• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“በጥቁር ገበያ” ምንዛሪ የተጠረጠሩ ሱቆች ታሸጉ

September 15, 2020 11:36 am by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ መንግስት አሁን በአገልግሎት ላይ የሚገኙትን የብር የገንዘብ አይነቶች እንዲሚቀይር በትላንትናው ዕለት ማስታወቁን ተከትሎ የ“ጥቁር ገበያ”ውን ለመቆጣጠር እርምጃ መውሰድ ተጀመረ።

በአዲስ አበባ ከባንክ ውጭ የሚደረጉ የውጭ ሀገር ገንዘብ ግብይቶችን በድብቅ ያከናውናሉ ከተባሉ ሱቆች መካከል የተወሰኑት ከትላንት ጀምሮ እንዲታሸጉ ተደርገዋል። 

የእርምጃው ሰለባ የሆኑት በይፋ ከሚታወቁባቸው አገልግሎቶች ባሻገር የውጭ ሀገር ገንዘቦች ምንዛሬን በተደራቢነት የሚሰጡ ሱቆች ናቸው። በኢትዮጵያ ሆቴል እና ጋንዲ ሆስፒታል አካባቢ የሚገኙት እነዚህ ሱቆች “ታሽጓል” የሚል ጽሁፍ እና ማህተም የሰፈረባቸው ወረቀቶች በየበሮቻቸው ላይ መለጠፋቸውን ዛሬ ረፋዱን በቦታው የተገኘው የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ዘጋቢ ተመልክቷል።

በሱቆቹ አካባቢ የአዲስ አበባ ፖሊስ የደንብ ልብስ የለበሱ የጸጥታ ኃይሎች በርከት ብለው የሚታዩ ሲሆን የተወሰኑቱ በወንበሮች ላይ ተቀምጠው ጥበቃ ሲያደርጉ ተስተውለዋል።

ፖሊስ የተወሰኑ ሱቆች የሚገኙባቸውን እና ቀደም ሲል እግረኞችና ተሽከርካሪዎች ይተላለፉባቸው የነበሩ መጋቢ መንገዶችን ለተጠቃሚዎች ዝግ አድርጓል። ከተዘጉት መንገዶች መካከል ከጋንዲ ሆስፒታል ወደ ብሔራዊ ትያትር የሚወስደው ማቋረጫ እና ከኢትዮጵያ ሆቴል ጎን የሚገኝ፣ ተሽከርካሪዎች በአንድ አቅጣጫ ብቻ የሚተላለፉበት መስመር ይገኙበታል።

በሱቆቹ አቅራቢያ ሸቀጦችን በመቸርቸር የሚተዳደር አንድ ወጣት ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” እንደተናገረው፤ ሱቆቹ የተዘጉት ትላንት ሰኞ አስር ሰዓት ገደማ በአካባቢው ድንገተኛ ፍተሻ ከተደረገ በኋላ ነው። በአካባቢው ባለ ሆቴል እና ፋርማሲ የሚሰሩ ሁለት ግለሰቦች ይህንኑ የወጣቱን ገለጻ አረጋግጠዋል።

የትላንትናው ድንገተኛ ፍተሻ በሚደረግበት ወቅት የፊት እና የጉልበት መከላከያ ያደረጉ የፌደራል ፖሊስ አባላት በአካባቢው ጥብቅ የጸጥታ ቁጥጥር ሲያደርጉ እንደነበር ወጣቱ ገልጿል። በፍተሻው ጋንዲ ሆስፒታል አካባቢ በነበሩ ሱቆች የተቀመጡ የውጭ ሀገር ገንዘቦች በጸጥታ ሃይሎች እንደተወሰዱ መስማቱንም አክሏል። 

ዛሬ የታሸጉት ሱቆች

ነባሮቹ የ10፣ የ50 እና የ100 ብር መገበያያዎች መቀየራቸውን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በትላንትናው ዕለት በሰጡት ማብራሪያ፤ ከፋይናንስ ተቋማት ውጪ የተከማቹ ገንዘቦችን ለመያዝ በየቦታው ድንገተኛ ፍተሻ እንደሚደረግ አስታውቀው ነበር። ድንገተኛ ፍተሻዎቹ የሚደረጉት “በሚጠረጠሩ ቦታዎች” ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ አሰሳ የግለሰብ ቤትም ይሁን የንግድ ቦታ ሊካተት እንደሚችል ጠቁመዋል።

“የሕግ አስከባሪ ተቋማት አንደኛ ጥቁር ገበያ፤ ሁለተኛ አየር መንገድ ከዛሬ ጀምሮ ባስቀመጥንው አቅጣጫ መሠረት እያንዳንዷ ሻንጣ ማስወጣት፤ ማስገባት በማይችል በአየር መንገድ ጥብቅ ሴኪዩሪቲ ይደረጋል። በድንበር አካባቢዎች በተለይ ከጅቡቲ ሶማሌ ሱዳን ከፍተኛ ገንዘብ እንዳለ ይታወቃል። በነዳጅ ቦቴም ይሁን በተለያየ መንገድ ገንዘቡ እንዳይገባ የሕግ አስከባሪ ተቋማት በወጣው ዕቅድ መሠረት ከመነሻው ጀምሮ ሰፊ ጥበቃ ያደርጋሉ። እኛ ገንዘቡን አንፈልገውም። ወርሰው የሕግ አስከባሪ ተቋማት ይጠናከሩበታል” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስጠንቅቀዋል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ባለፉት ሁለት ተኩል ዓመታት የአሸባሪው የወንበዴዎች ቡድን ህወሓት አባላትና ደጋፊዎች ብር ይቀየራል በሚል እሳቤ ከሕዝብ የዘረፉትን ወደ ዶላር ሲቀይሩ እንደነበር ይታወቃል። የብር ኖቶች መቀየራቸውን ተከትሎ ይህንን ሥራቸውን በሥፋት እንደሚያከናውኑት በመረዳት በተለይ በዳያስፖራ የሚገኘው ወገን ለጥቂት ብሮች ልዩነት በሚል በጥቁር ገበያ የሚልከው ገንዘብ መልሶ አገር ለማፍረስ ተግባር እንደሚውል በመገንዘብ ከዚህ ሥራ እንዲታቀብ አገራዊ ጥሪ ቀርቧል።

ጭንቅላቱ የደረቀውና መቀሌ በየሆቴሉ የመሸገው ራሱን ህወሓት እያለ የሚጠራው የወንበዴዎች ጥርቅም በቅርብ ጊዜ ውስጥ ኪሱም እንደሚደርቅ ይጠበቃል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: News, Right Column Tagged With: black market, new currency, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule