• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የስኳር ፋብሪካዎች ተሽጠው ዕዳቸውን እንዲከፍሉ ተወሰነ

April 14, 2021 08:53 am by Editor Leave a Comment

በመንግሥት ባለቤትነት ሥር ከሚገኙት 13 ስኳር ፋብሪካዎች ውስጥ አሥሩ ለግል ባለሀብቶች ተሸጠው፣ ከሽያጩ የሚገኘው ገቢ በከፍተኛ የዕዳ አጣብቂኝ ውስጥ ናቸው ተብለው ለተለዩ ሰባት የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ዕዳ ክፍያ ጥቅም ላይ እንዲውል ተወሰነ።

ሪፖርተር ያገኘው መንግሥታዊ መረጃ እንደሚያመለክተው ሰባቱ የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ካለባቸው አጠቃላይ ዕዳ ውስጥ፣ አመዛኙ እንደ አዲስ ወደ የሚቋቋመው ኮርፖሬሽን እንዲዘዋወር ተወስኗል። 

አዲስ የሚቋቋመው ተቋም “የዕዳና ሀብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን” የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን፣ ኮርፖሬሽኑን ለማቋቋምም የሚያስችል ደንብ ከጥቂት ሳምንታት በፊት በሚኒስትሮች ምክር ቤት መፅደቁ ይታወቃል። 

ኮርፖሬሽኑ ከፍተኛ የዕዳ ጫና ውስጥ ወድቀዋል ተብለው ከተለዩት ሰባት የመንግሥት ልማት ድርጅቶች አጠቃላይ ዕዳ ውስጥ፣ ኮርፖሬሽኑ አመዛኙን በመውረስ ዕዳቸውን የመክፈል፣ እንዲሁም ድርጅቶቹን ከዕዳ አስተዳደር ወጥተው ትርጉም ያለው ኢኮኖሚያዊ ተልዕኮ እንዲወጡ የማስቻል አስተዳደራዊ ሚናም ተጥሎበታል። 

በመንግሥት የተለዩት ሰባቱ የመንግሥት ልማት ድርጅቶች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን፣ ኢትዮ ኢንጅነሪግ ግሩፕ (የቀድሞው ሜቴክ)፣ ኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን፣ የኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽንና ስኳር ኮርፖሬሽን ናቸው።

እነዚህ ድርጅቶች ከአገር ውስጥ አበዳሪዎች በዋናነት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክና ከውጭ አበዳሪዎች ተበድረው ያልመለሱት አጠቃላይ ዕዳ 780 ቢሊዮን ብር ወይም 19.5 ቢሊዮን ዶላር እንደሆነ፣ ገንዘብ ሚኒስቴር ሰሞኑን ይፋ ያደረገው መረጃ ያመለክታል።

አዲስ የሚቋቋመው ኮርፖሬሽን ሰባቱ ድርጅቶች ካለባቸው 780 ቢሊዮን ዶላር ውስጥ 570 ቢሊዮን ብሩን ወርሶ የመክፈልና የማስተዳደር ኃላፊነት ተጥሎበታል።

ኮርፖሬሾኑ የሚቋቋመው ራሱን በቻለ የንግድ ተቋም አደረጃጀት እንደሚሆን፣ ኃላፊነቱን ለመረከብ የሚያስፈልገው የመጀመርያ ካፒታልም ከመንግሥት በጀት ውጪ እንደሚሆን መረጃው ያመለክታል። 

በመሆኑም አሥር የመንግሥት ስኳር ፋብሪካዎችን በመሸጥ የሚገኘው ገቢ ኮርፖሬሽኑ ለሚያስፈልገው የመጀመርያ ካፒታል ፈሰስ እንዲደረግ የተወሰነ ሲሆን፣ ከስኳር ፋብሪካዎቹ ሽያጭ ከሚገኘው ገቢ በተጨማሪ በቅርቡ ለውጭ ኩባንያዎች ከሚሰጠው የቴሌኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ፈቃድ ክፍያ፣ እንዲሁም ከኢትዮ ቴሌኮም ከፊል ሽያጭ የሚገኘው ገቢ ትልቅ ድርሻ ወደ ኮርፖሬሽኑ ፈሰስ እንዲደረግ መወሰኑ ታውቋል።

መንግሥት በመጀመርያ ይዞት የነበረው ዕቅድ 13 ስኳር ፋብሪካዎችን ለመሸጥ የነበረ ሲሆን፣ ይህንንም ወደ ተግባር ለመቀየር የሁሉም ፋብሪካዎች አጠቃላይ ሀብትና ንብረት በገለልተኛ የኦዲት ኩባንያ እንዲገመት አድርጓል።

ይህንን የሀብትና ንብረት ግመታ እንዲያከናውንም ቡከር ቴት የተባለ የእንግሊዝ ኩባንያ ተቀጥሮ የግመታ ሥራውን ከዓመት በፊት አጠናቆ፣ ሪፖርቱንም ለመንግሥት እንዳቀረበ የተገኘው የሰነድ መረጃ ያመለክታል።

ኩባንያው ባካሄደው የግመታ ሥራ የ13 ስኳር ፋብሪካዎችን አጠቃላይ ሀብትና ንብረት ከዓመት በፊት በነበረ ዋጋ መሠረት 88 ቢሊዮን ብር ገምቷል። 

ይሁን አንጂ በተመሳሳይ ወቅት የነበረው የስኳር ፋብሪካዎቹ አጠቃላይ የአገር ውስጥ ዕዳ ወለድን ሳይጨምር ብቻውን 81.6 ቢሊዮን ብር የነበረ ሲሆን፣ በዚህ ተመሳሳይ ወቅት የፋብሪካዎቹ አጠቃላይ የውጭ ዕዳ መጠን ወለድን ሳይጨምር 2.1 ቢሊዮን ዶላር ነበር። 

በመሆኑም የ13 ስኳር ፋብሪካዎች አጠቃላይ የአገር ውስጥና የውጭ ዕዳ ወለድን ሳይጨምር፣ በአሁኑ ወቅት ባለው የውጭ ምንዛሪ ተመን ሥሌት 165.6 ቢሊዮን ብር ይሆናል። ይሁን እንጂ ይህ ግመታ ከተከናወነ በኋላ መንግሥት ተጨማሪ ወጪዎች በስኳር ፋብሪካዎች ላይ በማፍሰሱ የምርት ማሻሻያ ሥራዎችን፣ እንዲሁም የተመረጡ ፋብሪካዎችን የግንባታ ደረጃ የማሻሻል ጥረቶችን ያደረገ በመሆኑ፣ በቀደመው የሀብት መጠን ላይ ለውጥ እንደሚያመጣ መረዳት ይቻላል።

መንግሥት ከ13 ፋብሪካዎች ውስጥ አሥር ፋብሪካዎች እንዲሸጡና የሚገኘው ገቢም የዕዳ ክፍያን ለማስተዳደር ወደ የሚቋቋመው ኮርፖሬሽን ሙሉ በሙሉ ፈሰስ እንዲደረግ በመወሰኑ፣ አሥሩ ፋብሪካዎች በተገመቱበት የሀብት መጠን ብቻ ቢሸጡ፣ ኮርፖሬሽኑ ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ መቋቋሚያ ካፒታሉን ከስኳር ፋብሪካዎች ሽያጭ ሊያገኝ ይችላል። 

ከስኳር ፋብሪካዎቹ ሽያጭ በተጨማሪ ከቴሌኮሙዩኒኬሽን ዘርፍ ገቢ ከፍተኛ ድርሻ ለኮርፖሬሽኑ ፈሰስ የሚደረግ ሲሆን፣ የቴሌኮሙዩኒኬሽን ዘርፉን ለውጭ ገበያ ለመክፈት በተወሰነው መሠረት፣ ለሁለት የውጭ ኩባንያዎች የቴሌኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ፈቃድ ለመሰጥት የተጀመረው የጨረታ ሒደት ተጠናቆ፣ በመጪዎች ጥቂት ሳምንታት አሸናፊዎቹ ኩባንያዎች ይፋ እንደሚደረጉ ይጠበቃል።

ጨረታውን የሚያሸንፉት ሁለት ኩባንያዎች እያንዳንዳቸው ለ15 ዓመታት የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት ፈቃድ የሚያገኙ ሲሆን፣ ከሁለቱ ኩባንያዎች የፈቃድ ክፍያ በትንሹ በአማካይ መንግሥት ሁለት ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገቢ ሊያገኝ እንደሚችል የዘርፉ ባለሙያዎች ይገምታሉ። 

ለሁለት የውጭ ኩባንያዎች የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት ፈቃድ ለመስጠት በመካሄድ ላይ ካለው የጨረታ ሒደት ጎን ለጎን፣ መንግሥት በኢትዮ ቴሌኮም ላይ ያለውን 45 በመቶ ድርሻ ለመሸጥ ዝግጅት እያደረገ መሆኑ ይታወቃል። 

የኢትዮ ቴሌኮም ከፊል ሽያጭን አስመልክቶ እስካሁን ከተደረጉት ዝግጅቶች መካከል የተቋሙ አጠቃላይ ሀብትና ንብረት ግመታ፣ በውጭ የኦዲት ኩባንያ ተሠልቶ መጠናቀቁና ለመንግሥት መቅረቡ ይገኝበታል። 

የኢትዮ ቴሌኮም ከፊል ሽያጭ እስኪጠናቀቅ ድረስ የተካሄደው የሀብትና ንብረት ግመታ ውጤት በሚስጥር መጠበቅ ያለበት በመሆኑ ይፋ አልተደረገም፡፡ ነገር ግን የኢትዮ ቴሌኮም ሀብት በመንግሥት ከተገመተው 42 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱ ተገልጿል።

ይህንንም ተከትሎ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ከጥቂት ወራት በፊት የኢትዮ ቴሌኮምን የተከፈለ ማቋቋሚያ ካፒታል ከ40 ቢሊዮን ብር ወደ 400 ቢሊዮን ብር ማሳደጉ ይታወሳል። (ሪፖርተር)

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: abay tsehaye, sugar factory, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule