• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“በጥቁር ገበያ” ምንዛሪ የተጠረጠሩ ሱቆች ታሸጉ

September 15, 2020 11:36 am by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ መንግስት አሁን በአገልግሎት ላይ የሚገኙትን የብር የገንዘብ አይነቶች እንዲሚቀይር በትላንትናው ዕለት ማስታወቁን ተከትሎ የ“ጥቁር ገበያ”ውን ለመቆጣጠር እርምጃ መውሰድ ተጀመረ።

በአዲስ አበባ ከባንክ ውጭ የሚደረጉ የውጭ ሀገር ገንዘብ ግብይቶችን በድብቅ ያከናውናሉ ከተባሉ ሱቆች መካከል የተወሰኑት ከትላንት ጀምሮ እንዲታሸጉ ተደርገዋል። 

የእርምጃው ሰለባ የሆኑት በይፋ ከሚታወቁባቸው አገልግሎቶች ባሻገር የውጭ ሀገር ገንዘቦች ምንዛሬን በተደራቢነት የሚሰጡ ሱቆች ናቸው። በኢትዮጵያ ሆቴል እና ጋንዲ ሆስፒታል አካባቢ የሚገኙት እነዚህ ሱቆች “ታሽጓል” የሚል ጽሁፍ እና ማህተም የሰፈረባቸው ወረቀቶች በየበሮቻቸው ላይ መለጠፋቸውን ዛሬ ረፋዱን በቦታው የተገኘው የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ዘጋቢ ተመልክቷል።

በሱቆቹ አካባቢ የአዲስ አበባ ፖሊስ የደንብ ልብስ የለበሱ የጸጥታ ኃይሎች በርከት ብለው የሚታዩ ሲሆን የተወሰኑቱ በወንበሮች ላይ ተቀምጠው ጥበቃ ሲያደርጉ ተስተውለዋል።

ፖሊስ የተወሰኑ ሱቆች የሚገኙባቸውን እና ቀደም ሲል እግረኞችና ተሽከርካሪዎች ይተላለፉባቸው የነበሩ መጋቢ መንገዶችን ለተጠቃሚዎች ዝግ አድርጓል። ከተዘጉት መንገዶች መካከል ከጋንዲ ሆስፒታል ወደ ብሔራዊ ትያትር የሚወስደው ማቋረጫ እና ከኢትዮጵያ ሆቴል ጎን የሚገኝ፣ ተሽከርካሪዎች በአንድ አቅጣጫ ብቻ የሚተላለፉበት መስመር ይገኙበታል።

በሱቆቹ አቅራቢያ ሸቀጦችን በመቸርቸር የሚተዳደር አንድ ወጣት ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” እንደተናገረው፤ ሱቆቹ የተዘጉት ትላንት ሰኞ አስር ሰዓት ገደማ በአካባቢው ድንገተኛ ፍተሻ ከተደረገ በኋላ ነው። በአካባቢው ባለ ሆቴል እና ፋርማሲ የሚሰሩ ሁለት ግለሰቦች ይህንኑ የወጣቱን ገለጻ አረጋግጠዋል።

የትላንትናው ድንገተኛ ፍተሻ በሚደረግበት ወቅት የፊት እና የጉልበት መከላከያ ያደረጉ የፌደራል ፖሊስ አባላት በአካባቢው ጥብቅ የጸጥታ ቁጥጥር ሲያደርጉ እንደነበር ወጣቱ ገልጿል። በፍተሻው ጋንዲ ሆስፒታል አካባቢ በነበሩ ሱቆች የተቀመጡ የውጭ ሀገር ገንዘቦች በጸጥታ ሃይሎች እንደተወሰዱ መስማቱንም አክሏል። 

ዛሬ የታሸጉት ሱቆች

ነባሮቹ የ10፣ የ50 እና የ100 ብር መገበያያዎች መቀየራቸውን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በትላንትናው ዕለት በሰጡት ማብራሪያ፤ ከፋይናንስ ተቋማት ውጪ የተከማቹ ገንዘቦችን ለመያዝ በየቦታው ድንገተኛ ፍተሻ እንደሚደረግ አስታውቀው ነበር። ድንገተኛ ፍተሻዎቹ የሚደረጉት “በሚጠረጠሩ ቦታዎች” ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ አሰሳ የግለሰብ ቤትም ይሁን የንግድ ቦታ ሊካተት እንደሚችል ጠቁመዋል።

“የሕግ አስከባሪ ተቋማት አንደኛ ጥቁር ገበያ፤ ሁለተኛ አየር መንገድ ከዛሬ ጀምሮ ባስቀመጥንው አቅጣጫ መሠረት እያንዳንዷ ሻንጣ ማስወጣት፤ ማስገባት በማይችል በአየር መንገድ ጥብቅ ሴኪዩሪቲ ይደረጋል። በድንበር አካባቢዎች በተለይ ከጅቡቲ ሶማሌ ሱዳን ከፍተኛ ገንዘብ እንዳለ ይታወቃል። በነዳጅ ቦቴም ይሁን በተለያየ መንገድ ገንዘቡ እንዳይገባ የሕግ አስከባሪ ተቋማት በወጣው ዕቅድ መሠረት ከመነሻው ጀምሮ ሰፊ ጥበቃ ያደርጋሉ። እኛ ገንዘቡን አንፈልገውም። ወርሰው የሕግ አስከባሪ ተቋማት ይጠናከሩበታል” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስጠንቅቀዋል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ባለፉት ሁለት ተኩል ዓመታት የአሸባሪው የወንበዴዎች ቡድን ህወሓት አባላትና ደጋፊዎች ብር ይቀየራል በሚል እሳቤ ከሕዝብ የዘረፉትን ወደ ዶላር ሲቀይሩ እንደነበር ይታወቃል። የብር ኖቶች መቀየራቸውን ተከትሎ ይህንን ሥራቸውን በሥፋት እንደሚያከናውኑት በመረዳት በተለይ በዳያስፖራ የሚገኘው ወገን ለጥቂት ብሮች ልዩነት በሚል በጥቁር ገበያ የሚልከው ገንዘብ መልሶ አገር ለማፍረስ ተግባር እንደሚውል በመገንዘብ ከዚህ ሥራ እንዲታቀብ አገራዊ ጥሪ ቀርቧል።

ጭንቅላቱ የደረቀውና መቀሌ በየሆቴሉ የመሸገው ራሱን ህወሓት እያለ የሚጠራው የወንበዴዎች ጥርቅም በቅርብ ጊዜ ውስጥ ኪሱም እንደሚደርቅ ይጠበቃል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: black market, new currency, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule