• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ልብ ላለው ሰው ድንጋይም ከትጥቅ በላይ ነው” ባለጥሩምባ ዘማች መምህርት ምዕራፍ ፍቃዴ

November 7, 2021 11:53 am by Editor Leave a Comment

እኔ ትጥቅ የለኝም፤ ወደትግሉ ስቀላቀል እንደ ትጥቅ ይዤ የገባሁት ጡርምባዬን ነው። ይህ የዘማቿ መምህርት ምዕራፍ ፍቃዴ ንግግር ነው።

አሸባሪውና ወራሪው ኃይል በአማራና አፋር ክልሎች እያካሄደ ያለውን መጠነ ሰፊ ጥቃት ተከትሎ በርካታ ዜጎች በቁጭት ይህን ኃይል ለመመከት ተነስተዋል። መምህርት ምዕራፍም በዚህ የህልውና ዘመቻ መልስ ከሰጡ እንስት ታጋዮች አንዷ ሆናለች።

የአማራ ክልል የጠራውን የህልውና ዘመቻ በስኬት እንዲጠናቀቅ የሚጠበቅባትን እየተወጣች እንድምትገኝ የምትናገራው ዘማቿ መምህርት፤ ለትግሉ መሳካት እየተጠቀመችበት ያለው ጥሩምባዋ የጦር መሳሪያ ያህል ነው ትላለች።

ልብ ላለው ሰው አገርን በወሬ ለመፍታት የሚጥርን ወራሪ ቡድን ለመፋለም ድንጋይም ከትጥቅ በላይ መሆኑን ትናገራለች።

“እኔም በጡሩምባ ለሠራዊቱ የሚሆን የተሳካ ሎጅስቲክስ ድጋፍ ማሰባሰብ ችያለሁ” ስትል የምትናገረው ወዶ ዘማቿ መምህርት፤ በባዶ እጁ ለወረራ የሚመጣ ቡድንን ለመፋለም “ልብ ካለን” ጥሩምባ ትልቅ መሳሪያ ነው ትላለች።

እንደ ዘማች መምህርቷ ገለጻ፤ አሸባሪው ትህነግ አንድን መሳሪያ ለሰባት ሰዎች በማስታጠቅ ኢትዮጵያን በወሬ ለማፍረስ እየጣረ ነው። በወሬ አገርን ለማፍረስ የሚጥርን ጠላት ለመፋለም ድንጋይም ከመሳሪያ በላይ ነው።አንዳንድ ወጣቶች ትጥቅ የለንም እና ሌሎች ሰበቦችን በማንሳት የህዝቡን ወኔ ለማዳከም ሲጥሩ ይስተዋላል። እነኝህ አካላት የአሸባሪው ሕወሓት ተላላኪ እንደሆኑ ሕዝቡ ሊገነዘብ ይገባል ትላለች።

በመንግሥት የተጠራው የህልውና ዘመቻ ነው። በህልውና ዘመቻ የግድ ሁሉም መሣሪያ ካልተሰጠኝ ብሎ ራስን ለጠላት አሳልፎ መስጠት አይገባም። የተነሳው ወጣት ስንቅ በማዘጋጀት፣ የደከመን የወገን ኃይል በማገዝ፣ መሳሪያ በመሸከም፣ ቁስለኛን በማሸሽ እንዲሁም ሌሎች ተግባራትን በማከናወን ወጣቱ የድርሻውን በማበርከት አሸባሪው ቡድን እስኪቀበር መታገል ይኖርበታል ትላለች።

አሸበሪው ሕወሓት የአማራ ክልልን ለመውረር ሲመጣ አብዛኛዎቹ የወራሪ ቡድኑ አባላት የመጡት ባዶ እጃቸውን ነው የምትለው ወዶ ዘማች መምህርት፤ ወገንም ከጠላቱ ተምሮ የሽብር ቡድኑ አገር ለማተራመስ የሚጠቀምበትን ምላሱን መቀሌ ድረስ በመሄድ መቁረጥ ይገባዋል።

በአማራ ክልል የተጠራውን የክተት አዋጅ ተከትሎ አሁን ወጣቱ እና ሚሊሻው ከየቦታው እጅግ በከፍተኛ ቁጥር ወደ ጦር ግንባር እየተመመ ይገኛል። ይህን ወጣት እና ሚሊሻ በትንሽ መስዋእትነት አሸናፊ እንዲሆን ለማስቻል የሚያግዙ የአደረጃጀት ሥራዎች ሲከናወንም ቆይቷል። (ሙሉቀን ታደገ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule