• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሓት/ትህነግ በአጥር ላይ

November 27, 2019 06:14 am by Editor Leave a Comment

ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት/ትህነግ) በማለት የሚጠራውና በኢትዮጵያ እጅግ አስከፊ የሚባልና ትውልድን ያወደመ ርዕዮት በመከተል አገር ያፈረሰው የተገንጣዮች ጥርቅም፤ አዲስ የተመሠረተውን ብልጽግና ፓርቲ አልቀላቀልም ብሎ ካፈነገጠ ወዲህ ሁኔታዎች መስመር እየለቀቁበት ነው። ላሁኑ አጥር ላይ መንጠልጠሉን አማራጭ አድርጓል።

እስካሁን በዓለምአቀፍ የአሸባሪዎች የመረጃ ቋት በአሸባሪነት ተመዝግቦ የሚገኘው ትህነግ/ህወሓት መሪ የነበረው መለስ በሥልጣን በቆየበት ዘመን ሲዘልፋቸው የኖረውን ተቃዋሚዎች ባንድ ወቅት እንዲህ ብሏቸው ነበር፤ አጥር ላይ መሆንና አንድ እግር ከግቢ ውስጥ ሌላኛውን ከውጭ ማድረግ አይቻልም። በአሁኑ ወቅት ህወሓት ያለችበት ወቅታዊ ሁኔታ የመለስን አጽም ካላበት ቦታ እንዲላወስ ያደረገ ሆኗል። አንድ እግሯ መቀሌ፤ ሌላው እግሯ አዲስ አበባ ሆኗል።

ባለፈው ዓመት ሐዋሳ ላይ በተደረገው የኢህአዴግ ፲፩ኛ ስብሰባ የግምባሩን ውህደት አስመልክቶ ጠቅላላው ጉባዔ የኢህአዴግ ምክርቤት ውህደቱ እንዲያስፈጽም ውክልና ሰጥቶት ነበር። ይህ ሲወሰን ህወሓቶች እጃቸውን ሰቅለው ዶ/ር ዐቢይን በሊቀመንበርነት እንደመረጡት ይህንንም ውሳኔ በሙሉ ድምጽ ደግፈዋል።

ላለፉት በርካታ ወራት አገር በማተራመስና ሕዝብን በማጋደል ሥራ ተጠምደው የነበሩት ህወሓቶች የማይደርስ መስሏቸው የግምባሩ ውህደት ሲደርስ አዲስ ትርክት ጀመሩ። ውህደት ጠቅላይነት ነው፤ አሃዳዊነት ነው፤ መብት ገፋፊ ነው፤ በማለት ሙሾአቸውን አሰሙ። ለነጻነት እንታገላለን ሲሉ እና ሕዝብ ሲደግፋቸው የነበሩ፤ ሕዝብን ክደው ቶርቸር ሲያደርጋቸው ከነበረው ህወሓት ጋር በመሰለፍ ፌደራሊስት ነን አሉ። የሚያዋጣ መስሏቸው ገፉበት።

ውህደቱ ዕውን ሲሆን ሦስቱ እህት ፓርቲዎች በሙሉ ድምጽ ሲደግፉ ለስብሰባው አዲስ አበባ ከመጡት የህወሓት አባላት መካከል ፊት አልባው መቀሌ ሲቀር ስድስቱ ተቃወሙ፤ ሁለቱ ደግሞ ለሽንት ወጥተው ነበር ተባለላቸው። እነዚህ የወጡት ደብረጽዮንና ኬሪያ እንደነበሩ በአንዳንዶች ተዘግቧል።

የህወሓት ተወካዮች ከሥራ አስፈጻሚው የውህደት ስብሰባ በኋላ ከዶ/ር ዐቢይ ጋር ውይይት እንዳደረጉ ተሰምቷል። በውጤቱም ስምምነት ሳይደርሱ ተለያዩ ቢባልም ጥያቄያቸው ውድቅ ተደረገባቸው የሚለው በአሳማኝነት ለመቀበል የሚቀል ይመስላል። መቀሌም ከደረሱ በኋላ ከተለያየ አቅጣጫ ተቃውሞ ሲደርስባቸው ያለፈው እሁድ ውህደቱን የሚቃወም ሰልፍ ጠሩ። ጊዜው ሲደርስ ግን ሠልፉ የተፈለገውን ዓላማ ለማሳኪያ እንደማይሆን በተረዱበት ጊዜ ሰረዙት። ከዚህ ጋር ተያይዞ የትግራይ ሕዝብ ከአዲስ አበባ ይዘው የመጡትን ውሃ የማይቋጥር ወሬ አንቀበልም እያላቸው እንደሆነ አየተሰማ ነው ያለው።

ሁኔታው ያላማራቸው የህወሓት መሪዎች ባንድ በኩል ለመዋሃድ እንፈልጋለን በማለት አዲስ አበባ ሽማግሌ መላካቸው የተሰማ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ኢህአዴግ በውህደት ስም አዲስ ፓርቲ ነው የመሠረተው፤ የኢህአዴግን ውርስ በመውሰድ አዲስ ፓርቲ መመሥረት አይቻልም፤ ተሰብሰበን እንወስናለን በማለት በደብረጽዮን አማካኝነት መግለጫ ሰጥተዋል።

ይህ ማለት እንግዲህ አምና የኢህአዴግ አጠቃላይ ጉባዔ ሐዋሳ ላይ የግምባሩን ውህደት ምክርቤቱ እንዲፈጽመው በማለት ሲወስን በሙሉ ድምጽ የወሰኑትን በመካድ ነው። ለሚዲያ ፍጆታ ብዙ ማወናበጃ መጠቀም ይቻል ይሆናል፤ ማስረጃ በሚጠቀስበት የፓርቲ ስብሰባ ላይ ግን እንዲህ ዓይነት ቀልድ እንደማይቻል እነጌታቸው ረዳና ደብረጽዮን አሳምረው ያውቁታል። ለዚህም ነው በሽምግልና እና በአንዋሃድም መካከል ላይ የተንጠለጠሉት። እውነታው ግን “የአስገቡኝ” ልመና ላይ ያሉ ለመሆናቸው አመላካቾች አሉ።

ከሁለት ቀን በፊት በትግራይ ክልል መሪ ደብረጽዮን ፊርማ የሽሬ ነዋሪ ለስብሰባ ተጠርቶ ነበር። ዋናው አጀንዳ የነበረው ስለ ውህደቱና በቀጣይ ለማድረግ ስለታሰበው ለመወያየት የነበረ ሲሆን ስብሰባውን በመቃወም ተሰብሳቢው ጥሎ መውጣቱ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ በስፋት ተዘግቦበታል። ለስብሰባ የመጣው ሕዝብ ተቃውሞውን እያሰማ ወደ ከተማ ወጥቶ የነበረ ሲሆን በተቃውሞ ሰልፉ ላይም “አማራ ጠላታችን አይደለም፤ ወደ ጦርነት መግባት አንፈልግም” የሚሉ መፈክሮች መሰማታቸው ታውቋል። ውህደቱንም በተመለከተ ህወሓት ለመዋሃድ አለመፈለጉ አንድ ጉዳይ ሲሆን መዋሃድ ከመገንጠል ጋር ምንም የሚያገናኘው ነገር የለም በማለት ሰልፈኞቹ በተቃውሟቸው አስረድተዋል።

ህወሓት ተስፋ ያደረጋቸው አጋር ፓርቲዎችም አፋር፣ ቤንሻንጉል፣ ጋምቤላ፣ ሐረሪ ውህደቱን እንቀበላለን ብለው ውሳኔ አስተላልፈዋል። ቀሪ አለኝ ብለው ተስፋ ያደረጉት ሶማሊም ዛሬ (ማክሰኞ) ውህደቱን እንደሚቀበል ወስኗል። ህወሓቶች በፌዴራሊስት ስም የሚሰበሰቧቸው ጥርቅምቃሚ ፓርቲዎች የአየለ ጫሚሶና የትዕግስቱ ዐወል ፓርቲዎች እንኳንስ ከህወሓት ጋር ወግነው ገና ከጅምሩ ሕዝብ አንቅሮ የተፋቸው በዘመነ ህወሓት የደኅንነቱ ተከፋዮች እንደነበሩ የሚታወቅ ነው።

መቀሌ ላይ “ኢትዮጵያን እናድን” በሚል ስብሰባ ጠርታ የነበረችው ህወሓት ስብሰባው እንደታሰበው ሳይሆን በመቅረቱ በቀጣይ ምን ማድረግ አለብን የሚለውን በለመደችው ድርጅታዊ እና ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት አሠራር በደብረጽዮን አማካኝነት በጠራችው ስብሰባ በቅርቡ ታስወስናለች።

በአሁኑ ጊዜ ከብዙ አቅጣጫ አጣብቂኝ ውስጥ የገባችው ህወሓት የመሪዋን መለስ ውለታ በልታ፤ በመቃብር ያለውን መሪዋን አሳፍራ ባጥር ላይ ተንጠልጥላ ትገኛለች። ሰሞኑን በጠራችው ስብሰባ ደግሞ ወይ እንዋሃድ ወይም አንጓጉል ብላ በመዋሃድ ስም መሠሪ ተግባሯን ትቀጥላለች ወይም ጓጉላ መጨረሻዋ መገለል ይሆናል። ለማንኛውም ህወሓቶች ተሰብስበው ሲጠያዩ (ሲገማገሙ) ቢያንስ አዲስ ህንፍሽፍሽ ወይም እርስበርስ ወደመጠፋፋት የሚወስድ መከፋፈል ሊከሰት ይችላል የሚለው ሌላው የሚጠበቅ ነው።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, meles zenawi, Middle Column, prosperity party, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule