• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም

September 8, 2023 02:31 pm by Editor 3 Comments

የኢትዮጵያ ክብርና ነፃነት በቆራጥ ልጆቿ መሥዋዕትነት የተገኘ መሆኑ የማያጠያይቅ ነው፡፡ ለሀገራችን ሠላም፣ ለሠንደቅ ዓላማችን ክብር ሲሉ መሥዋዕትነት ከከፈሉ ጀግና ኢትዮጵያውያን መካከል ደግሞ ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ሃብተማርያም አንዱ ናቸው፡፡ ዛሬ ጳጉሜ 2 ለኢትዮጵያ ሀገራቸው መሥዋዕትነት የከፈሉ ጀግኖች የሚታሰቡበት እና የሚዘከሩበት ቀን እንደመሆኑ በዛሬው የአውደ ሰብ አምዳችን ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ሃብተማርያምን ባለታሪካችን አድርገናቸዋል፡፡

ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ሀብተማርያም ተወልደው ያደጉት በጉራጌ ዞን ከቸሀ ወረዳ 20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ሲሰ መንደር ውስጥ ነው፡፡ እስከ 8ኛ ክፍል ያለውን ትምህርታቸውን እዚያው እምድብር ከተማ የተማሩ ሲሆን፣ በ1948 ዓመተ ምህረት የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ተፈትነው በጥሩ ውጤት አጠናቀዋል፡፡

የ8ኛ ክፍል ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቁም የአምቦ እርሻ ልማት ትምህርት ገብተው ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፤ በኋላም ወደ ጦር አካዳሚ በመግባት የ3 ዓመት ወታደራዊ ሳይንስና የአካዳሚ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁት በስመጥሩው የምርጥ መኮንኖች ማፍሪያ በሆነው ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ (ሀረር) ጦር አካዳሚ ነው። 

ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ በመቀጠልም የጦር ሠራዊቱን በመቀላቀል የአየር ወለድ ሥልጠና የወሰዱ ሲሆን፤ ሙያቸውን ለማጠናከርም በእስራኤል የኮማንዶ ትምህርት፣ አሜሪካ የልዩ ኃይል፣ ሞስኮ እና ህንድን ጨምሮ በተለያዩ የውትድርና ሥልጠናዎችን ራሳቸውን አብቅተዋል፡፡  

በ1969 ዓ.ም የሶማሊያ ተስፋፊ ሃይል ኢትዮጵያን ወሮ ከጅግጅጋ እና ጎዴ አልፎ መጥቶ እስከ ሜኢሶ ድረስ በመቅረብ መሬቱን በፈንጅ አጥሮ ነበር፡፡ ይህ መሰናከል ለሠራዊቱ እና ለህዝቡ መሰረታዊ የሆኑ ነገሮች ለማቅረብ በጣም ችግር ፈጠረ፡፡ ይህን ችግር ለመፍታትም የሶማሊያ ግዛት ክልል ውስጥ ዘልቆ መግባት እና ፈንጅ መቅበር አንድ መንገድ የነበረ ሲሆን፣ ይህ ግዳጅም ለብ/ጀነራል ተስፋዬ ተሰጠ፡፡ እሳቸው የሚመሩት ቡድንም ድንበር አቋርጦ ሶስት ቀን እና ሌሊት ፈንጂ በመቅበር የጠላትን እንቅስቃሴ አወከ፤ ትልቅ ውጤትም ማምጣት ተቻለ፡፡

በ1970ዎቹ መግቢያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በጠለፋ ምክንያት በጣም በከፍተኛ ሁኔታ ችግር ውስጥ ገብቶ የነበረ ሲሆን፣ በዚህም አንዳንድ ቦታዎች ላይ በረራ በመቆሙ ድርጅቱ ለሠራተኞቹ እንኳን ደሞዝ መክፈል ያልተቻለበት ሁኔታ ላይ ደርሶ ነበር፡፡ ችግሩን ለመፍታትም የበረራ ደህንነት እንዲቋቋም መንግሥት ሲወስን የድህንነት ቡድን እንዲያቋቁም ለብ/ጀነራል ተስፋዬ ኃላፊነት ተሰጣቸው፤ እሳቸውም የሰለጠኑ የደህንነት አባላት ከአውሮፕላኖቹ ጋር እንዲጓዙ በማድረግ ችግሮቹን መፍታት ችለዋል፡፡

በሰላም ለመኖር መሰረቱ ሥነ- ሥርዓት ነው የሚሉት ብርጋዴን ጄኔራል ተስፋዬ ሀ/ማርያም “በኢትዮጵያ ምድር ውስጥ ጥይት በሚፈነዳበት ቦታ ሁሉ እኔ ያልተሳተፍኩበት በጣም ጥቂት ሲሆን፣ አብዛኛው በተሳተፍኩባቸው ቦታዎች በድል ወይም በስኬት ነው የተጠናቀቁት” በማለት ስለ ህይወት ተሞክሮአቸው ይገልጻሉ፡፡

በ1970ዎቹ እርሳቸው የሚመሩት የአየር ወለድ ጦር ናቅፋ ተራራ ላይ ለ6 ወራት በጠላት ተከቦ በህይወት ቆይቶ የጠላትን ከበባ ሰብሮ በህይወት እንደወጣ ሲነገሩ፣ ይህ ታሪካዊ ክስተት በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የተፈጠረ የአየር ወለድ ሠራዊት ጀብድ እንደሆነ ይገልጻሉ፡፡   

ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ሃ/ማርያም በሶማሊያ ጦርነት ወቅት ለሠሩት ገድል እና በናቅፋ በሰሩት ጀብድና የአመራር ብቃት ከሻለቃነት ወደ ኮሎኔልነት በአንዴ ማደግ የቻሉ ወይም በ5 ዓመት የሚደረስበትን ወታደራዊ ማዕረግ በፈጥነት ማግኘት የቻሉ ጀግና ናቸው፡፡ ጀነራሉ በኢትዮጵያ ታሪክ ለማንም ወታደር እና መኮንን ተሸልሞ የማያውቀውን “ወደር የሌለውን የሕብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና ወታደራዊ ሜዳሊያም” ተሸልመዋል፡፡

ማንም ሰው ብቁ አሰልጣኝ ካገኝ አየር ወለድ መሆን እንደሚችል የሚገልጹት ብ/ጀነራል ተስፋዬ፣ እሳቸው ከሀረር ጦር አካዳሚ በመሰረታዊ ውትድርና ከሰለጠኑ በኋላ የአየር ወለድ ሥልጠና ያገኙት ከእስራኤሎች እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ 

“ኢትዮጵያ በየዘመኑ ጀግና የምታፈራ የጀግኖች ሀገር ናት” የሚሉት ብ/ጀነራል ተስፋዬ ሀብተማርያም ለዚህም መላው የሀገሪቱ ህዝብ ትልቅ ኩራት ሊሰማውና ተስፋ ሊሰንቅ እንደሚገባም ይናገራሉ።

“የሀገሪቱን ዕድገት ጎታች ሆኖ ፈተና ውስጥ የከተተን ነገር የእናት ጡት ነካሽ በሆኑ ከሀዲዎች በየጊዜው የሚከፈትብን ጦርነት ነው፤ ይህንን የህልውናችንን ጠላት ለመዋጋት ደግሞ ወጣቱ ከጦር ሜዳው ተሳትፎ ባልተናነሰ መልኩ መነሳትና አንድነት መፍጠር ይኖርበታል” ይላሉ። (ኢዜአ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature, Middle Column, Social Tagged With: Tesfaye Habtemariam

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    September 14, 2023 11:13 am at 11:13 am

    ኢትዮጵያ አሉኝ ብላ ከምትጠራቸው ከሞትና ከስደት ከተረፉት ልጆቿ መካከል ብ/ጄ ተስፋዬ ሃብተማሪያም ቀዳሚው ነው። የጦር ሜዳ ውሎ በተሰኘው መጽሃፉ ላይ እንደሚተርክልን “ላብ ደምን ያድናል” በማለት ለሃገሩ በአራቱ ማእዘናት የተፋለመ ሥራው በጠላትም ጭምር የተመሰከረለት ጀግና ነው።
    ሌላ ምን እላለሁ እንኳን ከዚያ ሁሉ የመጠላለፍና የሞት ፍልሚያ ወጥተህ እድሜ ጠግበህ ያኔ የሆነውና አሁን የሚሆነውን ሁሉ አይተህ አይ ጊዜ እንድትል ፈጣሪ እድሜውን ስለቸረህ በጣም ደስ ይለኛል። ያንተ ጀግንነት ለትውልድ በታሪክ ለማስተላለፍ ሰፋ ባለ መልኩ ፊልም/ድራማ ቢሰራ መልካም ይመስለኛል። መጽሃፍ ብቻውን በቂ አይሆንማና! ረጅም እድሜና ጤና ለኢትዮጵያ ባለውለታ ብ/ጄ ተስፋዬ ሃበተማሪያም ይሁን!

    Reply
  2. noah h.meskel says

    September 22, 2023 02:12 am at 2:12 am

    እኔም የአቶ ተሰፋን አሰተያየት እደግፋለሁ የእርሳቸውን (የብርጋዴር ጄነራልን) የጦር ገድል በፊልም ቢሰራ ለአዲሱ ትውልድ የሀገር ፍቅር ምን እንደሆነ ያሰተምራል::

    Reply
  3. Zeru metaferia says

    May 6, 2025 01:14 pm at 1:14 pm

    ጄኔራል ተስፋዬ 1992 ብላቴ እኔ ሰልጠኘሰ እሳቸው የማሰልጠኛው ኮማንደር ሆነው አውቃቸዋለሁ ኢትዮጵያ አሉኝ ብላ ከምትጠራቸው ከሞትና ከስደት ከተረፉት ልጆቿ መካከል ብ/ጄ ተስፋዬ ሃብተማሪያም ቀዳሚው ነው። የጦር ሜዳ ውሎ በተሰኘው መጽሃፉ ላይ እንደሚተርክልን “ላብ ደምን ያድናል” በማለት ለሃገሩ በአራቱ ማእዘናት የተፋለመ ሥራው በጠላትም ጭምር የተመሰከረለት ጀግና ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule