• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኦህዴድ ኢህአዴግን ከዳ

December 19, 2015 03:21 am by Editor 8 Comments

በበርካታ የኦሮሚያ ከተሞች የተቀሰቀሰው ሕዝባዊ ንቅናቄ የኦህዴድን መክዳት የሚያሳይ መሆኑ ተጠቆመ፡፡ ከንቅናቄው ጋር በተያያዘ ህወሃት/ኢህአዴግ ጥቅሙን ለማስከበር የትግራይ ወጣቶችን ለ“ብሔራዊ” ውትድርና እየጠራ መሆኑ ተሰማ፡፡

ሳምንታት ያስቆጠረውና የአዲስ አበባ ማስተር ፕላንን ምክንያት በማድረግ የተነሳው ሕዝባዊ እንቅስቃሴ በመጠኑም ሆነ በዓይነቱ ልዩ እየሆነ መሄዱ ኦህዴድ ኢህአዴግን የመክዳቱ ማስረጃ ነው ሲሉ በኦሮሚያ ጉዳዮች ላይ ለጎልጉል መረጃ የሚያቀብሉ አመራር አስታውቀዋል፡፡

በኢህአዴግ የአንድ ለአምስት ጥርነፋ፤ ስለላ፤ ሕዝባዊ አደረጃጀት፤ ቁጥጥር፤ … መዋቅሮችን ሁሉ አልፎ ይህንን ያህል ሕዝብ ያለአንዳች ከልካይ መውጣቱ አገዛዙ ሕዝቡን ለመጠርነፍ የተጠቀመበት አሠራር መልሶ ራሱን እየጠረነፈው እንደሆነ የሚያሳይ ነው፡፡ ታማኝ ተብሎ የተቀመጠው ካድሬም ሆነ የጥርነፋው መዋቅር ሕዝቡን ሊያስቆም አለመቻሉ የኦህዴድ እምቢተኛነትና ለአገዛዙ ድጋፍና እገዛ ከማድረግ ይልቅ ከሕዝቡ ጋር ለመቆሙ እንደ ዓይነተኛ ማስረጃ ይጠቀሳል፡፡

በኢህአዴግ ውስጥ ያለው የተዛባ አመራር እንዲሁም የኃይል (የሥልጣን) ሚዛን አለመስተካከል በኦሮሚያ ውስጥ ኢህአዴግን ተቀባይነት እያሳጣው ከመሄዱ ባሻገር ሕዝቡን “ኦነግ፤ አሸባሪ፤…” በማለት ህወሃት/ኢህአዴግ እስርቤቱን “ኦሮምኛ ተናጋሪ” እንዳደረገው በስፋት ሲነገር የቆየ ነው፡፡ የአዲስ አበባ ማስተር ፕላንን በተመለከተ የቀረበውን ዕቅድ ከደገፉት ሙክታር ከድርና አስቴር ማሞ በስተቀር የተቀረው የኦህዴድ አመራር በኢህአዴግ እምነት የሚጣልበት ባለመሆኑ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ኦህዴድ ኦሮሚያን የማስተዳደር ውክልናው ቆሞ ክልሉ ህወሃት በሚቆጣጠረው ደኅንነት እየተመራ መሆኑ አብሮ የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡

ኦህዴድ የሚታመን ባለመሆኑ ክልሉን የማረጋጋትም ሆነ የመምራት ኃላፊነት በመነፈጉ ኦህዴድ እና ኢህአዴግን የሚያስተሳስረው የመጨረሻ ገመድ ተበጥሷል፤ ከዚህ ሕዝባዊ ንቅናቄ ኢህአዴግ ማንሰራራት ቢችል እንኳን በአዲስ የሚፈጥረው ኦህዴድ ከቀድሞው ፍጹም የተለየ እንደሚሆን ይህንን ለማድረግ በራሱ ለህወሃት/ኢህአዴግ ፈታኝ እንደሆነ አብሮ ተጠቁሟል፡፡

ከኦህዴድ መክዳት ጋር በተያያዘ ህወሃት/ኢህአዴግ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የተነሳውን ሕዝባዊ ንቅናቄ በቁጥጥር ሥር ለማዋል የሚችል የሚያምነው ኃይል ባለመኖሩ የትግራይ ወጣቶች እንደ ብሔራዊ ውትድርና ዓይነት ግዳጅ መጠራታቸው ተሰምቷል፡፡ በኢትዮጵያም ሆነ በኢህአዴግ ውስጥ የህወሃት የጥቅም ተጽዕኖ ግልጽ በመሆኑ ይህንን ጥቅም ለማስጠበቅ የትግራይ ወጣቶች መስዋዕትነት የሚከፍሉበት ግዳጅ አሁን ነው በማለት ለአገልግሎት ተጠርተዋል፡፡

“አገርህን አድን” በሚል ዓይነት ጥሪ ወንድሟ ወደ ውትድርና መሄዱን በለቅሶ የተናገረች በአውሮጳ የምትገኝ እንዳለችው ከሆነ ይህ ዓይነቱ ግዳጅ ለምን ያህል ጊዜ እንደሚቆይ ምንም መረጃ እንደሌላት ተናግራለች፡፡ ወንድሟ በምን ዓይነት ለህይወት የሚያሰጋ ግዳጅ ላይ እንደሚሰማራም ካሁኑ ለማወቅ እንደማይቻል በማስረዳት እሷም ሆነች ቤተሰቧ በከፍተኛ ሃዘንና ጭንቀት ውስጥ እንደሚገኙ በመረበሽ አስረድታለች፡፡ ከትግራይ የተገኙ መረጃዎች እንዳመለከቱትም ወጣቶች ለተመሳሳይ ወታደራዊ ግዳጅ እየተጠሩ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡

በኦሮሚያ ሕዝቡ ያስነሳው የተቃውሞ ንቅናቄ ቀጥሎ በዛሬውም ዕለት በተለያዩ ቦታዎች በስፋት ቀጥሏል፡፡ በህወሃት/ኢህአዴግ የሚወሰደው እርምጃ የዚያኑ ያህል የቀጠለ ሲሆን በኦፊሺያል ከሚሰጠው ቁጥር በበለጠ መልኩ እስካሁን ከመቶ በላይ ሰዎች መገደላቸው በስፋት በማኅበራዊ ሚዲያዎች ይነገራል፡፡ በህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ የተመረሩ ኃይሎች በሁሉም ክልሎች የሚኖረው ሕዝብ እንዲሁም በውጭ አገር ያለው በኅብረት መንቀሳቀስ እንዳለበት ያሳስባሉ፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Abebe says

    December 19, 2015 11:39 am at 11:39 am

    እናንተ ፀረ-ኢትዮጵያዊያን መቼ ይሆን የኢትዮጵያን ጥፋት ከመመች የምታቆሙት? ስለምንስ ወንድም በወንድሙ ላይ እንዲነሳ ክብሪት ትጭራላችሁ? በሰው ደም መዝናናትስ ለምን ህሊናችሁ ፈቀደ? ለመሆኑ አንድ ዘገባ በሚዲያ ሲወጣ ለሀገር ያለውን ፋይዳ ትገነዘባላችሁ? ዘለፋና ጥላቻን በመስበክ በእስካሁን ጉዟችሁ ምን አተረፋችሁ? ብቻ እግዚአብሄር ልቦና ይስጣችሁ እንጂ ሌላ ምን ይባላል?!!!!!!

    Reply
    • Abebe says

      December 20, 2015 03:14 pm at 3:14 pm

      Abebe bileh melse yetsafkew, ante simih Hagos newe

      Reply
    • aradaw says

      January 6, 2016 10:42 pm at 10:42 pm

      I am really sorry for TPLF people, they can not see beyond their interest and benefit. Anyone who says enough is enough is ፀረ-ኢትዮጵያዊ, when does this stops. TPLF politically marginalized most Ethiopians, economically exploited and recently busy killing innocent Ethiopians for voicing exploitation, oppression. ስለምንስ ወንድም በወንድሙ ላይ እንዲነሳ ክብሪት ትጭራላችሁ? It is shame a genuine Ethiopian saying this. TPLF has divided and ruled Ethiopia for the last 25 years, enough is enough. ለሀገር ያለውን ፋይዳ ትገነዘባላችሁ? Hager means for TPLF exploitation and nothing else. እግዚአብሄር ልቦና ይስጣችሁ for all of us.

      Reply
  2. Bilisuma Seba says

    December 19, 2015 06:26 pm at 6:26 pm

    Ethiopia is not the property of TPLF.PLEASE tell them etio. is the country of nations and nationality.

    Reply
  3. alebel says

    December 20, 2015 08:32 am at 8:32 am

    asazagn new

    Reply
  4. Tomas says

    December 20, 2015 01:55 pm at 1:55 pm

    woyane leyelih zendiro k addis ababa bizu sew ende IsIs tebabren enatefachuhalen !

    Reply
  5. balcha says

    December 22, 2015 03:25 pm at 3:25 pm

    Tplf has been begged and begged to make national arbitration. Tplf ignored it b/c it said it is the bravest of all and only on it’s grave such thing could happen. Tplf humiliated greater clans by insulting irresponsibly. Tigray people never condemned any atrocity of tplf so far it is now the turn of the majority.

    Reply
  6. Kebede says

    December 23, 2015 02:38 pm at 2:38 pm

    It is lie. There is no national service in tigray. This a propganda and hate.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule