባለተራ ፤ ከያኔ ነኝ የሚል ጽፎ

በእሱ ቤት የማላውቅበት ፤ መከደሩን ለንብ ቀፎ

በየሔደበት ያወራል ፤ ጸሐፊያንን ነቃቅፎ

ጋዜጣ መጽሔት ድረ ገጽ ፤ ወደዛ! እያለ ተጸይፎ

አታንብቡ አትስሟቸው ፤ ብሎ ያርቃል አንባቢ

የጌቶቹ ጉድ እንዳይወጣ ፤ እንዳይገለጥ ሸባቢ

እንዴት ምን ነካህ? ለሚሉት ፤ ተገርመው በጭፍን ትችቱ

ችግር መኖሩ መች ጠፋን  ? ይሄ ሀገር የሚሻው በብርቱ

መፍትሔውን ቢነግሩን ነው ፤ ይላል ልሳኑን አስልቶ

መፍትሔው እንዳልተጻፈ ፤ ከችግሮቹ ጋር ጎልቶ፡፡

ይሄው አይደሉ እነሱ? ማደናቆር መተጣጠፍ

ምን እነግራለሁ ለእናንተ ፤ ታውቋቸው የለ ከወደአፍ?

በዐይን የሚታየው በጉልህ ፤ የሚጨበጠው ተይዞ

ካሳበቃቸው ጭራሽ የለም ፤ በቃ የለማ ማን አዞ?

የማይታየው የሌለው ፤ ምናባዊውን ሕልም እንጀራ

ብሉ ጠጡ ጥገቡ ነው ፤ እንዲሁ በባዶ ጉራ

እንዴ! እንዴት ሆኖ? አትሉም ፤ በቃ ይሄ ነዋ ክደራ፡፡

ግድ የለም ይሁን ወዳጀ ፤ ዐይኔ ዐላየም ካልክ መፍትሔ

ተጽፏል ብለህ ያመንከው ፤ ችግሮች ተብሎ ያ ይሄ

ችግርን ማወቅ መረዳት ፤ ያገር ሀብት ከንቱ የሚያስፈጅ

ግማሽ መፍትሔ ነው እንዲሉ ፤ ምዕራባዊያን ሥልጡን ፈረንጅ

ችግሮችህን መንገሩ ፤ ጸሐፊው ውዱን የሀገር ልጅ

ይገባሀል እንጂ ማመስገን ፤ አደግድገህ በመንሣት እጅ

እኮ በል እንዴት ሆኖ ነው? በአንተ ዝርው አፍ በገፈጅ

የሚነቀፍ የሚኮነነው ፤ መስታውቱ ጉድፍ አስወጋጅ ፡፡

የሌለውን አለ ሳልል ፤ ያለውን ግን አውጥቸ

ከነ መፍትሔ መላውም ፤ ጽፌልሐለው አጥርቸ

እኮ በል ልይህ ስትሔደው ፤ በአልኩህ መንገድ ማምለጫ

መፍትሔም አላልክ መድኃኒት? ከችጋር ግፍ አሳር መውጫ

እኮ በል ልይህ አድርገው? ያው እኮ ነገርኩህ ጩሄ

ግፈኞቹ የተውልህን ፤ የቀረህ ብቸኛ መፍትሔ

ደፋኸውሳ አንገትህን ፤ አሄሄ አሄሄ አሄሄ!

ተነቃቅተናል ወዳጀ ፤ ዝም ብለህ ልቀም ከበርሔ

ቡሌ ፍርፋሪህን ፤ የኩሊነትክን ድርሻ

ምን ማዕረግ አለውና ፤ ከዚህ በላይ የደጅ ውሻ?

ከዚያ ውጭ መፍትሔ ካለህ ፤ የሚሆን ያልተሞከረ

በላ ንገረን እንስማው ? ሳንሔድበት የቀረ፡፡

ግን እባክህን ወዳጀ ፤ የምለምንህ በብዙ

ከያኔ ነኝ አትበለን ፤ ቃናውም የለህ ወዙ

እናት ኪነትን ጠይቄያት ፤ ልጅ እንዳላት ብየ እንዳንተ

ኅሊናውን ለሆድ ሸጦ ፤ ቡሌ የሚለቅም የሳተ

እውነትን የሚረጋግጥ ፤ የግፈኛ አገልጋይ ሎሌ

የሞራል(የቅስም) እሴት የሌለው ፤ የማንም ምናምን ኩሊ

ልጀ አይደለም አላውቀውም ፤ እናቴ አይበለኝ አደራ

አደራ አደራ አደራ ፤ ቁጣየ እጅግ ነው መራራ

የእኔ ልጆቸ የታወቁ ፤ የእውነት ጠበቃ ለሐቅ ያደሩ

ኅሊናቸውን አክባሪ ፤ በሕዝብ በሀገር አይቆምሩ

ከዚህች ፈቀቅ የማይሉ ፤ ሞት እንኳን ቢሆን የማይፈሩ

ግፈኞችን ሳይዋጋ ፤ የሰላ ብዕሩን ወድሮ

መራሩን ዋጋ ሳይከፍል ፤ ለእውነት ሲል ወህኒ ተወርውሮ

ወህኒም ባይወርድ ባይጋዝ ፤ ፊት ሳይነፈግ ተገዳድሮ

የግፉአን ልሳን ሆኖ ፤ ለፍትሕ ለእውነት አብሮ

ይሄን ሳያደርግ ሳይተጋ ፤ መንፈሱን እራሱ ሰብሮ

የጨለማው ዓለም መብራቷ ፤ እንደ ድቅድቅ ጨላማ ጠቁሮ

ህዋሳቱን አደንዝዞ ፤ አእምሮውን አደንቁሮ

የጥፋት ኃይሎች ኃይል ሆኖ ፤ የሕዝብን እውነት ቀብሮ

ድንቄም ከያኔ የእኔም ልጅ ፤ የማን ነው ጭንጋፍ ቀበሮ?

ሕዝብና ሀገርን ከድቶ ፤ የእውነት ቀባሪ መደዴ

ይሄ ከያኔ አይደለም ፤ ነው ለሆዱ ያደረ ነጋዴ

ምንም ነገር እንደማያውቁት ፤ ያለሆዳቸው ምንዳ

ወደ እንስሳነት የተቀየረ ፤ ለምን? እንዴት? አይል ዱዳ

ብላሀለችና እናት ኪነት ፤ ደፍረህ ሳታፍር ሳተፈራ

ገጣሚ ደራሲ ሠዓሊ ፤ ተዋናይ ተጫዋች ዳንኪራ

ኪነት የነፍሴ ጥሪ ፤ ብለህ መስሟ እንዳትጠራ!!!

የፈለገኝ ሊያየኝ የሻ ፤ ምንጊዜን ቢሆን አድራሻየ

ከሕዝብ ከእውነት ጋራ ነው ፤ የእኔ መኖሪያ ቦታየ

የተፈጠርኩበት ዓላማ ፤ ሥራና ተግባር ሞያየ

ቃልኪዳኑን ሲያስርልኝ ፤ የጥበብ አምላክ ጌታየ

ሕይዎትን ቀና ማድረግ ነው ፤ ችግር ግፍ አሳር ታግየ

እንጅ ሕይዎትን ለማምረር ፤ አይደለም ለአውሬ ደልየ

ልብ  ያለው ሁሉ ልብ ይበል ፤ ጽኑ ነውና መሐላየ፡፡

ብላለችና ጥበብ ኪነት ፤ መልእክቱ ይድረስ ለሁሉ

የሳተ ቶሎ ይመለስ ፤ ይቅር ይባላል በደሉ፡፡

ነሐሴ 1 2006 ዓ.ም.

መታሰቢያነቷ ለልማታዊ ……በሚሉ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. speaker says

    August 23, 2014 05:20 pm at 5:20 pm

    I am crying.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule