• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ነጻ አውጪ ግምባር አገዛዝ እንጂ መንግሥት አይመሠርትም

October 9, 2015 08:12 am by Editor 1 Comment

ላለፉት 25 ዓመታት በነጻ አውጪ ግምባር ስም ኢትዮጵያን እየገዛ ያለው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር “ኢህአዴግ” ብሎ በፈጠረው ስያሜ አገር በግፍ እየገዛ መሆኑ ሳያንስ በየአምስት አመቱ በሚያካሂደው “ምርጫ” የሚመሠርተው “መንግሥት” መፍትሔ ሊሰጥ እንደማይችል መድረክ አስታወቀ። ሰማያዊ ፓርቲ በበኩሉ በኢትዮጵያ ለተከሰተው ረሃብ የአገዛዙ ፓርቲ ተጠያቂ ነው ይላል።

የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ “ኢህአዴግ ያቋቋመው መንግስት መፍትሄ አይሰጥም ተባለ” በሚል ርዕስ ያወጣው ዜና ከዚህ እንደሚከተው ይነበባል:-

ኢትዮጵያ ውስጥ እየተስተዋለ ያለው ረሃብ የገዥው ፓርቲን ፖሊሲ ውድቀት ያሳያል ሲል ሰማያዊ ፓርቲ ከሰሰ፡፡

ኢህአዴግ ያቋቋመዉ አምባገነን መንግስት ለኢትዮጵያ መሰረታዊ ችግሮች መፍትሄ ሊሰጥ አይችልም ሲል ታቃዋሚዉ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ አስታወቀ።

የ2007ቱን የምርጫ ሂደት የተቹት አመራሮቹ ህግ ወጥ የሆነ ነገር እየተንከባለለ መጥቶ መንግሥት ምስረታ ላይ ደርሷል ብላል።

በተያያዘ ዜናም የፊታትን ቅዳሜና እሁድ በጠቅላይ ሚንስትር ደሳለኝ ኃይለማሪያም ሰብሳቢነት የሚካሄደው የእድገትና የለውጥ ሽግግር እቅድ ስብሰባ ላይ ቢጋበዙም የማይገኙ መሆናቸውን የተለያዩ ተቃዋሚ ፓርቲዎች እየገለጹ ነው።

መድረክ የሰጠዉን መግለጫ የተከታተለው እስክንድር ፍሬዉ ተከታዮን ዘግቧል። ለማዳመጥ እዚህ ላይ ይጫኑ።

ይህ በ እንዲህ እንዳለ የሰማያዊ ፓርቲ “ረሃቡ የገዥው ፓርቲ የፖሊሲ ውድቀት ነው!” በሚል ርዕስ የሚከተለውን መግለጫ ሰጥቶዋል:-

ገዥው ፓርቲ ስልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ ህዝብ በቀን ሶሰት ጊዜ እንደሚመግብ ቃል ሲገባ ቆይቷል፡፡ በተለይ ባለፉት 10 አመታት ጀምሮ ኢኮኖሚውን በሁለት ዲጅት እያሳደገ እንደሚገኝ ልሳኑ ባደረጋቸው የመንግስት ብዙሃን መገናኛዎች በረሃብና በርዛት እየተሰቃየ ለሚገኘው ህዝብ መልሶ እየነገረ ይገኛል፡፡ ይሁንና ይህ ስርዓቱ ሀገሪቱን ወደመካከለኛ ገቢ ያደርሳል የሚለው እድገት ለጥቂት ጊዜያት በተከሰተና በተለመደ የዝናብ እጥረት የሚከሰትን ድርቅ እንኳ መቋቋም አቅቶት ዜጎቻችን በተደጋጋሚ የረሃብ ሰለባ ሲሆኑ ቆይተዋል፡፡

በተለይ በዚህ ወቅት በመላ ሀገሪቱ የተከሰተው አስደንጋጭ የረሃብ አደጋ ዜጎችን ለከፋ ስቃይና መከራ ዳርጓቸዋል፡፡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ከ7.5 ሚሊዮን በላይ ዜጎቻችን ለከፋ የረሃብ አደጋ ተጋልጠዋል፡፡ ከ40 ሺህ በላይ ህፃናት የረሃቡ ሰለባ ሆነዋል፡፡ ከግጦሽና ከውሃ እጥረት የተነሳ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የቤት እንሰሳት እየሞቱ ነው፡፡ ረሃቡ ባልጠናባቸው አካባቢዎች ሳይቀር አርሶ አደሩም ሆነ አርብቶ አደሩ ነፍሱን ለማዳን የእርሻ በሬዎቹን ሳይቀር ለገበያ እያቀረበ በርካሽ ዋጋ ለመሸጥ ተገዷል፡፡

ገዥው ፓርቲ ችግር ቢከሰት እንኳ በአደጋ ጊዜ ለዜጎች የሚበቃ እርዳታ አቀርባለሁ ሲል የነበረ ቢሆንም ለወገኖቻችን ግን የሚደርስላቸው አልተገኘም፡፡ ይባስ ብሎም ለዜጎች ዓለም አቀፍ ተቋማት እንዳይደርሱላቸው የተፈጠረው ረሃብ የራሱ የፖሊሲ ውድቀት መሆኑን የሚያውቀው ስርዓቱ የዜጎቻችን ስቃይና መከራ ሲሸፋፍን ከርሟል፡፡ ከአቅሙ በላይ ሲሆን ችግሩ እንደተከሰተ ቢገልፅም ለዜጎች ተገቢውን እርዳታ በሚያስገኝ መልኩ እርምጃ እየወሰደ አይደለም፡፡ በአሁኑ ወቅት በኦሮሚያ፣ በአፋር፣ በደቡብ፣ ትግራይ፣ በአማራ፣ በሶማሊና በሌሎቹም ክልሎች በተከሰተው ረሃብ ዜጎች ከፍተኛ ችግር ላይ ናቸው፡፡ ለተከሰተው የረሃብ አደጋ ተገቢው ትኩረት መነፈጉ ገዥው ፓርቲ እመራዋለሁ ለሚለው ህዝብ ደንታ ቢስነቱን የሚያረጋግጥ ነው፡፡ ረሃቡ፣ ርዛቱ፣ ድህነቱ፣ ስደቱ፣ ስራ አጥነቱ፣ የኑሮ ውድነቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ ዜጎችን በብርቱ እየተፈታተኑ በሚገኝበት ወቅት ገዥው ፓርቲና በስሩ ያሉ ድርጅቶች ተመሰረትንበት የሚሉትን ጊዜ ለወራት በቅንጦት በማክበት በብዙ ሚሊዮን ገንዘብ ከኢትዮጵያውያን ጉሮሮ ነጥቆ ድግስ ሲደግስና አሸሸ ገዳሜ ሲል በርካታ ኢትዮጵያውያንን አሳዝኗል፡፡

ለተከሰተው ረሃብ ኢህአዴግ ለይስሙላ ቆሜለታለሁ የሚለውን አርሶ አደርና አርብቶ አደርን ህይወት ለማሻሻል የረባ ስራ እንዳልሰራ ያረጋገጠ ነው፡፡ ግብርናው ኢኮኖሚውን ይመራል ቢልም እስካሁን ግን በየአመቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን የረሃብ ሰለባ እንደሆነ ቀጥለዋል፡፡ መሬት የመንግስት ነው በሚል ሽፋን አርሶ አደሩን ከቀየው እያፈናቀለ ለስርዓቱና ደጋፊዎችና ለባዕዳን መሬትን እየሸጠ አርሶ አደሩን ለረሃብ ተጋላጭ አድርጎታል፡፡ በስርዓቱ የፖሊሲ ውድቀት የተፈጠረውን አደጋ ለመሸፋፈን በሚያደርገው ጥረትም በርካታ ኢትዮጵያውያንን የችግሩ ሰለባ እየሆኑ ነው፡፡

ቢዘገይም ፓርቲያችን ሰማያዊ ገዥው ፓርቲ ለወገኖቻችን የሲቃ ድምፅ ጆሮ ዳባ ማለቱን አቁሞ አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስድ እንጠይቃለን፡፡ በተለይ ስለ ችግሩ ለኢትዮጵያውያንና ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ስለ ረሃቡ በደንብ የሚያስረዳ ገለልተኛ አካል ተቋቁሞ ለዜጎቻችን መፍትሄ እንዲፈለግ እንጠይቃለን፡፡ ስርዓቱ ደካማና ኃላፊነት የጎደለው እንደመሆኑ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ኢትዮጵያውያንና የዓለም ማህረሰብ ከወገኖቻችን ጎን እንዲቆሙ ጥሪ እናቀርባለን፡፡ በዋናነት ግን ይህ የኢትዮጵያውያን መከራ የመነጨው ከገዥው ፓርቲ የተሳሳተ ፖሊሲ፣ የአፈፃፀም ብቃት ችግርና ለኢትዮጵያውያንም ባለው ግድየለሽነት መሆኑን ተገንዝበን ይህን ለችግሮቻችን ምንጭ የሆነ ስርዓት በቁጥርጠኝነት መታገል እንዳለብን ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

ድል የህዝብ ነው!

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!

መስከረም 27 ቀን /2008 ዓ.ም

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Opinions Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. tsegaye jigso says

    October 10, 2015 11:58 am at 11:58 am

    good

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule