• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“በጥቁር ገበያ” ምንዛሪ የተጠረጠሩ ሱቆች ታሸጉ

September 15, 2020 11:36 am by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ መንግስት አሁን በአገልግሎት ላይ የሚገኙትን የብር የገንዘብ አይነቶች እንዲሚቀይር በትላንትናው ዕለት ማስታወቁን ተከትሎ የ“ጥቁር ገበያ”ውን ለመቆጣጠር እርምጃ መውሰድ ተጀመረ።

በአዲስ አበባ ከባንክ ውጭ የሚደረጉ የውጭ ሀገር ገንዘብ ግብይቶችን በድብቅ ያከናውናሉ ከተባሉ ሱቆች መካከል የተወሰኑት ከትላንት ጀምሮ እንዲታሸጉ ተደርገዋል። 

የእርምጃው ሰለባ የሆኑት በይፋ ከሚታወቁባቸው አገልግሎቶች ባሻገር የውጭ ሀገር ገንዘቦች ምንዛሬን በተደራቢነት የሚሰጡ ሱቆች ናቸው። በኢትዮጵያ ሆቴል እና ጋንዲ ሆስፒታል አካባቢ የሚገኙት እነዚህ ሱቆች “ታሽጓል” የሚል ጽሁፍ እና ማህተም የሰፈረባቸው ወረቀቶች በየበሮቻቸው ላይ መለጠፋቸውን ዛሬ ረፋዱን በቦታው የተገኘው የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ዘጋቢ ተመልክቷል።

በሱቆቹ አካባቢ የአዲስ አበባ ፖሊስ የደንብ ልብስ የለበሱ የጸጥታ ኃይሎች በርከት ብለው የሚታዩ ሲሆን የተወሰኑቱ በወንበሮች ላይ ተቀምጠው ጥበቃ ሲያደርጉ ተስተውለዋል።

ፖሊስ የተወሰኑ ሱቆች የሚገኙባቸውን እና ቀደም ሲል እግረኞችና ተሽከርካሪዎች ይተላለፉባቸው የነበሩ መጋቢ መንገዶችን ለተጠቃሚዎች ዝግ አድርጓል። ከተዘጉት መንገዶች መካከል ከጋንዲ ሆስፒታል ወደ ብሔራዊ ትያትር የሚወስደው ማቋረጫ እና ከኢትዮጵያ ሆቴል ጎን የሚገኝ፣ ተሽከርካሪዎች በአንድ አቅጣጫ ብቻ የሚተላለፉበት መስመር ይገኙበታል።

በሱቆቹ አቅራቢያ ሸቀጦችን በመቸርቸር የሚተዳደር አንድ ወጣት ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” እንደተናገረው፤ ሱቆቹ የተዘጉት ትላንት ሰኞ አስር ሰዓት ገደማ በአካባቢው ድንገተኛ ፍተሻ ከተደረገ በኋላ ነው። በአካባቢው ባለ ሆቴል እና ፋርማሲ የሚሰሩ ሁለት ግለሰቦች ይህንኑ የወጣቱን ገለጻ አረጋግጠዋል።

የትላንትናው ድንገተኛ ፍተሻ በሚደረግበት ወቅት የፊት እና የጉልበት መከላከያ ያደረጉ የፌደራል ፖሊስ አባላት በአካባቢው ጥብቅ የጸጥታ ቁጥጥር ሲያደርጉ እንደነበር ወጣቱ ገልጿል። በፍተሻው ጋንዲ ሆስፒታል አካባቢ በነበሩ ሱቆች የተቀመጡ የውጭ ሀገር ገንዘቦች በጸጥታ ሃይሎች እንደተወሰዱ መስማቱንም አክሏል። 

ዛሬ የታሸጉት ሱቆች

ነባሮቹ የ10፣ የ50 እና የ100 ብር መገበያያዎች መቀየራቸውን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በትላንትናው ዕለት በሰጡት ማብራሪያ፤ ከፋይናንስ ተቋማት ውጪ የተከማቹ ገንዘቦችን ለመያዝ በየቦታው ድንገተኛ ፍተሻ እንደሚደረግ አስታውቀው ነበር። ድንገተኛ ፍተሻዎቹ የሚደረጉት “በሚጠረጠሩ ቦታዎች” ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ አሰሳ የግለሰብ ቤትም ይሁን የንግድ ቦታ ሊካተት እንደሚችል ጠቁመዋል።

“የሕግ አስከባሪ ተቋማት አንደኛ ጥቁር ገበያ፤ ሁለተኛ አየር መንገድ ከዛሬ ጀምሮ ባስቀመጥንው አቅጣጫ መሠረት እያንዳንዷ ሻንጣ ማስወጣት፤ ማስገባት በማይችል በአየር መንገድ ጥብቅ ሴኪዩሪቲ ይደረጋል። በድንበር አካባቢዎች በተለይ ከጅቡቲ ሶማሌ ሱዳን ከፍተኛ ገንዘብ እንዳለ ይታወቃል። በነዳጅ ቦቴም ይሁን በተለያየ መንገድ ገንዘቡ እንዳይገባ የሕግ አስከባሪ ተቋማት በወጣው ዕቅድ መሠረት ከመነሻው ጀምሮ ሰፊ ጥበቃ ያደርጋሉ። እኛ ገንዘቡን አንፈልገውም። ወርሰው የሕግ አስከባሪ ተቋማት ይጠናከሩበታል” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስጠንቅቀዋል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ባለፉት ሁለት ተኩል ዓመታት የአሸባሪው የወንበዴዎች ቡድን ህወሓት አባላትና ደጋፊዎች ብር ይቀየራል በሚል እሳቤ ከሕዝብ የዘረፉትን ወደ ዶላር ሲቀይሩ እንደነበር ይታወቃል። የብር ኖቶች መቀየራቸውን ተከትሎ ይህንን ሥራቸውን በሥፋት እንደሚያከናውኑት በመረዳት በተለይ በዳያስፖራ የሚገኘው ወገን ለጥቂት ብሮች ልዩነት በሚል በጥቁር ገበያ የሚልከው ገንዘብ መልሶ አገር ለማፍረስ ተግባር እንደሚውል በመገንዘብ ከዚህ ሥራ እንዲታቀብ አገራዊ ጥሪ ቀርቧል።

ጭንቅላቱ የደረቀውና መቀሌ በየሆቴሉ የመሸገው ራሱን ህወሓት እያለ የሚጠራው የወንበዴዎች ጥርቅም በቅርብ ጊዜ ውስጥ ኪሱም እንደሚደርቅ ይጠበቃል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: black market, new currency, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule