• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስብሃት “እርቅን” እንሞክራለን፤ ከባልደረቦቼ ጋር እመክራለሁ አሉ

May 23, 2014 11:31 pm by Editor 6 Comments

ባለፈው ሳምንት የጀርመን ድምጽ ሬዲዮ የተቃዋሚ ፓርቲ ወኪሎችንና አቶ ስብሃትን ባንድነት በየተራ አናግሮ ነበር። ከውይይቱ የተለመደ ክርክር በዘለለ አቶ ስብሃት እርቅ አስፈላጊ መሆኑንን ማመናቸው የተለየ ጉዳይ ነበር። እንደ እርሳቸው አነጋገር አሁን የተጀመረውን መልካም የልማት ስራ ለማስቀጠል እርቅ አስፈላጊ ነው። የእርቅን አስፈላጊነት በማመን ከባልደረቦቻቸው ጋር በመምከር የእርቅ ጉባኤ ለማዘጋጀት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።

አቶ ስብሃት “የተቃዋሚ ፓርቲ አለ ብዬ አላምንም” በማለት ተቃዋሚዎችን እንደወትሮው ሁሉ ዘልፈዋል። “መደብ የላቸውም” ሲሉ ተቃዋሚዎችን ጭራሽ እንደ ፓርቲ እንደማይቆጥሯቸው የተናገሩት አቶ ስብሃት ከዘለፋቸው በኋላ ስለ እርቅ አግባብ መናገራቸውን፣ ጠያቂው እሳቸው ባነሱት አዲስ ሃሳብ ላይ በመንተራስ ማረጋገጫ ሲጠይቃቸው “ከጓደኞቼ ጋር መክሬ” በማለት በቅርቡ የእርቅ መድረክ እንዲፈጠር እንደሚተጉ መናገራቸውን ተከትሎ እርቅ ላይ እንሰራለን ከሚሉ ወገኖች ምላሽ አልተሰማም።

አሁን ባለው ውጥረት የነገሰበት የኢትዮጵያ ፖለቲካ አብዛኞችን ስጋት ውስጥ የከተተ ነው። በስዊድን አገር በአንድ የእራት ግብዣ ላይ ተገኙ የትግራይ ተወላጅ ለጎልጉል እንደተናገሩት “በጎሳና በክልል ተለይቶ የሚንቦገቦገው የጥላቻ ፖለቲካ መጠኑ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ አስግቶኛል። እርቅ ብቸኛ መፍትሔ ነው። በዚህ ሃሳብ ላይ መስራት ግድ ነው” የሚል አስተያየት ሰጥተዋል።

በፍርሃቻ ከሁሉም ያጣ ላለመሆን ኢህአዴግን የሚደግፉ እንዳሉ ያመለከቱት እኚሁ ሰው የኢትዮጵያ ጉዳይ በእጅጉ ዕረፍት እንደነሳቸው አልሸሸጉም። “ስብሃት ነጋ እርቅ ላይ ለመስራት ከልብ ያሰቡ ይመስልዎታል?” በሚል አስተያየታቸውን የተጠየቁት እኚሁ ሰው “ኢህአዴግም ሆነ ህወሃት እኮ የሰዎች ጥርቅም እንጂ ሌላ ግዑዝ ነገር አይደሉም። ችግሩን ከሁላችንም በላይ ይረዱታል። እንደውም እነሱ የሚያውቁትን ያህል የችግሩን አሳሳቢነት ተራው ነዋሪ ቢረዳ ልቡ በድንጋጤ ሊቆም ይችላል” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል። አያያዘውም ኢህአዴግ ችግሮች ገንፍለው እንዳይወጡ የሰጋበት ደረጃ እንደሚገኝ አመልክተዋል። በሁሉም አቅጣጫ የሚያገኟቸው ወገኖች የሚነግሯቸው ይህንኑ የስጋት ጉዳይ እንደሆነም ተናግረዋል።

ኢህአዴግ የሚነሳበትን ተቃውሞ በጥይት እያረገበ መዝለቅ እንደማይችል ብዙዎች እየተናገሩ ነው። ኢህአዴግ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ከማስወገድ ይልቅ ጥይትን መምረጡ የበቀሉን ደረጃ እያናረው ስለመሆኑም ክርክር የለም። ኢህአዴግ የገደላቸው ወገኖች በሙሉ ወገን አላቸው፣ ዘር አላቸው፣ ተቆርቋሪ አላቸው፣ ጎሳ አላቸው፣ ምድር አላቸው፣ ቀበሌና ቀዬ አላቸው፣ ወዳጆችና ተከራካሪዎች አሏቸው በሚል ኢህአዴግ ያልተመከረበት ወቅትና ጊዜ ለም። እንደውም ባንድ ወቅት ለጎልጉል አስተያየት የሰጡ “ብሶት ህወሃትን ብቻ አይወልድም፣ የብሶት የበኩር ልጅ ህወሃት ብቻም ሊሆን አይችልም” ብለው ነበር።

ከግድያው፣ ከእስሩ፣ ከአፈናው፣ ከድብዳው፣ ከማስፈራራቱ በተጨማሪ በአገሪቱ ሃብት ላይ ኢህአዴግ እየፈጸመ ያለው ፍትሃዊነት የጎደለው የንግድ ስምምነትና የንግድ ውድድር ያስቀየማቸው ወገኖች ቁጥርም ቀላል አይደለም። አብዛኞች በተለያዩ ወቅቶች ሲገልጹት እንደነበረው ኢህአዴግ ባለስልጣናቱ የህዝብን ሃብት በሽርክና በመቸብቸብ ሃብት አፍርተዋል። እነርሱ እንዳሻቸው እየዘረፉ ምስኪን አርሶ አደሮች ለእለት ጉርስ እየጫሩ ከሚኖሩበት ቀዬ ከነቤተሰቦቻቸው እንደ ባዕድ በጎሳ እየተለዩ እንዲፈናቀሉ ተደርጓል። ኢህአዴግ ካለበት ፍርሃቻ በመነሳት በየጊዜው በደልን እያበዛ ጠላቶቹን በማብዛቱ ስጋት የገባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ሰላማቸውን አጥተዋል።

በበዳዩ ወገኖች ተርታ በተሰለፉና በተበዳዩ ወገኖች ጎን ባሉት ዜጎች መካከል እየታየ ያለው የበቀል ስሜት ልክ እንዳጣ የሚናገሩ ክፍሎች አሁን አገሪቱ ላለችበት አጣብቂኝ ወቅት መፍትሔው እርቅ እንደሆነ ሲወተውቱ ዓመታት ተቆጥረዋል። አቶ ስብሃት የተናገሩት እርቅ ሃሳብ እውነተኛ ይሁን ከምርጫ ጋር በተያያዘ የተቃዋሚዎችንና የህዝቡን ስሜት “ለማቀዛቀዝ” ኢህአዴግ እንደለመደው ሊጠቀምበት የፈለገው ማደናገሪያ ይሁን በእርግጠኝነት ለመናገር አይቻልም፡፡ ሆኖም ግን ስብሃት ለተናገሩት የእርቅ ሃሳብ ድጋፍ በመስጠት አገሪቱ ላይ የነገሰውን የጥላቻና የቁጣ ፖለቲካ ማምከን አስፈላጊ ቢሆንም እስካሁን ከሌሎች ወገኖች የተሰማ ነገር አለመኖሩ አስገራሚ ሆኗል። በወቅቱ የጀርመን ድምጽ ሬዲዮ ዘጋቢ ነጋሽ መሐመድ የጋበዛቸው የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ግን ኢህአዴግ የእርቅ ጥሪ ካቀረበ እንደሚስማሙ ተናግረዋል።

ጥቅምት 25፤2006 ዓም (November 4, 2013) ላይ ጎልጉል “በህወሃት ውስጥ የዕርቅ ሃሳብ መነሳቱ ተሰማ” በሚል ርዕስ ባሰፈረው ዜና ላይ ምንጭ አድርጎ የጠቀሳቸው “የኢህአዴግ ከፍተኛ አመራርና ዲፕሎማት እንዳሉት ህወሃት ውስጥ “እርቅ አስፈላጊ ነው” በሚል እቅድ እንዲያዝና እንዲሰራበት ሃሳብ ቀርቧል። በድርጅቱ ውስጥ በተፈጠረ አለመተማመን ሳቢያ ስጋት የገባቸው የህወሃት ሰዎች የእርቅ ሃሳብ እንዲሰራበት ያቀረቡት ሃሳብ ግን በመደበኛ ስብሰባ አይደለም” ማለታቸውን ዘግበን ነበር፡፡

የዕርቁን ሃሳብ እንዲነሳ ያደረጉ ምክንያቶች በርካታ ቢሆኑም በዜና ዘገባው ላይ የቀረበው ቀዳሚ ሃሳብ “በህወሃትና ህወሃት በሚያዛቸው አቻ ፓርቲዎች መካከል ያለው የመከባበርና የመገዛት ስሜት ከመለስ ሞት በኋላ መበላሸቱ፣ በኢህአዴግም ሆነ በህወሃት ደረጃ የተፈጠረው ልዩነትና በሙስና ስም የተጀመረውን ዘመቻ ተከትሎ የተነሳው አለመግባባት አደጋ እንዳያስከትል መፈራቱ” ጎልጉል እንደ ምክንያት ጠቅሶ ነበር፡፡

ጎልጉል በዝርዝር ባሰፈረው በዚህ የዜና ዘገባ ላይ ምንጭ አድርጎ የጠቀሳቸው የኢህአዴግ አመራርና ዲፕሎማት በሰጡት አስተያየት ዕርቅ “በቅርብ ጊዜ ውስጥ የሚታይ ነው” ማለታቸውን ዘግቦ ነበር፡፡ ዲፕሎማቱ ሲቀጥሉም “አንዱ እኔ ነኝ። ሌሎችም አሉ። ብዙዎች ሰላማዊ ህይወት ናፍቆናል። የተወሳሰበውን አገራችንን ፖለቲካ አካሄድ ለመተንበይ ተቸግረናል። መፍትሔው የእርቅ ሃሳብ ብቻ ነው” ብለው ነበር።

አስተያየታቸውን ሲያጠናቅቁም “በድርጅታቸው ውስጥ የበላይና የበታች መጥፋቱን፣ የበታቹ የበላዩን እንደሚያዘው፣ አንዳንዴ የበላይ መስለው ምንም ዓይነት የውሳኔ ሰጪነት ሚና የሌላቸው ክፍሎች መኖራቸው የአደባባይ ምስጢር” መሆኑን አልሸሸጉም ነበር፡፡

በመጨረሻም በዕርቅ ሃሳብ ላይ ቀዳሚውን ቦታ የሚወስዱት ስብሃት መሆናቸውን ሲገልጹ “እርቅና ዋስትና የሚሰጥ አግባብ ቢያገኝ የመጀመሪያው ስምምነት ፈራሚና ደጋፊ ስብሃት ነው። ቀሪውን የጡረታ ዘመኑንን በትዝታ ያለውን እየበላ መኖር ይፈልጋል። እሱ ብቻ ሳይሆን ብዙዎች ተመሳሳይ ፍላጎት አለን። አስከማውቀው ድረስ ችግሩ ከራስ ምግባርና ከድርጅት ተልዕኮ በመነጨ የተሰሩት ጥፋቶችና ሃጢያቶች መብዛታቸው ከለውጥ በኋላ የሚያመጣቸው የተጠያቂነት ጣጣዎች ናቸው” ብለዋል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. ደምመላሽ says

    May 24, 2014 09:41 am at 9:41 am

    ለመሆኑ ጉልጉል መረጃውን ያገኘው ከጀርመን ሬዲዮ ነው።እኔ አሁን የጀርመን ፣የአሜሪካን፣የወያኔን ድምፅ መለየት ተስኖኛል።ሙዚቃቸው ፈፅሞ አንድ ነውና አታዘናጉን ።

    Reply
  2. ermias says

    May 24, 2014 10:14 am at 10:14 am

    ለማላውቅህ ኢህአዴግ
    1 2 3……23,በዚህ ቁጥር ከእድሜዬ ውጭ ሌላ ነገር ቆጠሬ አላውቅም።ለነገሩ አንተም እንደኔው ነህ።እኩያዬ ስለሆንክ እንደጏደኛ ልንገርህ።ስላንተ ብዙ ይወራል ይፃፋል፤አንተ ስለራስህ ከጻፍከው ውጭ አንድም ስለጥሩነትህ ሚመሠክርልህ በሀገር አጣው።እንዲው ሳስብህ ቀንድ ያለህ በኮቴህ ዱካ ባለፍክበት ሁሉ ጠባሣህን ያስቀመጥክ፤እራስህን በጨለምተኝነት ገንዘህ በጭቁን አገዛዝህ ለመቅበር የወሰንክ ሚካኤል በመጫሚያው ረግጦ የሚቀጠቅጥህ ሠይጣንን ትመስለኛለህ።
    (አያሩኔ)ነኝ ያገርህ ልጅ

    Reply
  3. aradaw says

    May 27, 2014 07:17 pm at 7:17 pm

    some time it is necessary to say a spade is a spade, enough is enough. I think the time has passed for any reconciliation. It is time to press for the overthrow of Woyane agazis. Rekindle the struggle in every possible ways, by individuals , groups. Agazis are shaken. They lost the whole population including their bases. The opportunists who became part are now slowly going away. Remember the the end of Derg. What we see now is the same.

    Reply
  4. Bekele says

    May 29, 2014 06:01 pm at 6:01 pm

    Here is a post about sebhat.
    http://erecycler.wordpress.com/2014/05/29/%E1%8B%88%E1%8B%AD-%E1%88%98%E1%8C%8D%E1%8B%B0%E1%88%8D%E1%8D%A3-%E1%8B%88%E1%8B%AD-%E1%88%98%E1%88%9D%E1%88%B0%E1%88%8D/

    Reply
  5. Negassi Y. AMAN says

    May 30, 2014 12:32 am at 12:32 am

    There are currently two big mistakes in Ethiopian scenario.
    And these are by
    1. woyane groups now defunct and
    2. the Neftegna Amhara followers of the Dergeu also now defunct.
    Both these defunct groups whose political appeal is already expired
    in New post Meles Ethiopia…….; though they try hard to look or appear
    different to the public they are the same and exactly a copy of each other
    in all their political beliefs and methods.
    A. They are both staunch proponents and advocates of Ethnic Nationalities
    political view though they approach it from different and opposing starting
    corners to suit their current situation and reality. The goal is the same. But
    UNFORTUNATELY with the good steps Ethiopia took and travelled it has made
    and rendered their un-appealing politics dysfunctional and expired.

    Reply
  6. AMAN ( part ii) says

    May 30, 2014 12:54 am at 12:54 am

    B. The UDJ and the Woyane which are both advocate factions for the supremacy
    of Amhara and Tigray respectively have drowned themselves in the nation-nationalities
    politics which they intended it for their vehicle to take them to power by pretending
    against it ( the former) and for it (the later) both for their own scheme of different
    approach but same goal.
    UDJ WHILE PRETENDING AGAINST AND CONDEMNING IT MAKES BEST USE OF IT IN
    ATTEMPTING TO PUT AMHARA DOMINANCE OVER THE REST AS IF RESISTING BUT
    ACTUALLY MAKING WOYANE/TPLF AS A SCAPEGOAT FOR ITS VEILED OBJECTIVES.
    WHILE THE OTHER (WOYANE/TPLF),
    APPROACHES IT DIRECT OWNING TO ITS STRENGTH IN STATE POWER CONTROL AND
    AS IF IT IS THE ONLY SOLUTION.
    Therefore this direct and indirect approach has the same objective as its GOAL. It is only
    veiled or apparent to hide or reflect their current status or situation which is reflected back by the EPRDF mirror of its ongoing new transformational system of free speech and democratic governance though at developmental stage ( it was able to reflect quite good and so much
    to the public of reactionary dictatorial & underground works of defunct politics and political factions).

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule