• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ክደራና ክየና

August 21, 2014 02:24 am by Editor 1 Comment

አንድ ብልጣብልጥ ባለተራ ፤ ከያኔ ነኝ የሚል ጽፎ

በእሱ ቤት የማላውቅበት ፤ መከደሩን ለንብ ቀፎ

በየሔደበት ያወራል ፤ ጸሐፊያንን ነቃቅፎ

ጋዜጣ መጽሔት ድረ ገጽ ፤ ወደዛ! እያለ ተጸይፎ

አታንብቡ አትስሟቸው ፤ ብሎ ያርቃል አንባቢ

የጌቶቹ ጉድ እንዳይወጣ ፤ እንዳይገለጥ ሸባቢ

እንዴት ምን ነካህ? ለሚሉት ፤ ተገርመው በጭፍን ትችቱ

ችግር መኖሩ መች ጠፋን  ? ይሄ ሀገር የሚሻው በብርቱ

መፍትሔውን ቢነግሩን ነው ፤ ይላል ልሳኑን አስልቶ

መፍትሔው እንዳልተጻፈ ፤ ከችግሮቹ ጋር ጎልቶ፡፡

ይሄው አይደሉ እነሱ? ማደናቆር መተጣጠፍ

ምን እነግራለሁ ለእናንተ ፤ ታውቋቸው የለ ከወደአፍ?

በዐይን የሚታየው በጉልህ ፤ የሚጨበጠው ተይዞ

ካሳበቃቸው ጭራሽ የለም ፤ በቃ የለማ ማን አዞ?

የማይታየው የሌለው ፤ ምናባዊውን ሕልም እንጀራ

ብሉ ጠጡ ጥገቡ ነው ፤ እንዲሁ በባዶ ጉራ

እንዴ! እንዴት ሆኖ? አትሉም ፤ በቃ ይሄ ነዋ ክደራ፡፡

ግድ የለም ይሁን ወዳጀ ፤ ዐይኔ ዐላየም ካልክ መፍትሔ

ተጽፏል ብለህ ያመንከው ፤ ችግሮች ተብሎ ያ ይሄ

ችግርን ማወቅ መረዳት ፤ ያገር ሀብት ከንቱ የሚያስፈጅ

ግማሽ መፍትሔ ነው እንዲሉ ፤ ምዕራባዊያን ሥልጡን ፈረንጅ

ችግሮችህን መንገሩ ፤ ጸሐፊው ውዱን የሀገር ልጅ

ይገባሀል እንጂ ማመስገን ፤ አደግድገህ በመንሣት እጅ

እኮ በል እንዴት ሆኖ ነው? በአንተ ዝርው አፍ በገፈጅ

የሚነቀፍ የሚኮነነው ፤ መስታውቱ ጉድፍ አስወጋጅ ፡፡

የሌለውን አለ ሳልል ፤ ያለውን ግን አውጥቸ

ከነ መፍትሔ መላውም ፤ ጽፌልሐለው አጥርቸ

እኮ በል ልይህ ስትሔደው ፤ በአልኩህ መንገድ ማምለጫ

መፍትሔም አላልክ መድኃኒት? ከችጋር ግፍ አሳር መውጫ

እኮ በል ልይህ አድርገው? ያው እኮ ነገርኩህ ጩሄ

ግፈኞቹ የተውልህን ፤ የቀረህ ብቸኛ መፍትሔ

ደፋኸውሳ አንገትህን ፤ አሄሄ አሄሄ አሄሄ!

ተነቃቅተናል ወዳጀ ፤ ዝም ብለህ ልቀም ከበርሔ

ቡሌ ፍርፋሪህን ፤ የኩሊነትክን ድርሻ

ምን ማዕረግ አለውና ፤ ከዚህ በላይ የደጅ ውሻ?

ከዚያ ውጭ መፍትሔ ካለህ ፤ የሚሆን ያልተሞከረ

በላ ንገረን እንስማው ? ሳንሔድበት የቀረ፡፡

ግን እባክህን ወዳጀ ፤ የምለምንህ በብዙ

ከያኔ ነኝ አትበለን ፤ ቃናውም የለህ ወዙ

እናት ኪነትን ጠይቄያት ፤ ልጅ እንዳላት ብየ እንዳንተ

ኅሊናውን ለሆድ ሸጦ ፤ ቡሌ የሚለቅም የሳተ

እውነትን የሚረጋግጥ ፤ የግፈኛ አገልጋይ ሎሌ

የሞራል(የቅስም) እሴት የሌለው ፤ የማንም ምናምን ኩሊ

ልጀ አይደለም አላውቀውም ፤ እናቴ አይበለኝ አደራ

አደራ አደራ አደራ ፤ ቁጣየ እጅግ ነው መራራ

የእኔ ልጆቸ የታወቁ ፤ የእውነት ጠበቃ ለሐቅ ያደሩ

ኅሊናቸውን አክባሪ ፤ በሕዝብ በሀገር አይቆምሩ

ከዚህች ፈቀቅ የማይሉ ፤ ሞት እንኳን ቢሆን የማይፈሩ

ግፈኞችን ሳይዋጋ ፤ የሰላ ብዕሩን ወድሮ

መራሩን ዋጋ ሳይከፍል ፤ ለእውነት ሲል ወህኒ ተወርውሮ

ወህኒም ባይወርድ ባይጋዝ ፤ ፊት ሳይነፈግ ተገዳድሮ

የግፉአን ልሳን ሆኖ ፤ ለፍትሕ ለእውነት አብሮ

ይሄን ሳያደርግ ሳይተጋ ፤ መንፈሱን እራሱ ሰብሮ

የጨለማው ዓለም መብራቷ ፤ እንደ ድቅድቅ ጨላማ ጠቁሮ

ህዋሳቱን አደንዝዞ ፤ አእምሮውን አደንቁሮ

የጥፋት ኃይሎች ኃይል ሆኖ ፤ የሕዝብን እውነት ቀብሮ

ድንቄም ከያኔ የእኔም ልጅ ፤ የማን ነው ጭንጋፍ ቀበሮ?

ሕዝብና ሀገርን ከድቶ ፤ የእውነት ቀባሪ መደዴ

ይሄ ከያኔ አይደለም ፤ ነው ለሆዱ ያደረ ነጋዴ

ምንም ነገር እንደማያውቁት ፤ ያለሆዳቸው ምንዳ

ወደ እንስሳነት የተቀየረ ፤ ለምን? እንዴት? አይል ዱዳ

ብላሀለችና እናት ኪነት ፤ ደፍረህ ሳታፍር ሳተፈራ

ገጣሚ ደራሲ ሠዓሊ ፤ ተዋናይ ተጫዋች ዳንኪራ

ኪነት የነፍሴ ጥሪ ፤ ብለህ መስሟ እንዳትጠራ!!!

የፈለገኝ ሊያየኝ የሻ ፤ ምንጊዜን ቢሆን አድራሻየ

ከሕዝብ ከእውነት ጋራ ነው ፤ የእኔ መኖሪያ ቦታየ

የተፈጠርኩበት ዓላማ ፤ ሥራና ተግባር ሞያየ

ቃልኪዳኑን ሲያስርልኝ ፤ የጥበብ አምላክ ጌታየ

ሕይዎትን ቀና ማድረግ ነው ፤ ችግር ግፍ አሳር ታግየ

እንጅ ሕይዎትን ለማምረር ፤ አይደለም ለአውሬ ደልየ

ልብ  ያለው ሁሉ ልብ ይበል ፤ ጽኑ ነውና መሐላየ፡፡

ብላለችና ጥበብ ኪነት ፤ መልእክቱ ይድረስ ለሁሉ

የሳተ ቶሎ ይመለስ ፤ ይቅር ይባላል በደሉ፡፡

ነሐሴ 1 2006 ዓ.ም.

መታሰቢያነቷ ለልማታዊ ……በሚሉ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. speaker says

    August 23, 2014 05:20 pm at 5:20 pm

    I am crying.

    Reply

Leave a Reply to speaker Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule