• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እኚህ ሰው ማናቸው? – ፲፫

September 22, 2014 10:56 pm by Editor 11 Comments

ከአዘጋጆቹ፤ባለፈው ጊዜ “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፲፪” በሚል ለቀረበው ምላሽ በድረገጻችን በመላክና በፌስቡክ ላይ በመለጠፍ የተሳተፋችሁትን በሙሉ እናመሰግናለን፡፡ በተለይ በግጥም ምላሻችሁን ለሰጣችሁ በሙሉ ከፍያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ የቅንብሩ አዘጋጅ ወለላዬ በቁጥር አስራ ሁለት ለቀረበው ጥያቄ ምላሻቸውን በሚከተለው መልኩ በግጥም አስፍረዋል፡፡

መልስwho is this 12

የኚህ ሰው ማናቸው – አይነተኛ ተግባር

አይደለም ሙሉውን – ታሪክ ለመዘርዘር

ጥቆማውን አይቶ – አንባቢ እንዲፈልግ

ይረዳል ብለን ነው – መንገዱን ለመጥረግ

ተሰማ እሸቴንም – በዚህ አጭር ግጥም

ማንነታቸውን – ማስቀመጥ ባንችልም

በዜማ በቅኔ – አዋቂነታችው

ምንጊዜም ይነሳል – ይጠራል ስማቸው

ከሊቅ እስከ ደቂቅ – ከሹም እስከ ንጉስ

ያገኙ ሰው ናቸው – እጅግ ታላቅ ሞገስ፡፡


ላሁኑ “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፲፫” ደግሞ ወለላዬ የሚከተለውን አቅርበዋል፡፡ ምላሻችሁን በግጥም በመመለስ ለዝግጅቱ ውበት እንድትሰጡ ለማደፋፈር እንወዳለን፡፡ በሚቀጥለው መልሱን በግጥም እናቀርባለን፡፡who is this person 13

ጥያቄ

በያንዳንዱ ጊዜ – በያንዳንዱ ዘመን

በቸገራት ጊዜ – ሀገርን የሚያድን

መነሳቱ አይቀርም – ድንገት አንድ ቆራጥ

ነፍሱን የሚገብር – ህይወቱን የሚሰጥ

እኚህም ታላቅ ሰው – የሰሩትም ሥራ

የምመሰክር ነኝ – ማንንም ሳልፈራ

ሆኖም ከዛ በፊት – እድሉን እንካችሁ

ማንነታቸውን – ንገሩኝ ጽፋችሁ።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Who is This Person Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Hagos says

    September 23, 2014 05:46 pm at 5:46 pm

    Ene yemilew timkhtengoch meche yihon bedimocrasi ena belimat yemiyamnut lenegeru yeshabiya kitirenga silehonachihu alferdibchihum koy tebiku yanen kirchat teshekami alekachihun birihanun yizen sinasgebalachihu maninetachiun tiredalachihu ,

    Reply
  2. Bombu says

    September 25, 2014 01:12 am at 1:12 am

    ከላይ የፃፍከው ሰው ሐጎስ የወያኔ
    መድከምህ በከንቱ ያሳዝናል ለኔ
    ወይ ጥያቄው አልገባሕ ወይ ከብዶሐል መልሱ
    እንደው ዘራፌዋ በአሰሱ ገሰሱ
    ባንተ አይፈረድም ያቅምህን ነውና
    እንደው መዘባረቅ አወይ ድንቁርና
    እንኩዋን ልትመልስ ጥያቄ ተረድትህ
    ገና ፈራሃቸው ፎቶአቸውን አይትህ
    አዎ ያስፈራሉ የኢትዮጵያ ጀግኖች
    ጊዜ ለስጥው ቅል ድንጋይ ሰባሪውች
    ምናልባት ከሆነ በግጥም መቅረቡ
    ለስድ ስድ ንባብ ጠይቅ በአግባቡ
    ትንሽ ታገሥና ዞር ዞር ብለህ
    ብትመለስ ሽጋ ከራሥህ ጋር ታርቀህ
    የምትሰማ ቢሆን ምክር ለአንዳፍታ
    ውርደት ቀለብ ላይሆን ሐፍረትም በተርታ
    ግጥሙ ላይሆንልህ ይቅር መዘባረቅ
    ሐጎስ አባ ሆዱ ኢትዮጵያዊን ለቀቅ‹

    Reply
    • ባየው ጉርሙ says

      September 25, 2014 11:24 pm at 11:24 pm

      ዘጠኝ ዓመት ጎንደር ተኝተው የከረሙት ኮሎኔል ታምራት ይገዙ

      Reply
  3. Ameha Alemu says

    September 25, 2014 01:01 pm at 1:01 pm

    Col.Tamirat Yigezu.

    Reply
  4. banch says

    September 25, 2014 01:36 pm at 1:36 pm

    Betekekel negerkew yehenen yezemen atela.

    Reply
  5. Bombu says

    September 27, 2014 12:43 am at 12:43 am

    ጌታው አቶ ጉርሙ ሆነብን ባጭሩ
    ሐሳቡ ይብራራ እንዲታይ ሚስጥሩ
    ወጉን ስላገኘን እዚህ መታደሙ
    ግልፅነት መልስ ነው ባየው አቶ ጉርሙ
    ጉዳዩ አልገባንም ይብራራልን ትንሽ
    በግምት ተነስተን ፀሐይ ጠልቃ ሳይመሽ
    መልዕክቱ ምን ይሆን የዕርስዎ አስተያየት
    ዳር ዳሩን አይሂዱ ሥጋ እንዳየ ድመት
    ዘጠኝ ዓመትማ ሁሉም ሰው የተኛል
    በናቱ መሐፅን በፍጥረት ይዋኛል
    ጎንደር አፍርታለች ጀግኖች በየተራ
    ለሁላችን መኩሪያ ታሪኳም የጋራ
    መተኛት የሚሉት የቃል አመራረጥ
    ማብራሪያው ካልመጣ ካልሆነ አንድ ወጥ
    ትችት ያስከትላል ጥርጣሬ አብዝቶ
    ፍራቻው ምን ይሆን ከአደባባይ ወጥቶ
    ሥለዚህ ወገኔ ግድ የለም አይፍሩ
    ግልፅነት ያዋጣል ቢሆንም ባጭሩ
    እንደገና መለስ ብለው ከተቻለ
    መልሱን ያብራሩልን ፍላጎቱ ካለ

    Reply
  6. አስናቀ ደመና says

    September 27, 2014 10:29 am at 10:29 am

    እኝህ ሰው ማናቸው – ብለው ለጠየቁን፣
    ለዕውቁ ገጣሚ – ለማስረዳት ሀቁን፣
    በዚህ በምስሉ ላይ – የሚታዩት ጀግና፣
    የፈጸሙት ገድል ብዙም አልተጠና።

    ግና…

    ብዙም ባይነገር – ዝክረ ታሪካቸው፣
    በሞት ቢለዩንም – በአፍላ ዕድሜቸው፣
    ሎረንዞ ታዘዘ – ይባላል ስማቸው።

    ፋሽስት ኢጣሊያ -ኢትዮጵያን ለመውጋት፣
    ዕቅድ ስታወጣ – ያለምንም ስጋት፣
    ከተወለዱበት – ከኤርትራ አምልጠው፣
    በጣም ተጠንቅቀው – በጅቡቲ ዞረው፣
    ለአጼ ኃይለሥላሴ – ምስጢር ሊያቀብሉ፣
    ሎረንዞ ታዘዘ (ወደ አዲስ አበባ) – ሌሊት ኮበለሉ።

    ንጉሡ ዘንድ ቀርበው – ጉዳዩን ሲያስረዱ፣
    በፈጸሙት ገድል – ስለተወደዱ፣
    ሹመት ተሰጣቸው – አገር እንዲመሩ፣
    ሕዝብ በቅንነት – እንዲያስተዳድሩ።
    ስለዚ ለእኝህ ሰው
    ይጻፍ ግድላቸው – ፍሰቱን ጠብቆ፣
    ይውጣ አደባባይ – አይቅር ተደብቆ።

    ማስታወሻ
    በዚህ ታሪክ ውስጥ የተጠቀሰ ጊዜ ፋሽስት ኢጣሊያ ኢትዮጵያን ዳግመኛ የወረረችበትን ከ1928 እስከ 1933 ዓ.ም ያለውን ጊዜ ያመለክታል።

    Reply
    • Firew Ayenachew says

      February 6, 2016 05:33 pm at 5:33 pm

      Lorenzo

      Reply
  7. Bombu says

    September 28, 2014 06:46 pm at 6:46 pm

    ይድረስ ለአስናቀ ደመናው ወገኔ
    ሰላምታና አድናቆ ቢቀበሉኝ ከኔ

    መልስ ማለት እንዲህ ሁሉንም አካቶ
    የግጥምን ውበት በዛው አሳይቶ
    መንደርደሪያውና ማረፊያው የሚታይ
    ማብራሪያ ከሥሩ ሁሉም ተከታታይ

    ቅደም ተከተሉ እንደተጠበቀ
    መሠረቱን ሳይለቅ ባግባቡ ዘለቀ
    ከላይ በቀረበው የተሳካ ሥራ
    ስለ ተደስትኩኝ እኔም እንደ ተራ

    በግጥም ወረዳ በዛ በጎዳናው
    ይመላለስበት አስናቀ ደመናው
    በማለት ላመስግን ለመልሱ ባለቤት
    ታሪኩን ተረዳሁ የቃላትም ሥሌት

    ከዚህ በተረፈ መልሱን አስመልክቶ
    የዐምዱ ባለቤት አስተያየት ስጥቶ
    ሎሬንዞ ታዘዘ ትክክል ከሆነ
    አስናቀ ደመናው ወደፊት ታመነ

    Reply
  8. Abiy Ethiopiawe Segawi We-Menfesawi says

    October 1, 2014 05:06 pm at 5:06 pm

    ወለላዬ ወዳጄ

    No—12

    የእኚህን አዛውንት ይህን ምስል አይቶ፤
    አላውቅም የሚል ሰው ታሪክን ዘንግቶ፤
    እዚህ ላይም አይጻፍ አይጫወት እግር ኳስ፤
    መልሱን እስኪሰጥህ ይህን ሊቀ-መኳስ።
    የኢትዮጵያ ውድ ልጅ ክቡር የቅኔ ሰው፤
    የኳስ አባት ወላጅ ሕዝብ የሚያስታውሰው፤
    የሚያስደንቅ ልጁ የጥቁሮች ጥበቃ፤
    በስፖርት ፍቅር ብቻ አዕምሮው እንደነቃ፤
    ታሪክ ፅፎ አለፈ አይደለም ውሸቴ፤
    የነጋ ድረስ ልጅ አያቱ እሸቴ።

    No 13—-

    የራስ መስፍን ምክትል፤
    ጉቦ አልወድም እንኳን ሳይል፤
    እሱም ገባና በመዘዙ፤
    ሌ/ኮረኔል ታምራት ይገዙ፤
    ነብሱን ገበረ እንደ መስፍን፤
    ሥልጣኑን በሞት ሊሸፍን።

    Reply
  9. yetnayet says

    October 2, 2014 10:33 pm at 10:33 pm

    Mengistu Newayn yimeslalu

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule