• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እኚህ ሰው ማናቸው? – ፲፬

May 3, 2015 12:47 pm by Editor 3 Comments

የጎልጉል ወዳጅ ወለላዬ “እኚህ ሰው ማናቸው?” በሚል ርዕስ ግሩም ዝግጅት ሲያቀርቡ መቆየታቸው ይታወሳል። ይህንን ዝግጅት በጥያቄና በግጥም መልክ የሚያቀርቡት እንደመሆኑ ምላሹም በግጥም እንዲሆን አንባቢያንን እርሳቸውም እኛም እናደፋፍራለን። ወለላዬ ከተለያዩ የግልና መሰል የህይወት ውጣውረዶች በኋላ አሁን ዝግጅታቸውን እንደገና ጀምረዋል። ጎልጉልም በደስታ እንኳን ደህና መጡ ይላቸዋል። የመጨረሻው “እኚህ ሰው ማናቸው?” ፲፫ኛው ነበር የዚያን መልስ ከአዲሱ ጥያቄ ጋር አቅርበናል። ወዳጃችን ወለላዬ በድጋሚ እንኳን ደህና መጡ ምስጋናችን ይድረስዎ።


ከዚህ በፊት ኮሎኔል ታምራት ይገዙን አቅርቤ መልስ ሳልሰጥ አቋርጨ ነበር። አሁን ከመልሱ ጋር አዲስ ልኪያለሁwho is this person 13

መልስ

ይዘን የቀረብነው ምስላቸውን በፊት

ይባሉ ነበረ ኮሎኔል ታምራት

ኮሎኔል ታምራት ታምራት ይገዙ

የሰሩ ሰው ናቸው ላገራቸው ብዙ።


ላሁኑ “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፲፬” ደግሞ ወለላዬ የሚከተለውን አቅርበዋል። ምላሻችሁን በግጥም በመመለስ ለዝግጅቱ ውበት እንድትሰጡ ለማደፋፈር እንወዳለን። በሚቀጥለው መልሱን በግጥም እናቀርባለን።

ጥያቄwho is this

የድሮውን ዘመን ታሪክ ያልተረዳ

ላለንበት ዘመን ይሆናል እንግዳ

ለምሳሌ እኝህ ሰው ባገራችን ታሪክ

በምን ስራቸው ነው የሚታወሱት ሰርክ

ብዙ አይጨነቁ ግጥም ልጻፍ ብለው

ያለውን ወርውሩ ዋናው ታሪኩ ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Who is This Person Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Yimeku Tamirat says

    May 4, 2015 02:00 pm at 2:00 pm

    እነድኔና እንዳንተ ስደት የቀመሱት
    ለሀገር ነጻነት ተግተው የደከሙት
    በአገር፣ በፍርድና በጽሕፈት ሚኒስቴር
    በአሩሲ፣ ኢሉባቡር አገር አስተዳደር
    ያገለገሉ ሰው ከመሆንም በላይ
    ቅድስጌ ማርያምን አሠሩ በድንጋይ
    በአባታቸው ቡልጌ፣ በናታቸው መንዝ
    ወልደ ጊዮርጊስ ማለት ፀሐፌ ትእዛዝ።

    Reply
  2. Bombu says

    May 6, 2015 09:59 pm at 9:59 pm

    ኣንቱ ኢትዮጵያዊ ተመርጦ ታሪኩ
    በጥያቄ ሲቀርብ በጣፈጠ መልኩ
    ጎልጉል መድረክ ሰጥቶ እኛም ስንሳተፍ
    አንዳንዴ ሲቀናን ባብዛኛው ግን ሲከሽፍ

    በዕረፍት የሁን ወይም በሌላ ምክንያት
    በመሐል ተቋርጦ ለጥቂት ወራት
    የነበረው እንካችሁ እኚህ ሰው ማናችው
    ወለላዬ መጣ ሊያገጣጥማቸው

    ፎⶆቸውን ከላይ የምናያቸው ሰው
    ታላቅ ሐላፊነት ባገር ላይ ተረክበው
    ባገር ወዳድነት አገልጋይ በትጋት
    ከነበሩት ሰዎች ከሌሎች ባንድነት
    የቅርብ ረዳትም እንዲሁም ወዳጅ
    ከሥልጣንም ሥልጣን ከንጉሱ ደጅ
    አክሊሉ ሐብተወልድ ሌሎችም ታዋቂ
    ያገርን መመሪያ ለውጭው አርቃቂ
    ሆነው ሲጨነቁ ሲወጡ ሲወርዱ
    እኚም ሰው አሉበት ከሌሎች እንዳንዱ

    ፀሐፊ ነበሩ ትዛዝም ተቀባይ
    ወልደጎርጊስ አንቱ የትጉሕ ተወካይ
    ብዬ ባጠቃልል እንደዝች ባጭሩ
    ከምኞትም ጋር ነው ዛሬ በነበሩ»

    Reply
  3. Nibret Yalew says

    May 13, 2015 02:06 am at 2:06 am

    እኝህ ሰው- አባታቸው ቆዳ በማልፋት የተለያዩ ባህላዊ እቃዎችን በመስራት ይተዳደሩ ነበር፡፡ እኝህ ሰው በሊሴ ገብረማረያም ትምህርት ቤት እስከ አምስተኛ ክፍል ተምረዋል፤ አዕምሯቸው ፈጠን ሲሆን፣ ፈረንሳይኛ አቀላጥፈው የሚናገሩ ሰው ነበሩ፤ በጊዜው የሁለተኛ ደረጃ እና የኮሌጅ ትምህርት በአገር ውስጥ ሰለማይሰጥ ሊከታተሉ አልቻሉም፤ በስራው ዓለም በአንድ ሚኒስተር መስርያቤት የመስራት እድሉን ቢያገኙም ለትምህርት ከፍተኛ ጉጉት ስለነበራቸው በዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል ፈረንሳየኛ በማስተርጎም ስራ ላይ መሰማራቱን መረጡ- እየሰሩ የቋንቋም ሆነ ሌሎች ችሎታዎችን በልምድ ሊያዳብሩ ስለወደዱ፡፡

    ….ከለዕታት በአንዱ ቀን መኮነን ሃብተወልድ አስም ታመው ወደሆስፒታል ስለገቡ ከእሳቸው ጋር የመተዋወቅ እድሉን አገኙ፤ አልጋ ወራሽ ተፈሪ መኮነንም አቶ መኮነን ሃብተወልድን ሊጠይቁ በመጡበት ወቅት ስለ እሳቸው ብቃት እና ችሎታ በአቶ በመኮን አማካኝነት ይገነዘባሉ…ከዝያም በወቅቱ አንድ ከፍተኛ ባለስልጣን ታሞ ስለነበር እኝህ ሰው እንዲያስታምሙት እና ቋንቋ እንዲያስተረጉሙ ወደፈረንሳይ ይላካሉ…. በፈረንሳይም ስለዘመናዊ መንግስት አስተዳደር፤ ስለፖለቲካ እና መስል እውቀቶችን ከተለያዩ መፃህፍተ አንብበውና ተመራምረው በእውቀት ላይ እውቀት ጨምረው ይመለሳሉ- ሰውየው በአገኙት አጋጣሚ መማር ይሻሉእና፡፡

    ከዚያም (እንደ ኢትዮ. አቆጣጠር ከ1932 እስከ 1947) በመጀመርያ የአገር ግዛት ሚንስትር፤ ቀጥሎም ፀሐፊ ትዕዛዝ በመሆን የአገሪቱን ከፍተኛ ስልጣን ሊጨብጡ የቻሉ እና በስልጣን ዘመናቸውም ውጤታማና ፍሬያማ ተግባራትን የከወኑ፣ “በመጨረሻም ስልጣኑን ሁሉ ጠቅልሎ በመያዝ ጃንሆይን ሊፈነቅሏቸው ነው” ተብለው ስለተጠረጠሩ ከሹመታቸው ወርደው የአሩሲ ክፍለ ሃገር ገዥ ሆነው የተላኩ ድንቅ እና ታላቅ ሰው ናቸው …. በችሎታቸው እና በየአጋጣሚው ከልምድ እና ከህይወት እየተማሩ ከትንሽ ቦታ ወደ ዙፋን የተጠጉ አስገራሚ ሰው ናቸው……ፀሐፊ ትዕዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ ወልደዮሐንስ!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule