• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የፀጥታና ደህንነት ተቋማት በዓላት ያለ ችግር እንዲከበሩ በዘመናዊ መልኩ ተዘጋጅተዋል

September 25, 2020 01:19 am by Editor Leave a Comment

መጪዎቹን የመስቀልና የኢሬቻ በዓላት ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲከበሩ ለማድረግ የፀጥታና የደህንነት ተቋማት አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅቶች ማድረጋቸው ተገለፀ።

ይህን የገለጸው ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ለፀጥታና ደህንነት አካላት በዘመናዊ መሳሪያ የታገዘ ተግባራዊ የፀረ-ሽብር ሥልጠና ሰጥቷል።

ሥልጠናው ከመከላከያ ሠራዊት፣ ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት፣ ከፌዴራልና ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽኖች፣ ከሪፐብሊካን ጋርድና ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ልዩ ኃይል ለተውጣጡ ከ330 በላይ አመራሮችና አባላት ነው የተሰጠው።

የንድፈ ሃሳብና የተግባር ሥልጠናው ሽብርተኝነትን መከላከልና ማክሸፍ፤ የሽብር ተልዕኮዎችንም አስቀድሞ ማወቅ የሚቻልበትን የመረጃ ሥራ ያካተተ ነው።

በዚሁ መሰረት ሰልጣኞቹ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊ /ቪ.አይ.ፒ/ እገታን በተቀናጀና ዘመናዊ መሳሪያ በመጠቀም ማስለቀቅ የሚያስችል ኦፕሬሽን በተግባር ስልጠናው አካሂደዋል።

ኦፕሬሽኑ ዘመናዊ የጦር መሳሪያ፣ ፈንጂ አምካኝ ሮቦትና ሌሎች የጸረ ሽብር ተግባራትን በማሟላት የተካሄደ ነው።

ሠልጣኞቹ ተለዋዋጩ የዓለም ሽብርተኝነት በሚያስከትለው ጉዳት የሕዝብ ሠላምና ደህንነት እንዳይደፈርስ ለመጠበቅ የሚያስችል አቅም ከስልጠናው ማግኘታቸውን ገልጸዋል።

የሽብር ጥቃቶች በኢትዮጵያ ቢቃጡ ቴክኖሎጂ በመጠቀም አስቀድሞ ለመከላከልና ለማክሸፍ ስልጠና አቅም እንደሆናቸውም አክለዋል።

ረዳት ኢንስፔክተር ተስፋዬ ብርሃኑ እና ኮማንደር ሰለሞን ፋንታሁን እንዳሉት በተግባር ልምምዱ በሽብርተኞች የሚጠመዱ ፈንጂዎችን ዘመናዊ ሮቦት በመጠቀም ማክሸፍ እንደሚቻል አሳይተዋል።

የፈንጂ አምካኝ ምህንድስና ባለሙያው መስፍን እንዳለ መሳሪያው ከሰው ሃይል አቅም በላይ የሆኑ የተጠመዱ ፈንጂዎችን በጥንቃቄ ማክሸፍ እንደሚችል ገልጸዋል።

ሥልጠናው ማንኛውንም አይነት የሽብር ወንጀል በቅንጅት ለመከላከልና ለማክሸፍ እንደሚያስችላቸው የተናገሩት ደግሞ የልዩ ኮማንዶ አስተባባሪ አቶ ለማ ባቱ ናቸው።

በምስራቅ አፍሪካ አካባቢ የሚንቀሳቀሱ የሽብር ቡድኖች በኢትዮጵያና በሕዝቦቿ ላይ የሚቃጡትን ጉዳት ለመከላከልም ያግዛል ብለዋል።

ሥልጠናው አል ቃይዳ፣ አይ.ኤስ እና አልሸባብ የሽብር ቡድኖች የኢትዮጵያና የአካባቢውን አገራት የሠላም፣ የትብብርና የልማት ማዕቀፍ ለማደናቀፍ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ ለመግታትና ለማክሸፍ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

ሽብርተኝነት የደቀነውን ስጋት ለመመከት ስልጠናው በአገሪቷ የተለያዩ የክልል ከተሞችም ቀጣይነት እንዳለው የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ለኢዜአ ገልጿል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule