• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የከረረው የአሜሪካና የህወሓት “ወዳጅነት ተበጥሷል”

February 18, 2018 11:51 pm by Editor 4 Comments

  • አጋራችን ብትሆኑ ኤምባሲችን ወደየሩሳሌም እንዲዛወር ድምፅ ትሰጡ ነበር – አሜሪካ ለህወሓት

ህወሓት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዳያውጅ በጌቶቹ ከተነገረው በኋላ በራሱ መንገድ መሄዱ የግንኙነት “ገመዱን እንደበጠሰው” ተነገረ። አሜሪካ ኤምባሲዋ ወደየሩሳሌም እንዳይሄድ የተቃወሙ አገራትን ዋጋ ትከፍላላችሁ ያለችውን በህወሓት ላይ ተግብራዋለች። አውሮጳውያን የጠነከረ ተቃውሟቸውን በህወሓት ላይ በዚህ ሳምንት ውስጥ እንደሚያሰሙ ይጠበቃል።

በባራክ ኦባማ አስተዳደር የዴሞክራሲና የሰብዓዊ መብቶች ረዳት ሚኒስትር የነበሩት ቶም ማሊኖውስኪ ባለፈው ዓመት ታህሳስ ወር ኢትዮጵያን ከጎበኙ በኋላ የአገሪቱን ሁኔታ የገለጹበትን አስመልክቶ ጎልጉል ይህንን መዘገቡ ይታወሳል። “ለለውጥ የተገባውን ቃል ተግባራዊ ማድረግ የኢትዮጵያ መንግሥት ብቸኛ ሃላፊነት ነው፤ … በኢትዮጵያ እንዲመጣ የሚፈለገው ለውጥ ሥርዓቱን ለዝነተ ዓለም ለማፅናት በሚደረግ ትግል ወይንም ሥርዓቱን በኃይል ለማፍረስ በሚወሰድ እርምጃም ሊሆን አይገባም፤ ሁኔታዎች በዚህ ከቀጠሉ ሥልጣን ማስረከብ ደረጃ ሊደረስ ይችላል” ካሉ በኋላ ሲቀጥሉም “እንደ ወዳጅ መክረናል … ምክንያቱም … ኢትዮጵያ ውስጥ አንድ ነገር ቢፈጠር ሙሉ ምስራቅ አፍሪቃ ምን ሊከተል እንደሚችል ስለምናውቅ … ነው” ብለው ነበር። “አገሪቱ አሁን ያለችበት ሂደት በእሳት ላይ ተጥዶ እንደሚንተከተክ ማሰሮ ይመስላል። እናም እንዲህ የሚንተከተክ ማሰሮ ለማስተንፈስ ያለው ምርጫ ክዳኑን ማንሳት ብቻ ነው፤ ያ ካልተደረገ መንተከተኩ አያቆምም። በዚያ ከቀጠለ ደግሞ መገንፈሉ አይቀርም። ከዚያ በኋላ የሚሆነው ሁላችንም እናውቀዋለን” ብለው ነበር።

ህወሓት/ኢህአዴግ “በአሻባሪነት” ስም በሶማሊያ የሚያደርገው ማስፈራሪያ ጊዜው ያለፈበት ይመስላል። የህወሃትና የአልሸባብ ግንኙነት እንዳለ ሆኖ አሸባሪነትን ለመዋጋት በሚል አርባ ምንጭ የሰው-አልባ አሮፕላን ማረፊያ (ድሮን ቤዝ) ማቋቋም ደርሳ የነበረችው አሜሪካ ከህወሓት ጋር ያላትን ፕሮጀክት ያጠናቀቀች ይመስላል። “ሶማሊያ ውስጥ … በኮንዶም አንዋጋም!” እያለ የሚያምታታ መለስ የሌለው ህወሃት/ኢህአዴግ ቁንጮውን ብቻ ሳይሆን ከበረሃ ጀምሮ ሲያግዙት የነበሩትን “ነጭ ወያኔዎችም” እያጣ ነው። ይህም ከሌሎች የአሜሪካ ማስጠንቀቂያዎችና ምክሮች ጋር ተዳምሮ የግንኙነት ገመዱ እንዲበጠስ ያደረጉ ምክንያቶች ናቸው።

ከዚህ በፊት በነበሩት ዓመታት ሁሉ ግምገማ በማካሄድ ራሱን ሲያብጠለጥል የኖረው ህወሓት/ኢህአዴግ እንደከዚህ በፊቱ በቃል ደረጃ ሟቹ መለስ እንዳለው “እስከ እንጥላችን ገምተናል” ባይልም ከዚያ ባልተለየ አገላለጽ አመራሩ እንደከሸፈ በገሃድ መስክሯል። ይህንን ካለ በኋላ ግን መላው አመራር ከያዘው ሥልጣን መነሳት ሲገባው ይኸው በመለስ አጠራር “እስከ እንጥሉ የገማው” አመራር በሥልጣኑ ላይ አንዳች ለውጥ ሳያደርግ ቀጥሏል።

በተደጋጋሚ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማውጣት በአገሪቱ ውስጥ የተነሳውን የተቃውሞ ማዕበል ለማብረድ ህወሓት ሙከራ ቢያደርግም አልተሳካለትም። ከጥቂት ወራት በፊት የተነሳውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተከትሎ በአገሪቱ ውስጥ የለውጥ እንቅስቃሴ አገርሽቷል። በየአቅጣጫው ዜጎች ያነሱትን ጥያቄ በግድያና በእስር ለመመለስ የሞከረው ህወሓት ሕዝባዊ ጽናትና የHR 128 ጡንቻ ተባብረውበት “አሸባሪ” እያለ ያሰራቸውን የፖለቲካ እስረኞች ለመፍታት ተገድዷል።

በዚህ ሁሉ ውስጥ የተለያዩ ማባበያዎችንና ማስፈራሪዎችን ለመጠቀም የሞከረው ህወሓት “እኛ ከተነሳን አልሸባብ ሶማሊያን ይቆጣጠራል፤ ቀጣናው ሰላም አልባ ይሆናል፤ …” የሚሉትን ራሱን የአሜሪካ እውነተኛ አጋር አድርጎ ለማቅረብ የሄደበትም መንገድ አልሠራለትም። እንዲያውም ሌላ አቧራ አስነስቶበታል።

(በትልቁ ለመመልከት ምስሉ ላይ ይጫኑ)

የትራምፕ አስተዳደር በእስራኤል የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ከቴል አቪቭ ወደየሩሳሌም እንዲዛወር ውሳኔ ካደረገ በኋላ የተባበሩት መንግሥታት በጉዳዩ ላይ ድምፅ ሰጥቶበት ነበር። ኢየሩሳሌም ዓለምአቀፋዊ ከተማ ከመሆኗ አንጻር ኤምባሲው ወደዚያ እንዳይዛወር የመንግሥታቱ ድርጅት ያቀረበውን ሃሳብ ኢትዮጵያን ጨምሮ 128 አገራት ሲደግፉ አሜሪካንን ጨምሮ 9 አገራት ብቻ ተቃውመውታል። ከአፍሪካ ደቡብ ሱዳን፣ ዑጋንዳ፣ ሩዋንዳ እና ሌሎች አገራት ድምጸ ተዓቅቦ ማድረጋቸው ይታወሳል። ከአሜሪካ ዕርዳታና ድጎማ እያገኙ አሜሪካንን መደገፍ ሲገባቸው የመንግሥታቱን ድርጅት በመደገፍ አሜሪካንን የተቃወሙትን 128 አገራት አስመልክቶ “ዋጋ እንደሚከፍሉ” በወቅቱ ከትራምፕ አስተዳደር ተነግሮ ነበር።

በምዕራባውያን የበጀት ድጎማና ዕርዳታ ኅልውናው የታሠረው ህወሓት ጌቶቹ የሚያዙትን በተግባር መፈጸም ግዴታው ከሆነ ሰነባብቷል። በአሜሪካ በኩል ያለውን የጠነከረ አቋም ለማለሳለስ፤ “እኛ ብቸኛ የአሜሪካ ጥቅም አስከባሪና አጋር ነን” በማለት በሹሞቹ በኩል ለማሳመን ሙከራ ቢያደርግም አልተሳካለትም። “አጋራችን ብትሆኑ ኖሮ ኤምባሲያችን ወደየሩሳሌም እንዲዛወር ያቀረብነውን ሃሳብ በተበባበሩት መንግሥታት ፊት ትደግፉ ነበር” በማለት “ተገቢ” ምላሽ እንደተሰጣቸው ጎልጉል ያገኘው መረጃ ይጠቁማል።

በመሆኑንም ሌላ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጅ ተቀባይነት እንደማይኖረው የተነገረው ህወሓት ከምዕራባውያን የተሰጠውን ትዕዛዝ ሳይቀበል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጇል። ይህ እንደተሰማ በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ከዚህ በፊት ከሚያወጣው መግለጫ ለየት ባለ መልኩ የህወሓትን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ “አጥብቆ” ተቃውሞታል። ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ይልቅ ሊሰጥ የሚገባው “ምላሽ ነጻነትን በማሳነስ ሳይሆን በማብዛት” መሆን እንዳለበት ኤምባሲው እንደሚያምን በመግለጫው ጠቁሟል። ይህ የኤምባሲው አቋም የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ (ስቴት ዲፓርትመንት) ውሳኔ ተደርጎ የሚታይ ሲሆን እስካሁን ከወጡት መግለጫዎች በዓይነቱም በይዘቱና በቃላት አጠቃቀሙ ጠንከር ያለ ሆኗል።

ይህንን የአሜሪካ አቋም ተከትሎ በዚህ በያዝነው ሳምንት ውስጥ የአውሮጳ ኅብረት፣ እንደ ጀርመን ያሉ አገራት በተናጠል እንዲሁም ካናዳ ተመሳሳይ ተቃውሞ እንደሚያሰሙ ጎልጉል ያገኘው መረጃ ይጠቁማል።

የጌቶቹ የተጠናከረ ተቃውሞ ያሳሰበው ህወሓት ያስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በተመለከተ አጣብቂኝ ውስጥ ገብቷል። ተቃውሞውን ሰምቶ ያወጣውን አዋጅ ከሰረዘ ተሸናፊነቱን የሚያሳይ ይሆናል። አሻፈረን ብሎ ከገፋበትም ከድርጎ ሰፋሪዎቹ ጋር ሊቆራረጥ ነው። ስለዚህ “መንግሥት ይህንን (የአስቸኳይ ጊዜ) ውሳኔ በሚቀጥሉት 15ቀናት ለብሔራዊ ፓርላማ በማቅረብ ያስጽድቃል” በማለት በዕንጥልጥል ሊተወው ይችላል የሚል ግምት ይሰጣል።

መለስ በG-20 ስብሰባ

ከመለስ ሞት በኋላ በህወሓትና በአሜሪካ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚከታተሉ እንደሚሉት፤ አሜሪካ በተደጋጋሚ በገሃድም ይሁን በምስጢር ህወሓትን ስትመክር ቆይታለች። ከዚህ በኋላም እንዲሁ በምክርና በመግለጫ ብቻ መቀጠሏ የማይታይ ከመሆኑ የተነሳ ነው “የህወሓት እና የአሜሪካ የግንኙነት ገመድ ተበጥሷል” በማለት የመረጃው ባለቤቶች ለጎልጉል ለመናገር የደፈሩት። ይህ ይበል የሚያሰኝ በመሆኑ በአገር ውስጥ ያለው የለውጥ ኃይል በአስቸኳይ ከውጪው ጋር በቅንጅት በመሥራት የጌቶቹ ድጋፍ እየተነፈገ ያለውን ህወሓት/ኢህአዴግን እንዳይመለስ አድርጎ መሸኘት ያስፈልጋል በማለት ተናግረዋል።  (ፎቶ: በአዲስ አበባ የአሜሪካ ኤምባሲ)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Ezira says

    February 20, 2018 12:12 am at 12:12 am

    it is very Good News!
    God Bless Ethiopia

    Reply
  2. Benkamin says

    February 20, 2018 12:17 am at 12:17 am

    TPLF is the dictator regime! We Ethiopian against this terrible regime and fight until we get our freedom! One Ethiopia forever!??❤

    Reply
  3. Benjamin says

    February 20, 2018 12:20 am at 12:20 am

    Am against the tplf regime!

    Reply
  4. Mulugeta Andargie says

    February 20, 2018 01:28 am at 1:28 am

    ሰዎች!! የጎልጉል ዜና ኣቅራቢዎችም ሆኑ፣ ጎልጉልና የዝግጅቱ ክፍል፤ ወሬው የወተላገደ ከመሆኑም በላይ፤ የተዘበራረቀ ሆኖ ኣግኝቸዋለሁ። እስቲ ረጋ ብላችሁ ከላይ ጀምራችሁ እየጨመቃችሁ ዝለቁት፣ ትንቢት ለመናገርም ይቃጣውና፣መልሶ ከጀልባ ላይ የወደቀ ዋነተኛ ሆኖ ሲንቦጫረቅ ያስቀናል። በሃገሪቱ የሌለ ወይም ያልተደረገ ዝብርቅርቅ ቅጥ ኣንባሩ ጥፍት ያለ ወሬ ሆኖ ታገኙታላችሁ። ወሬ የት ትሄዳለህ ብሎ እንዱ ጠየቀው ኣሉ ወሬን፣ ወሬም፣ ጎልጉል ቤት፣ እስቲ ኣረፍ በልና እህልም ቀማሰህ ይሉታል፣ወሬም፣ጎልጉል ቤት ሳልደርስ፣ኣፈር ድሜ ልቅመስ ብሎ ነጎደ ይባላል።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule