• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“በጥቁር ገበያ” ምንዛሪ የተጠረጠሩ ሱቆች ታሸጉ

September 15, 2020 11:36 am by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ መንግስት አሁን በአገልግሎት ላይ የሚገኙትን የብር የገንዘብ አይነቶች እንዲሚቀይር በትላንትናው ዕለት ማስታወቁን ተከትሎ የ“ጥቁር ገበያ”ውን ለመቆጣጠር እርምጃ መውሰድ ተጀመረ።

በአዲስ አበባ ከባንክ ውጭ የሚደረጉ የውጭ ሀገር ገንዘብ ግብይቶችን በድብቅ ያከናውናሉ ከተባሉ ሱቆች መካከል የተወሰኑት ከትላንት ጀምሮ እንዲታሸጉ ተደርገዋል። 

የእርምጃው ሰለባ የሆኑት በይፋ ከሚታወቁባቸው አገልግሎቶች ባሻገር የውጭ ሀገር ገንዘቦች ምንዛሬን በተደራቢነት የሚሰጡ ሱቆች ናቸው። በኢትዮጵያ ሆቴል እና ጋንዲ ሆስፒታል አካባቢ የሚገኙት እነዚህ ሱቆች “ታሽጓል” የሚል ጽሁፍ እና ማህተም የሰፈረባቸው ወረቀቶች በየበሮቻቸው ላይ መለጠፋቸውን ዛሬ ረፋዱን በቦታው የተገኘው የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ዘጋቢ ተመልክቷል።

በሱቆቹ አካባቢ የአዲስ አበባ ፖሊስ የደንብ ልብስ የለበሱ የጸጥታ ኃይሎች በርከት ብለው የሚታዩ ሲሆን የተወሰኑቱ በወንበሮች ላይ ተቀምጠው ጥበቃ ሲያደርጉ ተስተውለዋል።

ፖሊስ የተወሰኑ ሱቆች የሚገኙባቸውን እና ቀደም ሲል እግረኞችና ተሽከርካሪዎች ይተላለፉባቸው የነበሩ መጋቢ መንገዶችን ለተጠቃሚዎች ዝግ አድርጓል። ከተዘጉት መንገዶች መካከል ከጋንዲ ሆስፒታል ወደ ብሔራዊ ትያትር የሚወስደው ማቋረጫ እና ከኢትዮጵያ ሆቴል ጎን የሚገኝ፣ ተሽከርካሪዎች በአንድ አቅጣጫ ብቻ የሚተላለፉበት መስመር ይገኙበታል።

በሱቆቹ አቅራቢያ ሸቀጦችን በመቸርቸር የሚተዳደር አንድ ወጣት ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” እንደተናገረው፤ ሱቆቹ የተዘጉት ትላንት ሰኞ አስር ሰዓት ገደማ በአካባቢው ድንገተኛ ፍተሻ ከተደረገ በኋላ ነው። በአካባቢው ባለ ሆቴል እና ፋርማሲ የሚሰሩ ሁለት ግለሰቦች ይህንኑ የወጣቱን ገለጻ አረጋግጠዋል።

የትላንትናው ድንገተኛ ፍተሻ በሚደረግበት ወቅት የፊት እና የጉልበት መከላከያ ያደረጉ የፌደራል ፖሊስ አባላት በአካባቢው ጥብቅ የጸጥታ ቁጥጥር ሲያደርጉ እንደነበር ወጣቱ ገልጿል። በፍተሻው ጋንዲ ሆስፒታል አካባቢ በነበሩ ሱቆች የተቀመጡ የውጭ ሀገር ገንዘቦች በጸጥታ ሃይሎች እንደተወሰዱ መስማቱንም አክሏል። 

ዛሬ የታሸጉት ሱቆች

ነባሮቹ የ10፣ የ50 እና የ100 ብር መገበያያዎች መቀየራቸውን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በትላንትናው ዕለት በሰጡት ማብራሪያ፤ ከፋይናንስ ተቋማት ውጪ የተከማቹ ገንዘቦችን ለመያዝ በየቦታው ድንገተኛ ፍተሻ እንደሚደረግ አስታውቀው ነበር። ድንገተኛ ፍተሻዎቹ የሚደረጉት “በሚጠረጠሩ ቦታዎች” ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ አሰሳ የግለሰብ ቤትም ይሁን የንግድ ቦታ ሊካተት እንደሚችል ጠቁመዋል።

“የሕግ አስከባሪ ተቋማት አንደኛ ጥቁር ገበያ፤ ሁለተኛ አየር መንገድ ከዛሬ ጀምሮ ባስቀመጥንው አቅጣጫ መሠረት እያንዳንዷ ሻንጣ ማስወጣት፤ ማስገባት በማይችል በአየር መንገድ ጥብቅ ሴኪዩሪቲ ይደረጋል። በድንበር አካባቢዎች በተለይ ከጅቡቲ ሶማሌ ሱዳን ከፍተኛ ገንዘብ እንዳለ ይታወቃል። በነዳጅ ቦቴም ይሁን በተለያየ መንገድ ገንዘቡ እንዳይገባ የሕግ አስከባሪ ተቋማት በወጣው ዕቅድ መሠረት ከመነሻው ጀምሮ ሰፊ ጥበቃ ያደርጋሉ። እኛ ገንዘቡን አንፈልገውም። ወርሰው የሕግ አስከባሪ ተቋማት ይጠናከሩበታል” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስጠንቅቀዋል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ባለፉት ሁለት ተኩል ዓመታት የአሸባሪው የወንበዴዎች ቡድን ህወሓት አባላትና ደጋፊዎች ብር ይቀየራል በሚል እሳቤ ከሕዝብ የዘረፉትን ወደ ዶላር ሲቀይሩ እንደነበር ይታወቃል። የብር ኖቶች መቀየራቸውን ተከትሎ ይህንን ሥራቸውን በሥፋት እንደሚያከናውኑት በመረዳት በተለይ በዳያስፖራ የሚገኘው ወገን ለጥቂት ብሮች ልዩነት በሚል በጥቁር ገበያ የሚልከው ገንዘብ መልሶ አገር ለማፍረስ ተግባር እንደሚውል በመገንዘብ ከዚህ ሥራ እንዲታቀብ አገራዊ ጥሪ ቀርቧል።

ጭንቅላቱ የደረቀውና መቀሌ በየሆቴሉ የመሸገው ራሱን ህወሓት እያለ የሚጠራው የወንበዴዎች ጥርቅም በቅርብ ጊዜ ውስጥ ኪሱም እንደሚደርቅ ይጠበቃል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: black market, new currency, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule