• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለ “የጣመ ውይይት” ምላሽ

January 29, 2013 05:26 am by Editor Leave a Comment

“እኛ የመጨረሻዎቹ“ የሚል አንድ ጽሁፍ በድረ ገጾች የሚሽከረከር አይቼ፣ እውን እንዴት ቀን ቀንን ዓመት ዓመትን እየተካው ዓለም ምንኛ በተጨባጭ በግብርም፣ በሃሳብ በመንፈስም እንደተሽከረከረች እንደገና ልብ ብዬ ነበር። እኔም የትላንት ሰው ስለሆንኩ።

ነገር ግን እዚህ የውይይት መድረክ ውስጥ ሰገባ፣ የሃገሬ ልጆች አሁንም የዛሬ ሰላሳ ዓመት የፖለቲካ ቡድኖች የተከራከሩበትን፣ የተናቆሩበትን፣ ከዚያም ብዙ መዘዝና መዓት ሃገራችን የገባችበትን የፖለቲካ ልዩነቶችና ነጥቦች (ለምሳሌ የትጥቅ ትግል ዛሬ ያስፈልጋል፣ አያስፈልግም፣ ወይንም ግንባር፣ አንድነት፣ ወዘተ) አንስተው ዛሬም በ21ኛው ክፍለ ዘመን ሲከራከሩበት ስሰማና ሳነብ፣ ጉድ ነው፣ ዛሬም እዛው የዛሬ ሰላሳ ዓመት ከገባንበት ጭቃ፣ ይቅርታ ይደረግልኝና፣ አልወጣንም ማለት ተገደድሁ። ስለሆነም ዝርዝር ውስጥ ገብቼ እንዲህ ቢሆን እንዲህ ማለቴ ነው፣ እያልኩ ላሳምንም ልከራከርም ከቶም አያምረኝም፤ እውነት ለመናገርም ሰፊው አንባቢና ባለጉዳይ፣ ሰፊው የተበደለው ህዝባችን እንዲህ ዓይነቱ ውሃ ቀጠነ ሰልችቶታል፤ በሰላምና በብልህነት የሚታገልና የሚያታግለው ነው የሚሻው፤ ይህን ደግሞ እሩቅ ሳንሄድ ባለፈው ዓመት ሙዝሊም የኢትዮጵያ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን አሳይተውናል። ከሰሜን አፍሪቃው፣ በቱኒዝያ ጀምሮ ወደ ግብጽ ዘልቆ እስከዛሬ ድረስ በቆራጥነትና በብስለት ከሚራመዱት ህዝቦች ትግል አያሌ ትምህርት በመቅሰም!

እንዲህም በመሆኑ ካላይ ያነሳሁት ውይይት ውስጥ ገብቶ በሬ ወለደ ከማለት፣ በተለይም የግብጽ ወጣቶች ትግል በምን ዘይቤና ብልሃት ወደ ህዝቡ ሰረጾ በሰላማዊ አመጽ፥ በአልገዛም ባይነት፣ ያን እስተአፍ ጢሙ ድረስ የታጠቀን የሙባረክ መንግሥትን እንዴት እንዳምበረከከ አገናዝቦ፣ ምን ትምህርት እንደሚቀመስ ማየቱን እመርጣለሁ። መንግስት በሰላማዊ ታጋይነታቸው ብቻ ፈርቶዋቸው (መንግሥት የታጠቀ ቡድን አይፈራም!) በእስር ላይ የሚያማቅቃቸው፣ እነ እስክንድርን፣ እነ አንዷለምን በመንፈስ ያጠናክርልን እያልን፣ እኛም /ማለትም የተረፈው ሌላው የህብረሰብ ክፍልም ማለቴ ነው/ ከግማሽ ጎናችን ከሙስሊም ወገኖቻችን ጎን ቆመን ይልቅ፣ ያን ምድር እንዴት በሰላም ትግል ልናንቀጠቅጠው እንችላለን ብለን ብንመራመር  እጅግ ይበጃል እላለሁ። በመሆኑም በአፍላው የግብጽ ወጣቶች ትግል ጊዜ፣ ከግብጽ ሰላማዊ አመጽ ምን እንማራለን ስል፣ የወሰድኳቸውን አንዳንድ ማስታወሻዎች እዚህ የውይይት መድረካችሁ ላይ ልጋብዛችህ እወዳለሁ። ስለጉዳያችን አንድ፥ሁለት ፍሬ ነገር አያጣውምና፣ እስቲ፣ ይህንን ከተጻፈ ጥቂት የሰነበተ ጽሁፍ ተመልከቱት:-

Short Lessons …. From NEW EGYPT – HOW They Did It!

ሕሊና ብርሃኑ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule