• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በአፍራሽ ሥራ የተጠመዱ የረድኤት ድርጅቶች ሊባረሩ ይችላሉ

July 15, 2021 01:09 pm by Editor Leave a Comment

የዕርዳታ አቅራቢዎች ከኢትዮጵያ ኢትዮጵያ በአፍራሽ ስራ ላይ ተሰማርተዋል ያለቻቸውን አንዳንድ የእርዳታ አቅራቢዎችን ከሀገር ልታባርር እንደምትችል አስጠነቀቀች።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ዛሬ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ ሰጥረው ነበር።

አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ፥ “አንዳንድ የሰብዓዊ እርዳታ አስተባባሪዎች በሌሎች ሀገራት እንደተለመደው በኢትዮጵያም ከዚህ በፊት እንደታየው ከእርዳታ እህልና ከእርዳታ አቅርቦት ጋር በማያያዝ ሌላኛውን ወገን የማስታጠቅ ፣ ትግሉ፣ እንቅስቃሴው እንዳይቆም፣ ቀውሱ እንዳይበርድ ለማድረግ የሚያስችል አፍራሽ ሚና እንደሚጫወቱ ይታወቃል” ብለዋል።

አክለውም፥ በሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት ባለፉት 8 ወራት ይህ ሌላኛውን ወገን ለማስታጠቅ የሚደረገው ሙከራ እንዳጋጠመ ፤ ይህ ጉዳይ መልክ መያዝ እንዳለበት መንግስት ሲያሳስብ እንደነበር ገልፀዋል።

አምባሳደሩ፥ “አንዳንድ አካላት በተለይም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰብዓዊ እርዳታ እናስተባብራለን የሚሉ አንዳንድ ወገኖች በተናጠል ኢትዮጵያ ውስጥ ተቀምጠው እንዲሚያስተባብሩ  ከተመደቡ ሰዎቻቸው ውጭ ከርቀት ሆነው ከእርዳታ ይልቅ የፕሮፖጋንዳ ስራ የማስተባበር፣ ኢትዮጵያን የማዋከብ እና የማጠልሸት ዘመቻ ከፍተው ይገኛሉ” ሲሉ ወቅሰዋል።

መንግስት ከዚህ አይነት አፍራሽ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ለማስጠንቀቅ ሞክሯል ያሉት አምባሳደር ሬድዋን ይህን ድርጊት የማይቆም ከሆነ መንግስት ሀገርን ለማዳን ስለሚገደድ ከአንዳንዶቹ ጋር አብሮ የመስራቱን ሁኔታ እንደሚያጤን አንዳንዶቹንም ከሀገር ለማስወጣት እንደሚገደድ አስጠንቅቀዋል።

ተመድ ሆነ ማንኛውም ኢትዮጵያን እረዳለሁ የሚል /እርዳታ አቀርባለሁ የሚል አካል ስራው በእርዳታና ሰብዓዊነት ላይ ብቻ ታጥሮ መንቀሳቀስ እንዳለበት መንግስት ያሳስባል ሲሉም አክለዋል። (ቲክቫህ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: News, Right Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule