• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ነጻ አውጪ ግምባር አገዛዝ እንጂ መንግሥት አይመሠርትም

October 9, 2015 08:12 am by Editor 1 Comment

ላለፉት 25 ዓመታት በነጻ አውጪ ግምባር ስም ኢትዮጵያን እየገዛ ያለው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር “ኢህአዴግ” ብሎ በፈጠረው ስያሜ አገር በግፍ እየገዛ መሆኑ ሳያንስ በየአምስት አመቱ በሚያካሂደው “ምርጫ” የሚመሠርተው “መንግሥት” መፍትሔ ሊሰጥ እንደማይችል መድረክ አስታወቀ። ሰማያዊ ፓርቲ በበኩሉ በኢትዮጵያ ለተከሰተው ረሃብ የአገዛዙ ፓርቲ ተጠያቂ ነው ይላል።

የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ “ኢህአዴግ ያቋቋመው መንግስት መፍትሄ አይሰጥም ተባለ” በሚል ርዕስ ያወጣው ዜና ከዚህ እንደሚከተው ይነበባል:-

ኢትዮጵያ ውስጥ እየተስተዋለ ያለው ረሃብ የገዥው ፓርቲን ፖሊሲ ውድቀት ያሳያል ሲል ሰማያዊ ፓርቲ ከሰሰ፡፡

ኢህአዴግ ያቋቋመዉ አምባገነን መንግስት ለኢትዮጵያ መሰረታዊ ችግሮች መፍትሄ ሊሰጥ አይችልም ሲል ታቃዋሚዉ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ አስታወቀ።

የ2007ቱን የምርጫ ሂደት የተቹት አመራሮቹ ህግ ወጥ የሆነ ነገር እየተንከባለለ መጥቶ መንግሥት ምስረታ ላይ ደርሷል ብላል።

በተያያዘ ዜናም የፊታትን ቅዳሜና እሁድ በጠቅላይ ሚንስትር ደሳለኝ ኃይለማሪያም ሰብሳቢነት የሚካሄደው የእድገትና የለውጥ ሽግግር እቅድ ስብሰባ ላይ ቢጋበዙም የማይገኙ መሆናቸውን የተለያዩ ተቃዋሚ ፓርቲዎች እየገለጹ ነው።

መድረክ የሰጠዉን መግለጫ የተከታተለው እስክንድር ፍሬዉ ተከታዮን ዘግቧል። ለማዳመጥ እዚህ ላይ ይጫኑ።

ይህ በ እንዲህ እንዳለ የሰማያዊ ፓርቲ “ረሃቡ የገዥው ፓርቲ የፖሊሲ ውድቀት ነው!” በሚል ርዕስ የሚከተለውን መግለጫ ሰጥቶዋል:-

ገዥው ፓርቲ ስልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ ህዝብ በቀን ሶሰት ጊዜ እንደሚመግብ ቃል ሲገባ ቆይቷል፡፡ በተለይ ባለፉት 10 አመታት ጀምሮ ኢኮኖሚውን በሁለት ዲጅት እያሳደገ እንደሚገኝ ልሳኑ ባደረጋቸው የመንግስት ብዙሃን መገናኛዎች በረሃብና በርዛት እየተሰቃየ ለሚገኘው ህዝብ መልሶ እየነገረ ይገኛል፡፡ ይሁንና ይህ ስርዓቱ ሀገሪቱን ወደመካከለኛ ገቢ ያደርሳል የሚለው እድገት ለጥቂት ጊዜያት በተከሰተና በተለመደ የዝናብ እጥረት የሚከሰትን ድርቅ እንኳ መቋቋም አቅቶት ዜጎቻችን በተደጋጋሚ የረሃብ ሰለባ ሲሆኑ ቆይተዋል፡፡

በተለይ በዚህ ወቅት በመላ ሀገሪቱ የተከሰተው አስደንጋጭ የረሃብ አደጋ ዜጎችን ለከፋ ስቃይና መከራ ዳርጓቸዋል፡፡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ከ7.5 ሚሊዮን በላይ ዜጎቻችን ለከፋ የረሃብ አደጋ ተጋልጠዋል፡፡ ከ40 ሺህ በላይ ህፃናት የረሃቡ ሰለባ ሆነዋል፡፡ ከግጦሽና ከውሃ እጥረት የተነሳ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የቤት እንሰሳት እየሞቱ ነው፡፡ ረሃቡ ባልጠናባቸው አካባቢዎች ሳይቀር አርሶ አደሩም ሆነ አርብቶ አደሩ ነፍሱን ለማዳን የእርሻ በሬዎቹን ሳይቀር ለገበያ እያቀረበ በርካሽ ዋጋ ለመሸጥ ተገዷል፡፡

ገዥው ፓርቲ ችግር ቢከሰት እንኳ በአደጋ ጊዜ ለዜጎች የሚበቃ እርዳታ አቀርባለሁ ሲል የነበረ ቢሆንም ለወገኖቻችን ግን የሚደርስላቸው አልተገኘም፡፡ ይባስ ብሎም ለዜጎች ዓለም አቀፍ ተቋማት እንዳይደርሱላቸው የተፈጠረው ረሃብ የራሱ የፖሊሲ ውድቀት መሆኑን የሚያውቀው ስርዓቱ የዜጎቻችን ስቃይና መከራ ሲሸፋፍን ከርሟል፡፡ ከአቅሙ በላይ ሲሆን ችግሩ እንደተከሰተ ቢገልፅም ለዜጎች ተገቢውን እርዳታ በሚያስገኝ መልኩ እርምጃ እየወሰደ አይደለም፡፡ በአሁኑ ወቅት በኦሮሚያ፣ በአፋር፣ በደቡብ፣ ትግራይ፣ በአማራ፣ በሶማሊና በሌሎቹም ክልሎች በተከሰተው ረሃብ ዜጎች ከፍተኛ ችግር ላይ ናቸው፡፡ ለተከሰተው የረሃብ አደጋ ተገቢው ትኩረት መነፈጉ ገዥው ፓርቲ እመራዋለሁ ለሚለው ህዝብ ደንታ ቢስነቱን የሚያረጋግጥ ነው፡፡ ረሃቡ፣ ርዛቱ፣ ድህነቱ፣ ስደቱ፣ ስራ አጥነቱ፣ የኑሮ ውድነቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ ዜጎችን በብርቱ እየተፈታተኑ በሚገኝበት ወቅት ገዥው ፓርቲና በስሩ ያሉ ድርጅቶች ተመሰረትንበት የሚሉትን ጊዜ ለወራት በቅንጦት በማክበት በብዙ ሚሊዮን ገንዘብ ከኢትዮጵያውያን ጉሮሮ ነጥቆ ድግስ ሲደግስና አሸሸ ገዳሜ ሲል በርካታ ኢትዮጵያውያንን አሳዝኗል፡፡

ለተከሰተው ረሃብ ኢህአዴግ ለይስሙላ ቆሜለታለሁ የሚለውን አርሶ አደርና አርብቶ አደርን ህይወት ለማሻሻል የረባ ስራ እንዳልሰራ ያረጋገጠ ነው፡፡ ግብርናው ኢኮኖሚውን ይመራል ቢልም እስካሁን ግን በየአመቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን የረሃብ ሰለባ እንደሆነ ቀጥለዋል፡፡ መሬት የመንግስት ነው በሚል ሽፋን አርሶ አደሩን ከቀየው እያፈናቀለ ለስርዓቱና ደጋፊዎችና ለባዕዳን መሬትን እየሸጠ አርሶ አደሩን ለረሃብ ተጋላጭ አድርጎታል፡፡ በስርዓቱ የፖሊሲ ውድቀት የተፈጠረውን አደጋ ለመሸፋፈን በሚያደርገው ጥረትም በርካታ ኢትዮጵያውያንን የችግሩ ሰለባ እየሆኑ ነው፡፡

ቢዘገይም ፓርቲያችን ሰማያዊ ገዥው ፓርቲ ለወገኖቻችን የሲቃ ድምፅ ጆሮ ዳባ ማለቱን አቁሞ አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስድ እንጠይቃለን፡፡ በተለይ ስለ ችግሩ ለኢትዮጵያውያንና ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ስለ ረሃቡ በደንብ የሚያስረዳ ገለልተኛ አካል ተቋቁሞ ለዜጎቻችን መፍትሄ እንዲፈለግ እንጠይቃለን፡፡ ስርዓቱ ደካማና ኃላፊነት የጎደለው እንደመሆኑ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ኢትዮጵያውያንና የዓለም ማህረሰብ ከወገኖቻችን ጎን እንዲቆሙ ጥሪ እናቀርባለን፡፡ በዋናነት ግን ይህ የኢትዮጵያውያን መከራ የመነጨው ከገዥው ፓርቲ የተሳሳተ ፖሊሲ፣ የአፈፃፀም ብቃት ችግርና ለኢትዮጵያውያንም ባለው ግድየለሽነት መሆኑን ተገንዝበን ይህን ለችግሮቻችን ምንጭ የሆነ ስርዓት በቁጥርጠኝነት መታገል እንዳለብን ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

ድል የህዝብ ነው!

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!

መስከረም 27 ቀን /2008 ዓ.ም

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Opinions Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. tsegaye jigso says

    October 10, 2015 11:58 am at 11:58 am

    good

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule