• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የፀጥታና ደህንነት ተቋማት በዓላት ያለ ችግር እንዲከበሩ በዘመናዊ መልኩ ተዘጋጅተዋል

September 25, 2020 01:19 am by Editor Leave a Comment

መጪዎቹን የመስቀልና የኢሬቻ በዓላት ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲከበሩ ለማድረግ የፀጥታና የደህንነት ተቋማት አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅቶች ማድረጋቸው ተገለፀ።

ይህን የገለጸው ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ለፀጥታና ደህንነት አካላት በዘመናዊ መሳሪያ የታገዘ ተግባራዊ የፀረ-ሽብር ሥልጠና ሰጥቷል።

ሥልጠናው ከመከላከያ ሠራዊት፣ ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት፣ ከፌዴራልና ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽኖች፣ ከሪፐብሊካን ጋርድና ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ልዩ ኃይል ለተውጣጡ ከ330 በላይ አመራሮችና አባላት ነው የተሰጠው።

የንድፈ ሃሳብና የተግባር ሥልጠናው ሽብርተኝነትን መከላከልና ማክሸፍ፤ የሽብር ተልዕኮዎችንም አስቀድሞ ማወቅ የሚቻልበትን የመረጃ ሥራ ያካተተ ነው።

በዚሁ መሰረት ሰልጣኞቹ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊ /ቪ.አይ.ፒ/ እገታን በተቀናጀና ዘመናዊ መሳሪያ በመጠቀም ማስለቀቅ የሚያስችል ኦፕሬሽን በተግባር ስልጠናው አካሂደዋል።

ኦፕሬሽኑ ዘመናዊ የጦር መሳሪያ፣ ፈንጂ አምካኝ ሮቦትና ሌሎች የጸረ ሽብር ተግባራትን በማሟላት የተካሄደ ነው።

ሠልጣኞቹ ተለዋዋጩ የዓለም ሽብርተኝነት በሚያስከትለው ጉዳት የሕዝብ ሠላምና ደህንነት እንዳይደፈርስ ለመጠበቅ የሚያስችል አቅም ከስልጠናው ማግኘታቸውን ገልጸዋል።

የሽብር ጥቃቶች በኢትዮጵያ ቢቃጡ ቴክኖሎጂ በመጠቀም አስቀድሞ ለመከላከልና ለማክሸፍ ስልጠና አቅም እንደሆናቸውም አክለዋል።

ረዳት ኢንስፔክተር ተስፋዬ ብርሃኑ እና ኮማንደር ሰለሞን ፋንታሁን እንዳሉት በተግባር ልምምዱ በሽብርተኞች የሚጠመዱ ፈንጂዎችን ዘመናዊ ሮቦት በመጠቀም ማክሸፍ እንደሚቻል አሳይተዋል።

የፈንጂ አምካኝ ምህንድስና ባለሙያው መስፍን እንዳለ መሳሪያው ከሰው ሃይል አቅም በላይ የሆኑ የተጠመዱ ፈንጂዎችን በጥንቃቄ ማክሸፍ እንደሚችል ገልጸዋል።

ሥልጠናው ማንኛውንም አይነት የሽብር ወንጀል በቅንጅት ለመከላከልና ለማክሸፍ እንደሚያስችላቸው የተናገሩት ደግሞ የልዩ ኮማንዶ አስተባባሪ አቶ ለማ ባቱ ናቸው።

በምስራቅ አፍሪካ አካባቢ የሚንቀሳቀሱ የሽብር ቡድኖች በኢትዮጵያና በሕዝቦቿ ላይ የሚቃጡትን ጉዳት ለመከላከልም ያግዛል ብለዋል።

ሥልጠናው አል ቃይዳ፣ አይ.ኤስ እና አልሸባብ የሽብር ቡድኖች የኢትዮጵያና የአካባቢውን አገራት የሠላም፣ የትብብርና የልማት ማዕቀፍ ለማደናቀፍ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ ለመግታትና ለማክሸፍ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

ሽብርተኝነት የደቀነውን ስጋት ለመመከት ስልጠናው በአገሪቷ የተለያዩ የክልል ከተሞችም ቀጣይነት እንዳለው የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ለኢዜአ ገልጿል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule