• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ነጻ አውጪ ግምባር አገዛዝ እንጂ መንግሥት አይመሠርትም

October 9, 2015 08:12 am by Editor 1 Comment

ላለፉት 25 ዓመታት በነጻ አውጪ ግምባር ስም ኢትዮጵያን እየገዛ ያለው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር “ኢህአዴግ” ብሎ በፈጠረው ስያሜ አገር በግፍ እየገዛ መሆኑ ሳያንስ በየአምስት አመቱ በሚያካሂደው “ምርጫ” የሚመሠርተው “መንግሥት” መፍትሔ ሊሰጥ እንደማይችል መድረክ አስታወቀ። ሰማያዊ ፓርቲ በበኩሉ በኢትዮጵያ ለተከሰተው ረሃብ የአገዛዙ ፓርቲ ተጠያቂ ነው ይላል።

የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ “ኢህአዴግ ያቋቋመው መንግስት መፍትሄ አይሰጥም ተባለ” በሚል ርዕስ ያወጣው ዜና ከዚህ እንደሚከተው ይነበባል:-

ኢትዮጵያ ውስጥ እየተስተዋለ ያለው ረሃብ የገዥው ፓርቲን ፖሊሲ ውድቀት ያሳያል ሲል ሰማያዊ ፓርቲ ከሰሰ፡፡

ኢህአዴግ ያቋቋመዉ አምባገነን መንግስት ለኢትዮጵያ መሰረታዊ ችግሮች መፍትሄ ሊሰጥ አይችልም ሲል ታቃዋሚዉ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ አስታወቀ።

የ2007ቱን የምርጫ ሂደት የተቹት አመራሮቹ ህግ ወጥ የሆነ ነገር እየተንከባለለ መጥቶ መንግሥት ምስረታ ላይ ደርሷል ብላል።

በተያያዘ ዜናም የፊታትን ቅዳሜና እሁድ በጠቅላይ ሚንስትር ደሳለኝ ኃይለማሪያም ሰብሳቢነት የሚካሄደው የእድገትና የለውጥ ሽግግር እቅድ ስብሰባ ላይ ቢጋበዙም የማይገኙ መሆናቸውን የተለያዩ ተቃዋሚ ፓርቲዎች እየገለጹ ነው።

መድረክ የሰጠዉን መግለጫ የተከታተለው እስክንድር ፍሬዉ ተከታዮን ዘግቧል። ለማዳመጥ እዚህ ላይ ይጫኑ።

ይህ በ እንዲህ እንዳለ የሰማያዊ ፓርቲ “ረሃቡ የገዥው ፓርቲ የፖሊሲ ውድቀት ነው!” በሚል ርዕስ የሚከተለውን መግለጫ ሰጥቶዋል:-

ገዥው ፓርቲ ስልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ ህዝብ በቀን ሶሰት ጊዜ እንደሚመግብ ቃል ሲገባ ቆይቷል፡፡ በተለይ ባለፉት 10 አመታት ጀምሮ ኢኮኖሚውን በሁለት ዲጅት እያሳደገ እንደሚገኝ ልሳኑ ባደረጋቸው የመንግስት ብዙሃን መገናኛዎች በረሃብና በርዛት እየተሰቃየ ለሚገኘው ህዝብ መልሶ እየነገረ ይገኛል፡፡ ይሁንና ይህ ስርዓቱ ሀገሪቱን ወደመካከለኛ ገቢ ያደርሳል የሚለው እድገት ለጥቂት ጊዜያት በተከሰተና በተለመደ የዝናብ እጥረት የሚከሰትን ድርቅ እንኳ መቋቋም አቅቶት ዜጎቻችን በተደጋጋሚ የረሃብ ሰለባ ሲሆኑ ቆይተዋል፡፡

በተለይ በዚህ ወቅት በመላ ሀገሪቱ የተከሰተው አስደንጋጭ የረሃብ አደጋ ዜጎችን ለከፋ ስቃይና መከራ ዳርጓቸዋል፡፡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ከ7.5 ሚሊዮን በላይ ዜጎቻችን ለከፋ የረሃብ አደጋ ተጋልጠዋል፡፡ ከ40 ሺህ በላይ ህፃናት የረሃቡ ሰለባ ሆነዋል፡፡ ከግጦሽና ከውሃ እጥረት የተነሳ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የቤት እንሰሳት እየሞቱ ነው፡፡ ረሃቡ ባልጠናባቸው አካባቢዎች ሳይቀር አርሶ አደሩም ሆነ አርብቶ አደሩ ነፍሱን ለማዳን የእርሻ በሬዎቹን ሳይቀር ለገበያ እያቀረበ በርካሽ ዋጋ ለመሸጥ ተገዷል፡፡

ገዥው ፓርቲ ችግር ቢከሰት እንኳ በአደጋ ጊዜ ለዜጎች የሚበቃ እርዳታ አቀርባለሁ ሲል የነበረ ቢሆንም ለወገኖቻችን ግን የሚደርስላቸው አልተገኘም፡፡ ይባስ ብሎም ለዜጎች ዓለም አቀፍ ተቋማት እንዳይደርሱላቸው የተፈጠረው ረሃብ የራሱ የፖሊሲ ውድቀት መሆኑን የሚያውቀው ስርዓቱ የዜጎቻችን ስቃይና መከራ ሲሸፋፍን ከርሟል፡፡ ከአቅሙ በላይ ሲሆን ችግሩ እንደተከሰተ ቢገልፅም ለዜጎች ተገቢውን እርዳታ በሚያስገኝ መልኩ እርምጃ እየወሰደ አይደለም፡፡ በአሁኑ ወቅት በኦሮሚያ፣ በአፋር፣ በደቡብ፣ ትግራይ፣ በአማራ፣ በሶማሊና በሌሎቹም ክልሎች በተከሰተው ረሃብ ዜጎች ከፍተኛ ችግር ላይ ናቸው፡፡ ለተከሰተው የረሃብ አደጋ ተገቢው ትኩረት መነፈጉ ገዥው ፓርቲ እመራዋለሁ ለሚለው ህዝብ ደንታ ቢስነቱን የሚያረጋግጥ ነው፡፡ ረሃቡ፣ ርዛቱ፣ ድህነቱ፣ ስደቱ፣ ስራ አጥነቱ፣ የኑሮ ውድነቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ ዜጎችን በብርቱ እየተፈታተኑ በሚገኝበት ወቅት ገዥው ፓርቲና በስሩ ያሉ ድርጅቶች ተመሰረትንበት የሚሉትን ጊዜ ለወራት በቅንጦት በማክበት በብዙ ሚሊዮን ገንዘብ ከኢትዮጵያውያን ጉሮሮ ነጥቆ ድግስ ሲደግስና አሸሸ ገዳሜ ሲል በርካታ ኢትዮጵያውያንን አሳዝኗል፡፡

ለተከሰተው ረሃብ ኢህአዴግ ለይስሙላ ቆሜለታለሁ የሚለውን አርሶ አደርና አርብቶ አደርን ህይወት ለማሻሻል የረባ ስራ እንዳልሰራ ያረጋገጠ ነው፡፡ ግብርናው ኢኮኖሚውን ይመራል ቢልም እስካሁን ግን በየአመቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን የረሃብ ሰለባ እንደሆነ ቀጥለዋል፡፡ መሬት የመንግስት ነው በሚል ሽፋን አርሶ አደሩን ከቀየው እያፈናቀለ ለስርዓቱና ደጋፊዎችና ለባዕዳን መሬትን እየሸጠ አርሶ አደሩን ለረሃብ ተጋላጭ አድርጎታል፡፡ በስርዓቱ የፖሊሲ ውድቀት የተፈጠረውን አደጋ ለመሸፋፈን በሚያደርገው ጥረትም በርካታ ኢትዮጵያውያንን የችግሩ ሰለባ እየሆኑ ነው፡፡

ቢዘገይም ፓርቲያችን ሰማያዊ ገዥው ፓርቲ ለወገኖቻችን የሲቃ ድምፅ ጆሮ ዳባ ማለቱን አቁሞ አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስድ እንጠይቃለን፡፡ በተለይ ስለ ችግሩ ለኢትዮጵያውያንና ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ስለ ረሃቡ በደንብ የሚያስረዳ ገለልተኛ አካል ተቋቁሞ ለዜጎቻችን መፍትሄ እንዲፈለግ እንጠይቃለን፡፡ ስርዓቱ ደካማና ኃላፊነት የጎደለው እንደመሆኑ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ኢትዮጵያውያንና የዓለም ማህረሰብ ከወገኖቻችን ጎን እንዲቆሙ ጥሪ እናቀርባለን፡፡ በዋናነት ግን ይህ የኢትዮጵያውያን መከራ የመነጨው ከገዥው ፓርቲ የተሳሳተ ፖሊሲ፣ የአፈፃፀም ብቃት ችግርና ለኢትዮጵያውያንም ባለው ግድየለሽነት መሆኑን ተገንዝበን ይህን ለችግሮቻችን ምንጭ የሆነ ስርዓት በቁጥርጠኝነት መታገል እንዳለብን ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

ድል የህዝብ ነው!

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!

መስከረም 27 ቀን /2008 ዓ.ም

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Opinions Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. tsegaye jigso says

    October 10, 2015 11:58 am at 11:58 am

    good

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule