• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የህወሓት/ኢህአዴግ የገጠር መዋቅር ሊፈርስ ይችላል ተባለ

August 25, 2017 07:29 pm by Editor 7 Comments

  • ህወሓት በትግራይ ላይ የራሱን አቋም እንዲወስድ ተመክሯል

በኢትዮጵያ ያለማቋረጥ ሲካሄድ ከቆየው ሕዝባዊ ተቃውሞ አኳያ በህወሓት የደህንነት ክፍል የተሰበሰበው መረጃ፤ አሁን ካለው የተቃውሞ ንቅናቄ የተነሳ የኢህአዴግ የገጠር መዋቀር በኦሮሚያና በከፊል የአማራ ክልሎች ሊፈርስ እንደሚችል አስታወቀ። ከሁኔታው አሳሳቢነት የተነሳ ሊወሰዱ የሚችሉ አማራጮች ቢኖሩም ህወሓት ትግራይን አስመልክቶ የራሱን አቋም እንዲወስድ ሃሳብ ተሰጥቶታል።

ኢትዮጵያን በነጻ አውጪ ስም እየገዛ ያለው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት) ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እየደረሰበት ያለውን የሕዝብ ተቃውሞ ለመቆጣጠር ተስኖት ይገኛል። በተለይ “ባለራዕዩ መሪውን” ሞት እንደ ቡሽ ክዳን ካስፈነጠረው ወዲህ ግምባሩ በአንድ መጓዝ፣ በአንድ መስማማት፣ በአንድ ማሰብ አቅቶት በተቃዋሚው መዳከምና በአንጋሾቹ አለሁ ባይነት ብቻ በሥልጣን መንበር ላይ ሲንገታገት ቆቷል። ሕዝብ ፊቱን ካዞረበት ቢቆይም በተለይ ትውልድ ካመጸበት ወዲህ ግን የአገዛዙ ኃይል እንደ ሹራብ ክር መጎልጎል ጀምሯል የሚሉ ጥቂቶች አይደሉም።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአማራና በኦሮሞ ቦታዎች የተነሳው ሕዝባዊ ተቃውሞ ህወሓት በኢህአዴግ ሥም እንደ ጭቃ ጠፍጥፎ የሠራቸው ብአዴንና ኦህዴድ “ሕዝባቸውን” መምራት የተሳናቸው መሆኑን ያስመሰከረ ሆኗል። የእነዚህ ሁለት ድርጅቶች የበታች አመራሮች መክዳት በስለላና በጥርነፋ ሁሉንም “ልክ አስገባለሁ” እያለ የሚፎክረውን ህወሓት ከራሱ የውስጥ ችግር ጋር ተዳምሮ የማይለቅ ራስ ምታት ሆኖበታል። እንደ አንዳንዶች አገላለጽ ሁለቱን ድርጅቶች አራቱም ጎማው ወልቆ መንገድ ዳር ከቆመ መኪና ጋር ያመሳስሏቸዋል።

የዛሬ ሁለት ዓመት አካባቢ ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጋር በተያያዘ የተጀመረውን ሕዝባዊ ተቃውሞ ሲነሳ ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ሁኔታውን በዘገበበት ወቅት ስለ ኦህዴድ መክዳት ይህንን ብሎ ነበር፤ “ሳምንታት ያስቆጠረውና የአዲስ አበባ ማስተር ፕላንን ምክንያት በማድረግ የተነሳው ሕዝባዊ እንቅስቃሴ በመጠኑም ሆነ በዓይነቱ ልዩ እየሆነ መሄዱ ኦህዴድ ኢህአዴግን የመክዳቱ ማስረጃ ነው ሲሉ በኦሮሚያ ጉዳዮች ላይ ለጎልጉል መረጃ የሚያቀብሉ አመራር አስታውቀዋል።

“በኢህአዴግ የአንድ ለአምስት ጥርነፋ፤ ስለላ፤ ሕዝባዊ አደረጃጀት፤ ቁጥጥር፤ … መዋቅሮችን ሁሉ አልፎ ይህንን ያህል ሕዝብ ያለአንዳች ከልካይ መውጣቱ አገዛዙ ሕዝቡን ለመጠርነፍ የተጠቀመበት አሠራር መልሶ ራሱን እየጠረነፈው እንደሆነ የሚያሳይ ነው። ታማኝ ተብሎ የተቀመጠው ካድሬም ሆነ የጥርነፋው መዋቅር ሕዝቡን ሊያስቆም አለመቻሉ የኦህዴድ እምቢተኛነትና ለአገዛዙ ድጋፍና እገዛ ከማድረግ ይልቅ ከሕዝቡ ጋር ለመቆሙ እንደ ዓይነተኛ ማስረጃ ይጠቀሳል”።

የዛሬ ዓመት በጎንደር ከተማ በበርካታ ሺዎች የሚቆጠር ሕዝብ ሰላማዊ ትዕይንተ ሕዝብ በማካሄድ “በኦሮሚያ የሚደረገው የወንድሞቻችን ግድያ ይቁም፤ በጎዳና ላይ የሚፈሰው የኦሮሞ ወንድምና እህቶቻችን ደም የእኛም ደም ነው” ባሉበት ወቅት “ስልታዊ ጥርነፋውን አልፎ ሕዝቡ ሰላማዊ ሰልፉን ለማድረግ መቻሉ ብአዴን ህወሃት የሚዘውረውን ኢህአዴግ ለመክዳቱ ፍንጭ ሰጥቷል” በማለት ጎልጉል ዘግቦ ነበር።

ይህንን መሰሉ ግልጽ መከዳት ያሳሰበው ህወሓት በቅርቡ በደኅንነት ክፍሉ በኩል የቀረበለትን የመረጃ ትንተና አዳምጧል። እንደ መረጃው ከሆነ በአገሪቷ ላይ ሲካሄድ የቆየው ሕዝባዊ ንቅናቄ ኢህአዴግን ክፉኛ ጎድቶታል። የድርጅቶቹ በሕዝቡ ላይ ያላቸው የበላይነት ካከተመ ሰነባብቷል። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከተነሳ በኋላ ሁኔታው በዚህ መልኩ መቀጠሉ በህወሓት አዛዥነት የሚተገበረው የኦህዴድና የብአዴን የጥርነፋም ሆነ የስለላ መረብ መርገቡ የሚያሳይ ሆኗል። በመሆኑም በቅርብ ጊዜ ውስጥ በመላ ኦሮሚያና በከፊል አማራ ክልል የህወሓት/ኢህአዴግ የገጠር መዋቅር ሊፈርስ እንደሚችል የደኅንነት ክፍሉ ዘገባ ትንበያ ሰጥቷል።

የጋምቤላ ደን በህወሓት ከመውደሙ በፊት

ከዚህ ጋር በተያያዘ ዘገባው አማራጭ የሚላቸውን “የመፍትሔ” ሃሳቦችን ጠቁሟል። አንዱ፤ ያለውን ኃይል ሁሉ ተጠቅሞ ሕዝባዊ ንቅናቄውን መቀልበስ፤ ሕዝቡን የሚያነሳሱ የፕሮፓጋንዳ መስመሮችን ሁሉ መዝጋት፤ ሌላው በምዕራባውያን አገራት ገለልተኛ ዕገዛ ኢህአዴግን ከተቃዋሚው ጋር ጠረጴዛ ላይ በማቅረብ ወደ ድርድር መምጣት፤ ይህ ካልሆነ ግን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር የሆነው ህወሓት የትግራይን መጻዒ ዕድል በተመለከተ የራሱን አቋም እንዲወስድ ምክር ተለግሶታል።

ምዕራባውያን ፊታቸውን በሕወሓት ላይ ከማዞራቸው አንጻር ሁለቱ አማራጮች ምን ያህል ውጤታማ እንደሚሆኑ ለመገመት የሚከብድ ቢሆንም ሦስተኛን በተመለከተ ግን አሁን አገሪቱ ውስጥ እየተከሰተ ያለው እምቢተኝነት ትግራይን አገር ለማድረግ እየተሠራ ካለው ሥራ በመፍጠኑ ሁኔታዎችን ያወሳሰበ ይመስላል። ሆኖም ከመለስ ዜናዊ “እንኳን ከናንተ ተወለድኩኝ! እንኳንም የሌላ አልሆንኩኝ..” ንግግር ጀምሮ መለስ ትግራይን ኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ የአምስት ዓመት ስትራቴጂያዊ ዕቅድ አውጥቶ እንደ ነበር አዜብ መስፍን

ጋምቤላ በህወሓት ከወደመ በኋላ Photo: Ajiem Ogalla

“ምሥጢሩን” እስከተናገረችው ድረስ ትግራይን አገር ስለማድረግ በአስረጂነት የሚጠቀሱ ናቸው። ከዚህም አልፎ ሕዝባዊ ንቅናቄው በተነሳበት ወቅት የትግራይ ወጣቶችን ለ“ትግራይን አድን” የውትድርና ስልጠና ከመጥራት ጀምሮ የዛሬ አምስት ዓመት በትግራይ በክልተአውላዕሎ ወረዳ ውስጥ የምትገኘው አብርሃ ወ-አጽብሃ የገጠር ቀበሌ “የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማትን በማቀጣጠል” በዓለምአቀፍ ደረጃ መሸለም፤ ከአግዓዚያን የትግራይ ድንበር እስከ አስመራ ነው ርዕዮት እስከ ‘‘(ትግራይ) በተፈጥሮ ሃብት አጠባበቅ ባካናወነችው ድንቅ ስራ በዓለም አቀፍ ደረጃ በእጩነት ከቀረቡ ስድስት (እጩዎች) መካከል በአንደኝነት በመመረጥ የወርቅ ተሻለሚ” መሆን የትግራይን በሉዓላዊ አገርነት የመመሥረት ምልክቶች ሆነው በአስተያየት ሰጪዎች ይቀርባሉ።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Mulatu says

    August 26, 2017 05:20 pm at 5:20 pm

    ርዕሱና ሀተታው የማይገናኝ ፅሑፍ ማቅረባችሁ ለአንባቢ ያላችሁን ግምት ያሳያል። ከዚህ በመቀጠል ስለትግራይ በአለም ዓቀፍ ደረጃ መሽለም ስትገልፁ የኢትዮጵያ የግዛት አካል ሳትሆን ራሷን ሉዓላዊት አገር አድርጋ የቀረቀች አስመስላችሁ ስትገልጽ ትንሽ ሀፍረት አይሰማችሁም? እንደአገላለፃችሁ 2ኛ&3ኛ የወጡት የብራዚል እና የቻይና ግዛቶች ሉዓላዊነታቸው የተረጋገጠ መሆን አለበት ማለት ነው። የአብርሃ ወአፅብሃ ቀበሌ በሰራው የተፈጥሮ ስራ በዓለም አደባባይ እውቅና ሲሰጠው ከሚገባው በላይ ደስ ሊለንና የተራቆተውን የሀገራችን ስነ ምህዳር ለማደስ አርዓያነቱን ተጠቅመን ለተግባራዊነቱ መነሳሳት ሲገባን መዋሸቱ ለምን አስፈለገ?ምንስ ጥቅም ይሰጣል ከማባላት ውጭ?የድረገጹ ዓላማ በርትዕ ላይ የተመሠረተ ትክክለኛ የዜና ምንጭ መሆን ቢችል ሀገራዊ ጥቅም ሊሰጥ ይችላል አለያ ግን ለራሳችሁም አይጠቅም።

    Reply
    • Editor says

      August 28, 2017 09:31 pm at 9:31 pm

      Mulatu

      ከአስተያየትህ ጽሁፉ የተፈለገውን ዓላማ ያሳካ ለመሆኑ ራስህ ማስረጃ ስለ ሰጠኸን ከልብ እናመሰግናለን። ለአንባቢዎቻችንም ምን ያህል አክብሮት እንዳለን ያሳየ ዜና መሆኑን አንተን ከመሰለ አንባቢ ምስክርነት ማግኘታችን በራሱ ታላቅ ድል ነው። “ርትዕ” “አገራዊ ጥቅም” … ምናምን ያልከውን ከ26 ዓመታት በኋላ አሁን ስንጠየቅ ለመመለስ ሞከርንና መልሱ ጠፋብን።

      በውነት ያንተው

      የጎልጉል አርታኢ

      Reply
    • Tesfa says

      August 29, 2017 11:59 am at 11:59 am

      ወያኔ ሃገር ማፍረስ የጀመረው ገና በበረሃ እያለ ነው። ለወያኔ ህብረት፤ ውህደትና አንድነት ጭራሽ የማይዋጥለት እውነት ነው። ዛሬ በዘርና በጎሳ የከለላትን ሃገር ለራሱ እንዳመቸ ሲፈነጥዝባት ዘመናት ተቆጥሮአል። የሚገርመው ግን ጊዜው ሲመሽ እንኳን ጨለማን ከብርሃን መለየት አለመቻላቸው ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ወያኔን ከተፋው ቆይቷል። ያው በታጠቀው መሳሪያ እያስፈራራና እያፈነ ዛሬም እንደትላንቱ እኖራለሁ ብሎ ማሰቡ ግን ሞኝነት ነው። በባህርዳር በወያኔ አነጣጣሪ ተኳሾች ወደ ሥራ ስትሄድ ከሞተችው ሴት ቦርሳ የተገኘ ጽሁፍ እንዲህ ይላል።
      ፈጣሪ ጥሩ ነው ዘመን ያሻግራል
      ለእኔም ቀን ወቶልኝ አልፎልኝ በኑሮ
      እናቴን አባቴን እንካችሁ የምለው
      ጊዜው መቼ ይሆን ጥቂቱ ተርቦ
      ብዙው ጠግቦ እሚያድረው?
      ራሷ በጥይት ተቦድሶ፤ ቡናማ ቦርሳዋ አጠገብዋ ሰው ሆን ብሎ እንዳስቀመጠው እስከሬኗን የሚይይ ዓይን ያለው ፍጡር ይመስላል። ፎቶው በብዙ ድህረ ገጾች ላይ ሰውን ያላቀሰ ነው። ወያኔ ዲሞክራሲን አያውቃትም። ዛሬ በሃገር ውስጥ መጽሃፍ ጽፈው ላሳታሚ ከሰጡ በህዋላ አሳታሚውን በማስፈራራት ህትምት እንዲቆም ያደርጋሉ፤ ከባንክ ገንዘብ ይዘርፋሉ። በጥቁር ገቢያ የዶላር ለዋጮች በሙሉ የወያኔ የድብቅ ሰራተኞች ናቸው። በንግድ ዓለም የተቃረናቸውን ከውድድር ያስወጣሉ፤ ያፍናሉ፤ ይገድላሉ። በዚህ ዓመት ብቻ የአሜሪካ መንግስት ስድስት ጊዜ ዜጎቿ በኢትዮጵያ በሚዘዋወሩበት ሥፍራ ሁሉ ጥንቃቄ እንዲያረጉ ይመክራል። እንደ ፈሳሽ ውሃ በፈለገው ጊዜ ወያኔ የሚቆልፈው የኢንተርኔት አገልግሎት ሰው ለሰው እንዳይረዳዳ ሆን ተብሎ የሚደረግ አፍራሽ የወያኔ ሴራ ነው።
      እንደ አቶ ሙላቱ አይነቱ ወስላታ የጠራ እይታ በማጣት የሚተነፍሱበት ሳንባና የሚያስቡበት ጭንቅላት የተገጠመላቸው በወያኔ የዘር ፓለቲካ ነው። የትግራይ ክልል መልማት ምንንም ቢሆን ደስ ያሰኛል። ይሁን እንጂ የሌላው የሃገራችን ክፍል እየተመነጠረና እሳት እየተለቀቀበት ትግራይ ብቻ አረንጓዴ ሆነች እስይ በሉ ማለት ተጨፈኑና ላሞኛችሁ እንደማለት ነው። የፓለቲካ ወስላቶች የዛሬን እንጂ የነገን አያዮም። እኔን እንጂ እኛን ማለት አይወዱም። ከሌላው የሃገሪቱ ክፍል እየተዘረፈ ትግራይን አለማን በአለም እውቅና አገኘን ማለት ፓለቲካዊ ኪሳራ እንጂ ትርፍ የለውም። ስርቆት የሚከበርበት፤ የተማሩና ለሃገሪቱ የሚያስቡ ወገኖቻችን በካቴና ተተፍረው ወህኒ የወረዱበት የወያኔዋ ከቁራሽ ተራፊ ኢትዮጵያ የእብዶች ስብስብ የሚያተራምሷት እድለ ቢስ ሃገር ናት። ያው አንተም ውሻ በበላበት ይጮሃል ነውና ለወያኔ ለማደር የድርሻህን የትርምስ ፓለቲካ ትነዛለህ።
      ታላቋ ትግራይ የወያኔ ህልም እንጂ እውነትነት አይኖረውም። ህልማቸው በአለም መንግሥታት ተቀባይነት የምይኖረው፤ ቀሪውን የኢትዮጵያ ህዝብ ለጦርነት የሚያዘጋጅ ነው። እርስ በርስ የሚያስተላልቅ ህልም ነው። ኢትዮጵያ ፈርሳ ትግራይ አትኖርም። ለዘመናት የአማራን ህብረተሰብ እንደ ቀንደኛ ጠላትነት የፈረጀው ወያኔ አሁንም በጎንደር ቅማንት ለራሱ ይሁን እያለ የሚያድበሰብሰው የአማራን ህዝብ ለመከፋፈል እንጂ ሌላ እይታ የለውም። በኤቢሲ የታየውም ካርታ ትክክለኛ ወያኔ የነደፈውን ሴራ ያሳያል እንጂ ማስተባበያ አያስፈልገውም። ወያኔ እኮ ደንቆሮ ነው። አባይን ትግራይ ውስጥ ነው ብሎ መጽሃፍ እንዲጻፍ ያደረገ ጭፍን ድርጅት። እንደሚታወቀው የአባይም ወደ ትግራይ በካርታ ላይ መጠቃለል በስህተት ነው ተብሎ ነው የታለፈው።
      ዘፋኞች የሙዚቃ ድግሳቸውን ለማቅረብ የማይፈቀድበት፤ የመሰብሰብና የመናገር ነጻነት የተነፈገበት፤ በሙስና ስም ሲበሉ ያዮትን እንጂ የበሉትን የማያስር፤ በዘር ችርቻሮ የከበረው የጠባብ ብሄርተኛው ቁንጮ ወያኔ የሮም አወዳደቅ ሲወድቅ ይታየኛል። ዛሬ በፀረ-ሽብር በሙስና እያመካኘ በሃገሪቱ እስር ቤቶች ያገታቸው የወያኔን ድብቅና ይፋ ሴራ የተጋፈጡትን ነው። ሃገር ማለት ለወያኔ ትግራይ ብቻ ነው። የለማው፤ የተሻለ ቀለም መሸመቻ የትምህርት ተቋማት የቆሙለት ለትግራይ ህዝብ ብቻ ነው። ሌላው ፍርፋሪ ለቃሚ ነው። በወያኔው አለቃ ሞት የተነሳ ወያኔ የባለ ብዙ አለቆችና የአዕላፍ ነጭ ለባሾች ስብስብ በመሆኑ መልህቅ እንደለላት መርከብ አቅጣጫ አልባ ነው የሚጓዙት። ጠ/ሚ የይስሙላ፤ ምክትል ጠ/ሚ በጥፊ በወያኔ የሚመታ (በዶ/ር ደብረጽዮን)፤ ጠበንጃ አንጋቹ በወታደርነት ስም የሚዘርፍና ህዝባችንን በሜዳ የሚረሽን የጨካኞች ስብስብ ነው። ወያኔ የጎንደርን ቆላማ ክፍል ለሱዳንና ለራሱ እየሸራረፈ የሚወስደውም የአማራን ህዝብ ለማበርክከ ነው። ሱዳንን አቆላምጦ ካልያዘ በዚያ በኩል የሚገቡ የተቃዋሚ ድርጅቶች ወያኔን በቀላሉ እንደሚያጠፉት ያውቃል። ምንም ይሁን ምንም ወያኔ ለፈጸመው ሃገር አፍራሽ ሥራው ዋጋ እንደሚያገኝ አምናለሁ። ጊዜው እየቀረበ ነው። ጀሮ ያለው ይስማ!!

      Reply
      • Messay Dejene Beshah says

        August 30, 2017 01:09 am at 1:09 am

        To the vast majority of Ethiopians the fate of Tigre/Tigrai is already sealed. In all honesty, no conscious Ethiopian would wish to see Tigres as anything but a neigbour.

        Having a common heritage or history does not necessarily lead to a harmonious unity.
        TPLF and its Tigre masses have acted as nothing but a brutal occupation force bent on completely destroying Ethiopia as we know it.

        From fighting alongside Eritreans to ceding vast tracts of land to the Sudan as well as annexing Afar, Benshangul, Gondar, and Wollo, to brazen genocides, they have done it all with impunity.

        Well, the writing is in the wall. Whatever it takes, the Tigre atrocities will be avenged before our borders are redrawn with our blood. Every Nazi German who was alive, was tracked down ruthlessly, thanks to the tireless Israeli intelligence services. Primitive, witless and ostentatious Tigres cannot be likened to the meticulous Germans.

        Criminal Tigres will be herded like lambs from wherever they are and brought to justice. America is not a safe heaven for terrorists and mmoney launderers which Tigres are. The thousands of bottle stores and shopping malls Tigres have opened in Denver, Dallas, Chicago and elsewhere will not shelter them from the American justice system when the day of reckoning beckons.

        Reply
  2. Ras Dejen says

    August 30, 2017 01:08 pm at 1:08 pm

    There won’t be right and wrong if there was no law and/or conscience based culture!
    With the same token, there is no criminal, no terrorist, no liar, no looter, no killer, no racist and no dictator if appraised by Western states and intelligences.
    If ordained or instituted by USA/CIA/UK/etc,
    An absolute criminal is absolutely lawful;
    An absolute terrorist is absolutely wise;
    An absolute liar is absolutely genuine;
    An absolute looter is absolutely righteous;
    An absolute killer is absolutely blameless;
    An absolute racist is absolutely liberal;
    An absolute oligarch is absolutely democrat;
    An absolute dictator is absolutely democrat.

    TPLF is procured, installed, hired and sustained by USA/CIA/MOSAD/UK. Enemy of TPLF is enemy of UK too. Genuine democrat, genuine humanitarian, genuine human, etc. is absolute enemy of UK, USA and their partners. That because such entities object deceit and sadism.

    But, Ethiopians need to hold on humanity!
    Sadist and narcissists shall be shattered like the other times by Ethiopians!
    And humanity will be liberated and cherish in our course again.

    Reply
  3. Mulugeta Andargie says

    September 2, 2017 09:37 pm at 9:37 pm

    ሃ/ማርያም: ሃ/ማርያም!!
    ያገራችን መሪ ድባብ! ተማም!
    ኣንደበተ ርቱእ ለምለም!!
    ቢናገሩት ዓይከፌ ዝናም

    አገር በቀል መጤ ዓይደል
    ያገር ልጅ ጠንበለል
    ዘመድ ለዘመድ ኣፋላጊ
    ሃገር ወዳድ ጠላት ዓስጊ
    ያገር ልጅ ያገር ኩራት
    ሃገራችንን ወደፊት የምናያት
    እንኳን ኣደረሰሽ እንበላት!!!
    ለመጀመሪያ ጊዜ እንበላት!!
    ያንድት የኩልነት ይሁንላት!!
    ባንተ ጊዜ እንኳን ለዚህ በቃሽ እንበላት!!!
    ሃ/ማርያም!! ታደግህላት!!
    ከመበጣጠስ ዓዳንካት!!
    ሁላችንም እንኳን ለዚህ ዓበቃሽ በሏት!!!

    ጠ/ሚ: ሃ/ማርያም በሱዳን ያደረጉት ጉብኝት እጅግ የምደነቅ ስራ ነው!!! ትልቅ የስራ ውጤት ነው!! መሪያችን እናመግኖታለን!!!

    Reply
  4. Bekel says

    November 2, 2017 03:05 pm at 3:05 pm

    I feel pity for “PM” Hailemariam!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule