• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እኚህ ሰው ማናቸው? – ፲፬

May 3, 2015 12:47 pm by Editor 3 Comments

የጎልጉል ወዳጅ ወለላዬ “እኚህ ሰው ማናቸው?” በሚል ርዕስ ግሩም ዝግጅት ሲያቀርቡ መቆየታቸው ይታወሳል። ይህንን ዝግጅት በጥያቄና በግጥም መልክ የሚያቀርቡት እንደመሆኑ ምላሹም በግጥም እንዲሆን አንባቢያንን እርሳቸውም እኛም እናደፋፍራለን። ወለላዬ ከተለያዩ የግልና መሰል የህይወት ውጣውረዶች በኋላ አሁን ዝግጅታቸውን እንደገና ጀምረዋል። ጎልጉልም በደስታ እንኳን ደህና መጡ ይላቸዋል። የመጨረሻው “እኚህ ሰው ማናቸው?” ፲፫ኛው ነበር የዚያን መልስ ከአዲሱ ጥያቄ ጋር አቅርበናል። ወዳጃችን ወለላዬ በድጋሚ እንኳን ደህና መጡ ምስጋናችን ይድረስዎ።


ከዚህ በፊት ኮሎኔል ታምራት ይገዙን አቅርቤ መልስ ሳልሰጥ አቋርጨ ነበር። አሁን ከመልሱ ጋር አዲስ ልኪያለሁwho is this person 13

መልስ

ይዘን የቀረብነው ምስላቸውን በፊት

ይባሉ ነበረ ኮሎኔል ታምራት

ኮሎኔል ታምራት ታምራት ይገዙ

የሰሩ ሰው ናቸው ላገራቸው ብዙ።


ላሁኑ “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፲፬” ደግሞ ወለላዬ የሚከተለውን አቅርበዋል። ምላሻችሁን በግጥም በመመለስ ለዝግጅቱ ውበት እንድትሰጡ ለማደፋፈር እንወዳለን። በሚቀጥለው መልሱን በግጥም እናቀርባለን።

ጥያቄwho is this

የድሮውን ዘመን ታሪክ ያልተረዳ

ላለንበት ዘመን ይሆናል እንግዳ

ለምሳሌ እኝህ ሰው ባገራችን ታሪክ

በምን ስራቸው ነው የሚታወሱት ሰርክ

ብዙ አይጨነቁ ግጥም ልጻፍ ብለው

ያለውን ወርውሩ ዋናው ታሪኩ ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Who is This Person Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Yimeku Tamirat says

    May 4, 2015 02:00 pm at 2:00 pm

    እነድኔና እንዳንተ ስደት የቀመሱት
    ለሀገር ነጻነት ተግተው የደከሙት
    በአገር፣ በፍርድና በጽሕፈት ሚኒስቴር
    በአሩሲ፣ ኢሉባቡር አገር አስተዳደር
    ያገለገሉ ሰው ከመሆንም በላይ
    ቅድስጌ ማርያምን አሠሩ በድንጋይ
    በአባታቸው ቡልጌ፣ በናታቸው መንዝ
    ወልደ ጊዮርጊስ ማለት ፀሐፌ ትእዛዝ።

    Reply
  2. Bombu says

    May 6, 2015 09:59 pm at 9:59 pm

    ኣንቱ ኢትዮጵያዊ ተመርጦ ታሪኩ
    በጥያቄ ሲቀርብ በጣፈጠ መልኩ
    ጎልጉል መድረክ ሰጥቶ እኛም ስንሳተፍ
    አንዳንዴ ሲቀናን ባብዛኛው ግን ሲከሽፍ

    በዕረፍት የሁን ወይም በሌላ ምክንያት
    በመሐል ተቋርጦ ለጥቂት ወራት
    የነበረው እንካችሁ እኚህ ሰው ማናችው
    ወለላዬ መጣ ሊያገጣጥማቸው

    ፎⶆቸውን ከላይ የምናያቸው ሰው
    ታላቅ ሐላፊነት ባገር ላይ ተረክበው
    ባገር ወዳድነት አገልጋይ በትጋት
    ከነበሩት ሰዎች ከሌሎች ባንድነት
    የቅርብ ረዳትም እንዲሁም ወዳጅ
    ከሥልጣንም ሥልጣን ከንጉሱ ደጅ
    አክሊሉ ሐብተወልድ ሌሎችም ታዋቂ
    ያገርን መመሪያ ለውጭው አርቃቂ
    ሆነው ሲጨነቁ ሲወጡ ሲወርዱ
    እኚም ሰው አሉበት ከሌሎች እንዳንዱ

    ፀሐፊ ነበሩ ትዛዝም ተቀባይ
    ወልደጎርጊስ አንቱ የትጉሕ ተወካይ
    ብዬ ባጠቃልል እንደዝች ባጭሩ
    ከምኞትም ጋር ነው ዛሬ በነበሩ»

    Reply
  3. Nibret Yalew says

    May 13, 2015 02:06 am at 2:06 am

    እኝህ ሰው- አባታቸው ቆዳ በማልፋት የተለያዩ ባህላዊ እቃዎችን በመስራት ይተዳደሩ ነበር፡፡ እኝህ ሰው በሊሴ ገብረማረያም ትምህርት ቤት እስከ አምስተኛ ክፍል ተምረዋል፤ አዕምሯቸው ፈጠን ሲሆን፣ ፈረንሳይኛ አቀላጥፈው የሚናገሩ ሰው ነበሩ፤ በጊዜው የሁለተኛ ደረጃ እና የኮሌጅ ትምህርት በአገር ውስጥ ሰለማይሰጥ ሊከታተሉ አልቻሉም፤ በስራው ዓለም በአንድ ሚኒስተር መስርያቤት የመስራት እድሉን ቢያገኙም ለትምህርት ከፍተኛ ጉጉት ስለነበራቸው በዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል ፈረንሳየኛ በማስተርጎም ስራ ላይ መሰማራቱን መረጡ- እየሰሩ የቋንቋም ሆነ ሌሎች ችሎታዎችን በልምድ ሊያዳብሩ ስለወደዱ፡፡

    ….ከለዕታት በአንዱ ቀን መኮነን ሃብተወልድ አስም ታመው ወደሆስፒታል ስለገቡ ከእሳቸው ጋር የመተዋወቅ እድሉን አገኙ፤ አልጋ ወራሽ ተፈሪ መኮነንም አቶ መኮነን ሃብተወልድን ሊጠይቁ በመጡበት ወቅት ስለ እሳቸው ብቃት እና ችሎታ በአቶ በመኮን አማካኝነት ይገነዘባሉ…ከዝያም በወቅቱ አንድ ከፍተኛ ባለስልጣን ታሞ ስለነበር እኝህ ሰው እንዲያስታምሙት እና ቋንቋ እንዲያስተረጉሙ ወደፈረንሳይ ይላካሉ…. በፈረንሳይም ስለዘመናዊ መንግስት አስተዳደር፤ ስለፖለቲካ እና መስል እውቀቶችን ከተለያዩ መፃህፍተ አንብበውና ተመራምረው በእውቀት ላይ እውቀት ጨምረው ይመለሳሉ- ሰውየው በአገኙት አጋጣሚ መማር ይሻሉእና፡፡

    ከዚያም (እንደ ኢትዮ. አቆጣጠር ከ1932 እስከ 1947) በመጀመርያ የአገር ግዛት ሚንስትር፤ ቀጥሎም ፀሐፊ ትዕዛዝ በመሆን የአገሪቱን ከፍተኛ ስልጣን ሊጨብጡ የቻሉ እና በስልጣን ዘመናቸውም ውጤታማና ፍሬያማ ተግባራትን የከወኑ፣ “በመጨረሻም ስልጣኑን ሁሉ ጠቅልሎ በመያዝ ጃንሆይን ሊፈነቅሏቸው ነው” ተብለው ስለተጠረጠሩ ከሹመታቸው ወርደው የአሩሲ ክፍለ ሃገር ገዥ ሆነው የተላኩ ድንቅ እና ታላቅ ሰው ናቸው …. በችሎታቸው እና በየአጋጣሚው ከልምድ እና ከህይወት እየተማሩ ከትንሽ ቦታ ወደ ዙፋን የተጠጉ አስገራሚ ሰው ናቸው……ፀሐፊ ትዕዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ ወልደዮሐንስ!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule