• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የስኳር ፋብሪካዎች ተሽጠው ዕዳቸውን እንዲከፍሉ ተወሰነ

April 14, 2021 08:53 am by Editor Leave a Comment

በመንግሥት ባለቤትነት ሥር ከሚገኙት 13 ስኳር ፋብሪካዎች ውስጥ አሥሩ ለግል ባለሀብቶች ተሸጠው፣ ከሽያጩ የሚገኘው ገቢ በከፍተኛ የዕዳ አጣብቂኝ ውስጥ ናቸው ተብለው ለተለዩ ሰባት የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ዕዳ ክፍያ ጥቅም ላይ እንዲውል ተወሰነ።

ሪፖርተር ያገኘው መንግሥታዊ መረጃ እንደሚያመለክተው ሰባቱ የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ካለባቸው አጠቃላይ ዕዳ ውስጥ፣ አመዛኙ እንደ አዲስ ወደ የሚቋቋመው ኮርፖሬሽን እንዲዘዋወር ተወስኗል። 

አዲስ የሚቋቋመው ተቋም “የዕዳና ሀብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን” የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን፣ ኮርፖሬሽኑን ለማቋቋምም የሚያስችል ደንብ ከጥቂት ሳምንታት በፊት በሚኒስትሮች ምክር ቤት መፅደቁ ይታወቃል። 

ኮርፖሬሽኑ ከፍተኛ የዕዳ ጫና ውስጥ ወድቀዋል ተብለው ከተለዩት ሰባት የመንግሥት ልማት ድርጅቶች አጠቃላይ ዕዳ ውስጥ፣ ኮርፖሬሽኑ አመዛኙን በመውረስ ዕዳቸውን የመክፈል፣ እንዲሁም ድርጅቶቹን ከዕዳ አስተዳደር ወጥተው ትርጉም ያለው ኢኮኖሚያዊ ተልዕኮ እንዲወጡ የማስቻል አስተዳደራዊ ሚናም ተጥሎበታል። 

በመንግሥት የተለዩት ሰባቱ የመንግሥት ልማት ድርጅቶች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን፣ ኢትዮ ኢንጅነሪግ ግሩፕ (የቀድሞው ሜቴክ)፣ ኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን፣ የኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽንና ስኳር ኮርፖሬሽን ናቸው።

እነዚህ ድርጅቶች ከአገር ውስጥ አበዳሪዎች በዋናነት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክና ከውጭ አበዳሪዎች ተበድረው ያልመለሱት አጠቃላይ ዕዳ 780 ቢሊዮን ብር ወይም 19.5 ቢሊዮን ዶላር እንደሆነ፣ ገንዘብ ሚኒስቴር ሰሞኑን ይፋ ያደረገው መረጃ ያመለክታል።

አዲስ የሚቋቋመው ኮርፖሬሽን ሰባቱ ድርጅቶች ካለባቸው 780 ቢሊዮን ዶላር ውስጥ 570 ቢሊዮን ብሩን ወርሶ የመክፈልና የማስተዳደር ኃላፊነት ተጥሎበታል።

ኮርፖሬሾኑ የሚቋቋመው ራሱን በቻለ የንግድ ተቋም አደረጃጀት እንደሚሆን፣ ኃላፊነቱን ለመረከብ የሚያስፈልገው የመጀመርያ ካፒታልም ከመንግሥት በጀት ውጪ እንደሚሆን መረጃው ያመለክታል። 

በመሆኑም አሥር የመንግሥት ስኳር ፋብሪካዎችን በመሸጥ የሚገኘው ገቢ ኮርፖሬሽኑ ለሚያስፈልገው የመጀመርያ ካፒታል ፈሰስ እንዲደረግ የተወሰነ ሲሆን፣ ከስኳር ፋብሪካዎቹ ሽያጭ ከሚገኘው ገቢ በተጨማሪ በቅርቡ ለውጭ ኩባንያዎች ከሚሰጠው የቴሌኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ፈቃድ ክፍያ፣ እንዲሁም ከኢትዮ ቴሌኮም ከፊል ሽያጭ የሚገኘው ገቢ ትልቅ ድርሻ ወደ ኮርፖሬሽኑ ፈሰስ እንዲደረግ መወሰኑ ታውቋል።

መንግሥት በመጀመርያ ይዞት የነበረው ዕቅድ 13 ስኳር ፋብሪካዎችን ለመሸጥ የነበረ ሲሆን፣ ይህንንም ወደ ተግባር ለመቀየር የሁሉም ፋብሪካዎች አጠቃላይ ሀብትና ንብረት በገለልተኛ የኦዲት ኩባንያ እንዲገመት አድርጓል።

ይህንን የሀብትና ንብረት ግመታ እንዲያከናውንም ቡከር ቴት የተባለ የእንግሊዝ ኩባንያ ተቀጥሮ የግመታ ሥራውን ከዓመት በፊት አጠናቆ፣ ሪፖርቱንም ለመንግሥት እንዳቀረበ የተገኘው የሰነድ መረጃ ያመለክታል።

ኩባንያው ባካሄደው የግመታ ሥራ የ13 ስኳር ፋብሪካዎችን አጠቃላይ ሀብትና ንብረት ከዓመት በፊት በነበረ ዋጋ መሠረት 88 ቢሊዮን ብር ገምቷል። 

ይሁን አንጂ በተመሳሳይ ወቅት የነበረው የስኳር ፋብሪካዎቹ አጠቃላይ የአገር ውስጥ ዕዳ ወለድን ሳይጨምር ብቻውን 81.6 ቢሊዮን ብር የነበረ ሲሆን፣ በዚህ ተመሳሳይ ወቅት የፋብሪካዎቹ አጠቃላይ የውጭ ዕዳ መጠን ወለድን ሳይጨምር 2.1 ቢሊዮን ዶላር ነበር። 

በመሆኑም የ13 ስኳር ፋብሪካዎች አጠቃላይ የአገር ውስጥና የውጭ ዕዳ ወለድን ሳይጨምር፣ በአሁኑ ወቅት ባለው የውጭ ምንዛሪ ተመን ሥሌት 165.6 ቢሊዮን ብር ይሆናል። ይሁን እንጂ ይህ ግመታ ከተከናወነ በኋላ መንግሥት ተጨማሪ ወጪዎች በስኳር ፋብሪካዎች ላይ በማፍሰሱ የምርት ማሻሻያ ሥራዎችን፣ እንዲሁም የተመረጡ ፋብሪካዎችን የግንባታ ደረጃ የማሻሻል ጥረቶችን ያደረገ በመሆኑ፣ በቀደመው የሀብት መጠን ላይ ለውጥ እንደሚያመጣ መረዳት ይቻላል።

መንግሥት ከ13 ፋብሪካዎች ውስጥ አሥር ፋብሪካዎች እንዲሸጡና የሚገኘው ገቢም የዕዳ ክፍያን ለማስተዳደር ወደ የሚቋቋመው ኮርፖሬሽን ሙሉ በሙሉ ፈሰስ እንዲደረግ በመወሰኑ፣ አሥሩ ፋብሪካዎች በተገመቱበት የሀብት መጠን ብቻ ቢሸጡ፣ ኮርፖሬሽኑ ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ መቋቋሚያ ካፒታሉን ከስኳር ፋብሪካዎች ሽያጭ ሊያገኝ ይችላል። 

ከስኳር ፋብሪካዎቹ ሽያጭ በተጨማሪ ከቴሌኮሙዩኒኬሽን ዘርፍ ገቢ ከፍተኛ ድርሻ ለኮርፖሬሽኑ ፈሰስ የሚደረግ ሲሆን፣ የቴሌኮሙዩኒኬሽን ዘርፉን ለውጭ ገበያ ለመክፈት በተወሰነው መሠረት፣ ለሁለት የውጭ ኩባንያዎች የቴሌኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ፈቃድ ለመሰጥት የተጀመረው የጨረታ ሒደት ተጠናቆ፣ በመጪዎች ጥቂት ሳምንታት አሸናፊዎቹ ኩባንያዎች ይፋ እንደሚደረጉ ይጠበቃል።

ጨረታውን የሚያሸንፉት ሁለት ኩባንያዎች እያንዳንዳቸው ለ15 ዓመታት የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት ፈቃድ የሚያገኙ ሲሆን፣ ከሁለቱ ኩባንያዎች የፈቃድ ክፍያ በትንሹ በአማካይ መንግሥት ሁለት ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገቢ ሊያገኝ እንደሚችል የዘርፉ ባለሙያዎች ይገምታሉ። 

ለሁለት የውጭ ኩባንያዎች የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት ፈቃድ ለመስጠት በመካሄድ ላይ ካለው የጨረታ ሒደት ጎን ለጎን፣ መንግሥት በኢትዮ ቴሌኮም ላይ ያለውን 45 በመቶ ድርሻ ለመሸጥ ዝግጅት እያደረገ መሆኑ ይታወቃል። 

የኢትዮ ቴሌኮም ከፊል ሽያጭን አስመልክቶ እስካሁን ከተደረጉት ዝግጅቶች መካከል የተቋሙ አጠቃላይ ሀብትና ንብረት ግመታ፣ በውጭ የኦዲት ኩባንያ ተሠልቶ መጠናቀቁና ለመንግሥት መቅረቡ ይገኝበታል። 

የኢትዮ ቴሌኮም ከፊል ሽያጭ እስኪጠናቀቅ ድረስ የተካሄደው የሀብትና ንብረት ግመታ ውጤት በሚስጥር መጠበቅ ያለበት በመሆኑ ይፋ አልተደረገም፡፡ ነገር ግን የኢትዮ ቴሌኮም ሀብት በመንግሥት ከተገመተው 42 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱ ተገልጿል።

ይህንንም ተከትሎ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ከጥቂት ወራት በፊት የኢትዮ ቴሌኮምን የተከፈለ ማቋቋሚያ ካፒታል ከ40 ቢሊዮን ብር ወደ 400 ቢሊዮን ብር ማሳደጉ ይታወሳል። (ሪፖርተር)

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: abay tsehaye, sugar factory, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule