• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሕዝብ “በጠብመንጃ መገዛት በቃን” አለ!! ትውልድ እንዳመጸ ነው!

August 23, 2017 09:02 pm by Editor 1 Comment

  • ለፖለቲከኞች እስር እውቅና የሰጡ “ፓርቲዎች” እየተደራደሩ – ሕዝብ እያመጸ ወዴት?

“እንወክለዋለን” በሚሉት ሕዝብ ዘንድ እውቅና ያላቸው ተቀናቃኝ ፓርቲዎች እጅግ አነስተኛ እንደሆኑ ይነገራል። አብዛኞቹ በምርጫ ቦርድ እውቅና ያገኙት የፖለቲካ ፓርቲዎች “ጥቂት” ከተሰኙት ውጪ ስለመኖራቸው እንኳን እንደማይታወቁ በተደጋጋሚ አስተያየት ይሰጣል። እነዚህን ፓርቲዎች ሰብሰቦ ድርድር መቀመጥ የአገሪቱን ችግር ማስተንፈስ እንደማይቻል የሚከራከሩ ወገኖች ድርድሩን አያከብሩትም። በሌላ በኩል ደግሞ ህወሓት/ኢህአዴግ እዚህ ደረጃ መምጣቱ በራሱ አንድ ርምጃ ነው የሚሉና ድጋፋቸውን የሚሰጡ ጥቂት አይደሉም። በውጤቱ ሲታይ ግን አመጹም፣ ቅሬታውም፣ ችግሩም መልኩን ሲቀያይር እንጂ ሲለዝብ ማስተዋል አልተቻለም።

ለዚህም ይመስላል የኦፌኮ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ሙላቱ ገመቹ “ከሚመለከታቸው ወገኖች ጋር ቁጭ ብሎ ከመወያየት ሌላ አማራጭ የለም” ሲሉ ለቪኦኤ የተናገሩት። የፖለቲካ መፍትሄ ለመፈለግ ንግግር እየተደረገ ባለበትና “ተደራዳሪ የሚባሉት” ብዙ ርቀት መሄዳቸውን በሚናገሩበት ወቅት “ሌላ አማራጭ የለም” ሲሉ አቶ ሙላቱ መፍትሄ ስለሚያስገኝ እውነተኛ ድርድር መናገራቸው ለንግግሩ እውቅና የመንፈግና መፍትሄ እንደማያመጣ አመላካች ስለመሆኑ ሂደቱን የሚከታተሉ የሚሰጡት አስተያየት ነው።

ህወሓት/ኢህአዴግ እና ተደራዳሪዎቹ ፓርቲዎች እያካሄዱት ካለው ድርድር በአገሪቱ ዴሞክራሲ እንዲጎለብት የሚያስችል ውጤት እንደሚገኝ፣ ፍትሃዊ ምርጫ የሚደረግበት አግባብ እንደሚፈጠር፣ እንዲሁም የመቻቻል ሃሳብና የፖለቲካው ምህዳር እንደሚሰፋ ተስፋ በሚሰጡበት ወቅት በአማራና በኦሮሚያ ተደጋጋሚ አድማ መካሄዱ የድርድሩን ውጤት ከወዲሁ አመላካች አድርጎታል። በዚህ ጉዳይ ላይ ቀደም ሲል ጀምሮ የሚሰጠው አስተያየት ሲጠቃለል “የሚሰሙና ተቀባይነት ያላቸው ፓርቲዎች ችግሩ ከመከሰቱ በፊት ያቀረቡት የድርድር ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቶ ቢሆን ኖሮ፣ ህዝቡን አርፈህ ተቀመጥ፣ የድርድሩን ውጤት ጠብቅ በማለት ሊገስጹት በቻሉ ነበር። ከዚህም በላይ አመጹን ለመቆጣጠር በተወሰደው የሃይል ርምጃ የጠፋውን ሰብዓዊና ቁሳዊ ውድመት ማስቆም በተቻለ …”

የእንደራደር ጥያቄ ቢኖርም በተለያየ ወቅት አግባብ ያለው ምላሽ ባለማግኘቱ፣ የአገሪቱ ፖለቲካ ምህዳር መጥበቡና የዴሞክራሲ መብቶች መገደባቸው ጋር ተዳምሮ ዛሬ ላይ ደርሷል። ይህ ክልላዊ ስሜት የተላበሰው አመጽ ህወሓት/ኢህአዴግን እንደ አገዳ ውስጥ ውስጡን ሲበላው ቆይቶ ዛሬ ሲፈነዳ “በጥልቅ ተሃድሶ በአስር ሺህ የሚቆጠሩትን አባሎቼን አባረርኩ” በማለት አደባባይ አባላቱ እንደተንሸራተቱበት በራሱ አንደበት ለማመን ተገዷል።

ኢህአዴግ “ራሴን አጽድቼ፣ የመልካም አስተዳድር ችግሮችን ፈትቼ፣ የፖለቲካ ድርድር አካሄጄ፣ ለስራ አጦች በቢሊዮን ብር መድቤ፣ የኢንዱስትሪ አብዮት አካሂጄ፣ ታርሜና ታድሼ…” በማለት ከአመጹ ማግስት ጀምሮ ቃል እየገባ ቢመጣም ቦግ ድርግም የሚለው አመጽ ግን እየሰፋና መልኩን እየለወጠ፣ በስልትም እየጠለቀ መሄዱን ገለልተኛ ወገኖች እየመሰከሩ ነው። “ታድሼያለሁ፣ ቀድሞ የከዱኝን አባርሬ አዲስ ቁርጠኛ አባላትን መልምዬ ለሃላፊነት አብቅቻለሁ” ቢልም የክልላዊ አስተሳሰብ በዜናና በፕሮፓጋንዳ እንዲሁ በቀላሉ የሚተን ባለመሆኑ ሌላ ኢህአዴግ አማራጭ ፖለቲካዊ ርምጃ መወሰዱ እንደሚሻለው አገር ወዳዶች እየመከሩ ነው።

ከማስተር ፕላን ጋር በተያያዘ የተጀመረው የኦሮሚያ ሕዝባዊ አመጽ አድማሱን ወደ አማራ ክልል በማስፋት በማንነት ጥያቄ ሲታጀብ የፈጠረው ድንጋጤ አሁን ድረስ እንዳለ ነው። ኢህአዴግ አመጹ የተቀጣጠለው በራሱ ችግር እንደሆነ አምኖ የማስተር ፕላኑን ሃሳብ መጣሉን በማወጅ የኦሮሚያን ተቃውሞ ሊያስተነፍስ ቢሞክርም አልሆነም። አሁን እንደሚነገረውና የዓይን ምስክሮች እንደሚሉት ሶስተኛ የተባለ ሕዝባዊ አመጽ ተጀምሯል። በአማራ ክልልም በተመሳሳይ ከቤት ውስጥ ያለመውጣት አድማ ለማስጀመር ዝግጅት እንዳለ እየተሰማ ነው።

“ቄሮ የኦሮሞ ወጣቶች” የሚባሉትን የህቡዕ አደራጆችን በመጠቀስ ከዛሬ ጀምሮ ለአምስት ቀን የታወጀው ስርዓቱን የመቃወምና ቤት ውስጥ የመቀመጥ አድማ ተግባራዊ የሆነባቸው ከተሞችን በመዘርዘርና የዓይን እማኞችን በማነጋገር “ገለልተኛ” የሚባሉ ሚዲያ ይፋ አድርገዋል። የኦሮሚያ ሚዲያ ኔት ዎርክ እና ኢሳት ለዜናው ቅድሚያ ቢይዙም ቪኦኤ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ በሚገኘው ዘጋቢው አማካይነት ሃተታ አቅርቧል።

በዚሁ ዜና ላይ እንደተመለከተው ከሻሸመኔ፣ ከአምቦ፣ ከነቀምት እማኞች ስማቸው እንዳይጠቀሰ ጠይቀው ያዩትን ተናገረዋል። ሶስቱም የአይን ምስክሮች እንዳሉት የአድማው ምክንያት የታሰሩ የፖለቲካ መሪዎቻችን ይፈቱ፣ ያላ አግባብ የተጣለው የገቢ ግብር ይነሳ፣ በኦሮሚያና ሶማሌ ክልል የሚፈሰውን ደምና የድንበር ግጭት መንግስት ያስቁም የሚሉ ናቸው። የሻሸመኔው አስተያየት ሰጪ ግን “ህዝቡ በጠመንጃ አፈሙዝ አንገዛም ነው የሚለው” ሲሉ ተደምጠዋል።

በሻሸመኔ ሁለት ሆኖ መራመድ እንደማይቻል፣ እቤት ውስጥ አድሞ መቀመጥ ክልክል መሆኑንን፣ ታጣቂዎች ቤት ድረስ እየገቡ እንደሚደባደቡና በግድ ውጡ እንደሚሉና በከተማው በግድ ሱቅ ክፈቱ በሚል ማስፈራራት ይደረግ እንደነበር አስረድተዋል።

የነቀምቴው አስተያየት ሰጪ የመንግሥት ሰራተኛ መሆናቸውን ተናገረው “አንድ ሁለት ሱቆች ተከፍተው ነበር” ካሉ በኋላ፣ ከአድማው መጀመር አንድ ቀን በፊት ካቢኔው ተሰብስቦ የመንግሥት ሰራተኞች ከስራ ቢቀሩ እንደሚታሰሩና ከስራ እንደሚባረሩ ማስፈራሪያ በአለቆች በኩል መላካቸውን ተናግሯል።

ከአዲስ አበባ ዙሪያ የኦሮሚያ ከተሞች ጀምሮ በተለያዩ የኢትዮጵያ ከተሞች የተጀመረው የቤት ውስጥ መቀመጥ አድማ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል፣ ውጤታማ እንደሚሆንና ተከታታይ የተጠኑ ስልቶች እንደሚተገበሩ እንቅስቃሴውን ከዳያስፖራ ሆነው ይመራሉ የሚባሉ ወገኖች ሲናገሩ ተደምጧል።

ሌንጮ ለታ የሚመሩት የኦዴግ ከፍተኛ አመራር የሆኑት በያን አሶባ በበኩላቸው ትግሉ ሁሉን አቀፍ በመሆኑ መላውን አገሪቱን በሚያስተባበር መልኩ ሊቀጥል እንደሚገባ አመልከተዋል። በኢሳት አማካይነት ከአንድ ቀን በፊት ድምጻቸውን ያሰሙት ዶ/ር በያን ትግሉ የመላው ኢትዮጵያውያን እንደሆነ መጠቆማቸውን ተከትሎ አድማው በአማራ ክልልም ለማስጀመር ዝግጅት መጀመሩን ለማወቅ ተችሏል።

የዛሬ ዓመት የኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጠኛ JEFFREY GETTLEMAN በኢትዮጵያ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ የተነተነበትን ጽሁፍ ጎልጉል ባቀረበበት ወቅት ይህን የጋዜጠኛውን ቃል ጠቅሶ ዘግቦ ነበር፤ “ሕዝቡን ካፈንከው እና ከመቃወም ሌላ አማራጭ ካሳጣኸው ይፈነዳል፤ ወጣቱ በሙሉ ዓመጽ ላይ ነው፤ ትውልድ አምጿል”፡፡ (ከዜና ዘገባው ጋር Violent Protests in Ethiopia በሚል ርዕስ የጸጥታ ኃይሎች ሰላማዊ ሰልፍ በወጣ ህዝብ ላይ የሚፈጽሙትን  አሰቃቂ ግፍ እና ጨካኝ ድብደባ እዚህ ላይ መመልከቱ የግድ ይላል)፡፡

ይህንን መሰሉን ግፍ እና በጠብመንጃ የታገዘ የግፍ አገዛዝ ሕዝብ አልቀበልም ማለቱ የሚጠበቅ እንጂ የሚያስገርም ጉዳይ አለመሆኑን የሚናገሩ ወገኖች፤ በአማራና በኦሮሚያ መካከል የትግል ትብብር ማድረግ የህወሓት/ኢህአዴግን ጉልበት እንደሚያርደው አሁንም ይመክራሉ፡፡ ባለፈው በተነሳው ሕዝባዊ ተቃውሞ ይህ መሰሉ ትብብር ያስደነገጠው ህወሓት በተጨነቀበትና በሚዲያ ወጥቶ ራሱን ባጋለጠበት ወቅት በተለይ ከዳያስፖራ የሚነዛ የነበረው በዘር የመከፋፈል ጠባብ አስተሳሰብ ህወሓት/ኢህአዴግን እንደገና እንዲሰነብት አስችሎታል ይላሉ፡፡ ሕዝብ በጠብመንጃ አልገዛም ካለ ቆይቷል፤ ወጣቱ ትውልድም አምጿል፤ ፖለቲካውን እንመራዋለን የሚሉት ግን ይህ የገባቸው አይመስልም ወይም በአፋቸው ሕዝባዊ በልባቸው ግላዊ ሆነዋል፡፡

(በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ የተለያዩ ከተሞች የተካሄዱትን የቤት ውስጥ አድማ ፎቶዎች ከዚህ በታች ለዕይታ አቅርበናል፤ ምንጫቸው ያልተጠቀሰው ፎቶዎች በሙሉ የተገኙት ከStar.com.tr ድረገጽ ነው)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Ras Dejen says

    August 25, 2017 10:06 am at 10:06 am

    At any cost, TPLF should go to the pit;
    No sovereign Ethiopia, no nationhood with this shit junta in Ethiopia!
    First we close Western shelters against TPLF;
    Then cleaning Ethiopia from the dirt (TPLF)!

    TPLF is assigned to dislodge Ethiopia. It is a well engineered project.
    There is a lot to draw from this accurate theological account: https://www.youtube.com/watch?v=pvP7vVQ8NGU

    Ethiopia will regain its sovereignty and cause liberty to others again!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule