• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ልብ ላለው ሰው ድንጋይም ከትጥቅ በላይ ነው” ባለጥሩምባ ዘማች መምህርት ምዕራፍ ፍቃዴ

November 7, 2021 11:53 am by Editor Leave a Comment

እኔ ትጥቅ የለኝም፤ ወደትግሉ ስቀላቀል እንደ ትጥቅ ይዤ የገባሁት ጡርምባዬን ነው። ይህ የዘማቿ መምህርት ምዕራፍ ፍቃዴ ንግግር ነው።

አሸባሪውና ወራሪው ኃይል በአማራና አፋር ክልሎች እያካሄደ ያለውን መጠነ ሰፊ ጥቃት ተከትሎ በርካታ ዜጎች በቁጭት ይህን ኃይል ለመመከት ተነስተዋል። መምህርት ምዕራፍም በዚህ የህልውና ዘመቻ መልስ ከሰጡ እንስት ታጋዮች አንዷ ሆናለች።

የአማራ ክልል የጠራውን የህልውና ዘመቻ በስኬት እንዲጠናቀቅ የሚጠበቅባትን እየተወጣች እንድምትገኝ የምትናገራው ዘማቿ መምህርት፤ ለትግሉ መሳካት እየተጠቀመችበት ያለው ጥሩምባዋ የጦር መሳሪያ ያህል ነው ትላለች።

ልብ ላለው ሰው አገርን በወሬ ለመፍታት የሚጥርን ወራሪ ቡድን ለመፋለም ድንጋይም ከትጥቅ በላይ መሆኑን ትናገራለች።

“እኔም በጡሩምባ ለሠራዊቱ የሚሆን የተሳካ ሎጅስቲክስ ድጋፍ ማሰባሰብ ችያለሁ” ስትል የምትናገረው ወዶ ዘማቿ መምህርት፤ በባዶ እጁ ለወረራ የሚመጣ ቡድንን ለመፋለም “ልብ ካለን” ጥሩምባ ትልቅ መሳሪያ ነው ትላለች።

እንደ ዘማች መምህርቷ ገለጻ፤ አሸባሪው ትህነግ አንድን መሳሪያ ለሰባት ሰዎች በማስታጠቅ ኢትዮጵያን በወሬ ለማፍረስ እየጣረ ነው። በወሬ አገርን ለማፍረስ የሚጥርን ጠላት ለመፋለም ድንጋይም ከመሳሪያ በላይ ነው።አንዳንድ ወጣቶች ትጥቅ የለንም እና ሌሎች ሰበቦችን በማንሳት የህዝቡን ወኔ ለማዳከም ሲጥሩ ይስተዋላል። እነኝህ አካላት የአሸባሪው ሕወሓት ተላላኪ እንደሆኑ ሕዝቡ ሊገነዘብ ይገባል ትላለች።

በመንግሥት የተጠራው የህልውና ዘመቻ ነው። በህልውና ዘመቻ የግድ ሁሉም መሣሪያ ካልተሰጠኝ ብሎ ራስን ለጠላት አሳልፎ መስጠት አይገባም። የተነሳው ወጣት ስንቅ በማዘጋጀት፣ የደከመን የወገን ኃይል በማገዝ፣ መሳሪያ በመሸከም፣ ቁስለኛን በማሸሽ እንዲሁም ሌሎች ተግባራትን በማከናወን ወጣቱ የድርሻውን በማበርከት አሸባሪው ቡድን እስኪቀበር መታገል ይኖርበታል ትላለች።

አሸበሪው ሕወሓት የአማራ ክልልን ለመውረር ሲመጣ አብዛኛዎቹ የወራሪ ቡድኑ አባላት የመጡት ባዶ እጃቸውን ነው የምትለው ወዶ ዘማች መምህርት፤ ወገንም ከጠላቱ ተምሮ የሽብር ቡድኑ አገር ለማተራመስ የሚጠቀምበትን ምላሱን መቀሌ ድረስ በመሄድ መቁረጥ ይገባዋል።

በአማራ ክልል የተጠራውን የክተት አዋጅ ተከትሎ አሁን ወጣቱ እና ሚሊሻው ከየቦታው እጅግ በከፍተኛ ቁጥር ወደ ጦር ግንባር እየተመመ ይገኛል። ይህን ወጣት እና ሚሊሻ በትንሽ መስዋእትነት አሸናፊ እንዲሆን ለማስቻል የሚያግዙ የአደረጃጀት ሥራዎች ሲከናወንም ቆይቷል። (ሙሉቀን ታደገ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule