• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ልብ ላለው ሰው ድንጋይም ከትጥቅ በላይ ነው” ባለጥሩምባ ዘማች መምህርት ምዕራፍ ፍቃዴ

November 7, 2021 11:53 am by Editor Leave a Comment

እኔ ትጥቅ የለኝም፤ ወደትግሉ ስቀላቀል እንደ ትጥቅ ይዤ የገባሁት ጡርምባዬን ነው። ይህ የዘማቿ መምህርት ምዕራፍ ፍቃዴ ንግግር ነው።

አሸባሪውና ወራሪው ኃይል በአማራና አፋር ክልሎች እያካሄደ ያለውን መጠነ ሰፊ ጥቃት ተከትሎ በርካታ ዜጎች በቁጭት ይህን ኃይል ለመመከት ተነስተዋል። መምህርት ምዕራፍም በዚህ የህልውና ዘመቻ መልስ ከሰጡ እንስት ታጋዮች አንዷ ሆናለች።

የአማራ ክልል የጠራውን የህልውና ዘመቻ በስኬት እንዲጠናቀቅ የሚጠበቅባትን እየተወጣች እንድምትገኝ የምትናገራው ዘማቿ መምህርት፤ ለትግሉ መሳካት እየተጠቀመችበት ያለው ጥሩምባዋ የጦር መሳሪያ ያህል ነው ትላለች።

ልብ ላለው ሰው አገርን በወሬ ለመፍታት የሚጥርን ወራሪ ቡድን ለመፋለም ድንጋይም ከትጥቅ በላይ መሆኑን ትናገራለች።

“እኔም በጡሩምባ ለሠራዊቱ የሚሆን የተሳካ ሎጅስቲክስ ድጋፍ ማሰባሰብ ችያለሁ” ስትል የምትናገረው ወዶ ዘማቿ መምህርት፤ በባዶ እጁ ለወረራ የሚመጣ ቡድንን ለመፋለም “ልብ ካለን” ጥሩምባ ትልቅ መሳሪያ ነው ትላለች።

እንደ ዘማች መምህርቷ ገለጻ፤ አሸባሪው ትህነግ አንድን መሳሪያ ለሰባት ሰዎች በማስታጠቅ ኢትዮጵያን በወሬ ለማፍረስ እየጣረ ነው። በወሬ አገርን ለማፍረስ የሚጥርን ጠላት ለመፋለም ድንጋይም ከመሳሪያ በላይ ነው።አንዳንድ ወጣቶች ትጥቅ የለንም እና ሌሎች ሰበቦችን በማንሳት የህዝቡን ወኔ ለማዳከም ሲጥሩ ይስተዋላል። እነኝህ አካላት የአሸባሪው ሕወሓት ተላላኪ እንደሆኑ ሕዝቡ ሊገነዘብ ይገባል ትላለች።

በመንግሥት የተጠራው የህልውና ዘመቻ ነው። በህልውና ዘመቻ የግድ ሁሉም መሣሪያ ካልተሰጠኝ ብሎ ራስን ለጠላት አሳልፎ መስጠት አይገባም። የተነሳው ወጣት ስንቅ በማዘጋጀት፣ የደከመን የወገን ኃይል በማገዝ፣ መሳሪያ በመሸከም፣ ቁስለኛን በማሸሽ እንዲሁም ሌሎች ተግባራትን በማከናወን ወጣቱ የድርሻውን በማበርከት አሸባሪው ቡድን እስኪቀበር መታገል ይኖርበታል ትላለች።

አሸበሪው ሕወሓት የአማራ ክልልን ለመውረር ሲመጣ አብዛኛዎቹ የወራሪ ቡድኑ አባላት የመጡት ባዶ እጃቸውን ነው የምትለው ወዶ ዘማች መምህርት፤ ወገንም ከጠላቱ ተምሮ የሽብር ቡድኑ አገር ለማተራመስ የሚጠቀምበትን ምላሱን መቀሌ ድረስ በመሄድ መቁረጥ ይገባዋል።

በአማራ ክልል የተጠራውን የክተት አዋጅ ተከትሎ አሁን ወጣቱ እና ሚሊሻው ከየቦታው እጅግ በከፍተኛ ቁጥር ወደ ጦር ግንባር እየተመመ ይገኛል። ይህን ወጣት እና ሚሊሻ በትንሽ መስዋእትነት አሸናፊ እንዲሆን ለማስቻል የሚያግዙ የአደረጃጀት ሥራዎች ሲከናወንም ቆይቷል። (ሙሉቀን ታደገ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Left Column, News

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule