• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እኚህ ሰው ማናቸው? – ፲፫

September 22, 2014 10:56 pm by Editor 11 Comments

ከአዘጋጆቹ፤ባለፈው ጊዜ “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፲፪” በሚል ለቀረበው ምላሽ በድረገጻችን በመላክና በፌስቡክ ላይ በመለጠፍ የተሳተፋችሁትን በሙሉ እናመሰግናለን፡፡ በተለይ በግጥም ምላሻችሁን ለሰጣችሁ በሙሉ ከፍያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ የቅንብሩ አዘጋጅ ወለላዬ በቁጥር አስራ ሁለት ለቀረበው ጥያቄ ምላሻቸውን በሚከተለው መልኩ በግጥም አስፍረዋል፡፡

መልስwho is this 12

የኚህ ሰው ማናቸው – አይነተኛ ተግባር

አይደለም ሙሉውን – ታሪክ ለመዘርዘር

ጥቆማውን አይቶ – አንባቢ እንዲፈልግ

ይረዳል ብለን ነው – መንገዱን ለመጥረግ

ተሰማ እሸቴንም – በዚህ አጭር ግጥም

ማንነታቸውን – ማስቀመጥ ባንችልም

በዜማ በቅኔ – አዋቂነታችው

ምንጊዜም ይነሳል – ይጠራል ስማቸው

ከሊቅ እስከ ደቂቅ – ከሹም እስከ ንጉስ

ያገኙ ሰው ናቸው – እጅግ ታላቅ ሞገስ፡፡


ላሁኑ “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፲፫” ደግሞ ወለላዬ የሚከተለውን አቅርበዋል፡፡ ምላሻችሁን በግጥም በመመለስ ለዝግጅቱ ውበት እንድትሰጡ ለማደፋፈር እንወዳለን፡፡ በሚቀጥለው መልሱን በግጥም እናቀርባለን፡፡who is this person 13

ጥያቄ

በያንዳንዱ ጊዜ – በያንዳንዱ ዘመን

በቸገራት ጊዜ – ሀገርን የሚያድን

መነሳቱ አይቀርም – ድንገት አንድ ቆራጥ

ነፍሱን የሚገብር – ህይወቱን የሚሰጥ

እኚህም ታላቅ ሰው – የሰሩትም ሥራ

የምመሰክር ነኝ – ማንንም ሳልፈራ

ሆኖም ከዛ በፊት – እድሉን እንካችሁ

ማንነታቸውን – ንገሩኝ ጽፋችሁ።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Who is This Person Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Hagos says

    September 23, 2014 05:46 pm at 5:46 pm

    Ene yemilew timkhtengoch meche yihon bedimocrasi ena belimat yemiyamnut lenegeru yeshabiya kitirenga silehonachihu alferdibchihum koy tebiku yanen kirchat teshekami alekachihun birihanun yizen sinasgebalachihu maninetachiun tiredalachihu ,

    Reply
  2. Bombu says

    September 25, 2014 01:12 am at 1:12 am

    ከላይ የፃፍከው ሰው ሐጎስ የወያኔ
    መድከምህ በከንቱ ያሳዝናል ለኔ
    ወይ ጥያቄው አልገባሕ ወይ ከብዶሐል መልሱ
    እንደው ዘራፌዋ በአሰሱ ገሰሱ
    ባንተ አይፈረድም ያቅምህን ነውና
    እንደው መዘባረቅ አወይ ድንቁርና
    እንኩዋን ልትመልስ ጥያቄ ተረድትህ
    ገና ፈራሃቸው ፎቶአቸውን አይትህ
    አዎ ያስፈራሉ የኢትዮጵያ ጀግኖች
    ጊዜ ለስጥው ቅል ድንጋይ ሰባሪውች
    ምናልባት ከሆነ በግጥም መቅረቡ
    ለስድ ስድ ንባብ ጠይቅ በአግባቡ
    ትንሽ ታገሥና ዞር ዞር ብለህ
    ብትመለስ ሽጋ ከራሥህ ጋር ታርቀህ
    የምትሰማ ቢሆን ምክር ለአንዳፍታ
    ውርደት ቀለብ ላይሆን ሐፍረትም በተርታ
    ግጥሙ ላይሆንልህ ይቅር መዘባረቅ
    ሐጎስ አባ ሆዱ ኢትዮጵያዊን ለቀቅ‹

    Reply
    • ባየው ጉርሙ says

      September 25, 2014 11:24 pm at 11:24 pm

      ዘጠኝ ዓመት ጎንደር ተኝተው የከረሙት ኮሎኔል ታምራት ይገዙ

      Reply
  3. Ameha Alemu says

    September 25, 2014 01:01 pm at 1:01 pm

    Col.Tamirat Yigezu.

    Reply
  4. banch says

    September 25, 2014 01:36 pm at 1:36 pm

    Betekekel negerkew yehenen yezemen atela.

    Reply
  5. Bombu says

    September 27, 2014 12:43 am at 12:43 am

    ጌታው አቶ ጉርሙ ሆነብን ባጭሩ
    ሐሳቡ ይብራራ እንዲታይ ሚስጥሩ
    ወጉን ስላገኘን እዚህ መታደሙ
    ግልፅነት መልስ ነው ባየው አቶ ጉርሙ
    ጉዳዩ አልገባንም ይብራራልን ትንሽ
    በግምት ተነስተን ፀሐይ ጠልቃ ሳይመሽ
    መልዕክቱ ምን ይሆን የዕርስዎ አስተያየት
    ዳር ዳሩን አይሂዱ ሥጋ እንዳየ ድመት
    ዘጠኝ ዓመትማ ሁሉም ሰው የተኛል
    በናቱ መሐፅን በፍጥረት ይዋኛል
    ጎንደር አፍርታለች ጀግኖች በየተራ
    ለሁላችን መኩሪያ ታሪኳም የጋራ
    መተኛት የሚሉት የቃል አመራረጥ
    ማብራሪያው ካልመጣ ካልሆነ አንድ ወጥ
    ትችት ያስከትላል ጥርጣሬ አብዝቶ
    ፍራቻው ምን ይሆን ከአደባባይ ወጥቶ
    ሥለዚህ ወገኔ ግድ የለም አይፍሩ
    ግልፅነት ያዋጣል ቢሆንም ባጭሩ
    እንደገና መለስ ብለው ከተቻለ
    መልሱን ያብራሩልን ፍላጎቱ ካለ

    Reply
  6. አስናቀ ደመና says

    September 27, 2014 10:29 am at 10:29 am

    እኝህ ሰው ማናቸው – ብለው ለጠየቁን፣
    ለዕውቁ ገጣሚ – ለማስረዳት ሀቁን፣
    በዚህ በምስሉ ላይ – የሚታዩት ጀግና፣
    የፈጸሙት ገድል ብዙም አልተጠና።

    ግና…

    ብዙም ባይነገር – ዝክረ ታሪካቸው፣
    በሞት ቢለዩንም – በአፍላ ዕድሜቸው፣
    ሎረንዞ ታዘዘ – ይባላል ስማቸው።

    ፋሽስት ኢጣሊያ -ኢትዮጵያን ለመውጋት፣
    ዕቅድ ስታወጣ – ያለምንም ስጋት፣
    ከተወለዱበት – ከኤርትራ አምልጠው፣
    በጣም ተጠንቅቀው – በጅቡቲ ዞረው፣
    ለአጼ ኃይለሥላሴ – ምስጢር ሊያቀብሉ፣
    ሎረንዞ ታዘዘ (ወደ አዲስ አበባ) – ሌሊት ኮበለሉ።

    ንጉሡ ዘንድ ቀርበው – ጉዳዩን ሲያስረዱ፣
    በፈጸሙት ገድል – ስለተወደዱ፣
    ሹመት ተሰጣቸው – አገር እንዲመሩ፣
    ሕዝብ በቅንነት – እንዲያስተዳድሩ።
    ስለዚ ለእኝህ ሰው
    ይጻፍ ግድላቸው – ፍሰቱን ጠብቆ፣
    ይውጣ አደባባይ – አይቅር ተደብቆ።

    ማስታወሻ
    በዚህ ታሪክ ውስጥ የተጠቀሰ ጊዜ ፋሽስት ኢጣሊያ ኢትዮጵያን ዳግመኛ የወረረችበትን ከ1928 እስከ 1933 ዓ.ም ያለውን ጊዜ ያመለክታል።

    Reply
    • Firew Ayenachew says

      February 6, 2016 05:33 pm at 5:33 pm

      Lorenzo

      Reply
  7. Bombu says

    September 28, 2014 06:46 pm at 6:46 pm

    ይድረስ ለአስናቀ ደመናው ወገኔ
    ሰላምታና አድናቆ ቢቀበሉኝ ከኔ

    መልስ ማለት እንዲህ ሁሉንም አካቶ
    የግጥምን ውበት በዛው አሳይቶ
    መንደርደሪያውና ማረፊያው የሚታይ
    ማብራሪያ ከሥሩ ሁሉም ተከታታይ

    ቅደም ተከተሉ እንደተጠበቀ
    መሠረቱን ሳይለቅ ባግባቡ ዘለቀ
    ከላይ በቀረበው የተሳካ ሥራ
    ስለ ተደስትኩኝ እኔም እንደ ተራ

    በግጥም ወረዳ በዛ በጎዳናው
    ይመላለስበት አስናቀ ደመናው
    በማለት ላመስግን ለመልሱ ባለቤት
    ታሪኩን ተረዳሁ የቃላትም ሥሌት

    ከዚህ በተረፈ መልሱን አስመልክቶ
    የዐምዱ ባለቤት አስተያየት ስጥቶ
    ሎሬንዞ ታዘዘ ትክክል ከሆነ
    አስናቀ ደመናው ወደፊት ታመነ

    Reply
  8. Abiy Ethiopiawe Segawi We-Menfesawi says

    October 1, 2014 05:06 pm at 5:06 pm

    ወለላዬ ወዳጄ

    No—12

    የእኚህን አዛውንት ይህን ምስል አይቶ፤
    አላውቅም የሚል ሰው ታሪክን ዘንግቶ፤
    እዚህ ላይም አይጻፍ አይጫወት እግር ኳስ፤
    መልሱን እስኪሰጥህ ይህን ሊቀ-መኳስ።
    የኢትዮጵያ ውድ ልጅ ክቡር የቅኔ ሰው፤
    የኳስ አባት ወላጅ ሕዝብ የሚያስታውሰው፤
    የሚያስደንቅ ልጁ የጥቁሮች ጥበቃ፤
    በስፖርት ፍቅር ብቻ አዕምሮው እንደነቃ፤
    ታሪክ ፅፎ አለፈ አይደለም ውሸቴ፤
    የነጋ ድረስ ልጅ አያቱ እሸቴ።

    No 13—-

    የራስ መስፍን ምክትል፤
    ጉቦ አልወድም እንኳን ሳይል፤
    እሱም ገባና በመዘዙ፤
    ሌ/ኮረኔል ታምራት ይገዙ፤
    ነብሱን ገበረ እንደ መስፍን፤
    ሥልጣኑን በሞት ሊሸፍን።

    Reply
  9. yetnayet says

    October 2, 2014 10:33 pm at 10:33 pm

    Mengistu Newayn yimeslalu

    Reply

Leave a Reply to አስናቀ ደመና Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule