• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት

February 17, 2023 12:35 pm by Editor 2 Comments

የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳደር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በክልሉ ታጥቆ ለሚብቀሳቀሰው የኦነግ ሸኔ ቡድን የሰላም እና የእርቅ ጥሪ አቀረቡ። ጨፌ ኦሮሚያ በዛሬው እለት መደበኛ ስብሰባውን እያደረገ ይገኛል። አቶ ሽመልስ አብዲሳ መንግሥት የክልሉን ሰላም ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል።

ጨፌ ኦሮሚያ በዛሬው እለት መደበኛ ስብሰባውን ማድረግ የጀመረ ሲሆን፣ የክልሉ ርእሰ መስተዳደር አቶ ሽመልስ አብዲሳ የክልሉ መንግሥት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል።

በዚህም አቶ ሽመልስ፣ “ሰላም ለሁሉም ነገር መሰረት ነው፣ ሰላም በሌለበት ስለ ልማት ማሰብ አይቻልም” ያሉ ሲሆን፣ የኦሮሚያ ክልል መንግሥት የክልሉን ሰላም ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል።

ርእሰ መስተዳደር አቶ ሽመልስ በንግግራቸው፣ “በዚህ በተከበረው ጨፌው ፊት በክልላችን ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ አካላት ማለትም ኦነግ ሸኔ በእርቅ ወደ ሰላማዊ መንገድ ተመልሶ እንዲገባ በክብር ጥሪ አቀርባለሁ” ብለዋል።

አቶ ሽመልስ አክለውም መንግሥት ለሰላም ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ኦነግ ሸኔ እና መሰል የጥፋት ሃይሎች ትክክለኛውን መንገድ እንዲይዙ እየሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል።

በክልሉ ሰላም እንዲሰፍን እስከ ህይወት መሰዋእትነት እየከፈሉ ላሉ የጸጥታ አካላትም ምስጋናቸውን ያቀረቡት ርእሰ መስተዳደሩ፣ ለክልሉ ሰላም የሰሩት ስራ ሁሌም በታሪክ ስዘከር ይኖራል ብለዋል።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ2013 ግንቦት ወር ላይ በኦሮሚያ ክልል ታጥቆ የሚንቀሳቀሰውን “ኦነግ ሸኔ” ቡድንን በሽብርተኝትነት መፈረጁ ይታወሳል።

በተለምዶ “ሸኔ” ተብሎ የሚጠራውና በኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀሰዉ ቡድን በርካቶችን ህይወት እንዲጠፋ፣ እንዲፈናቀሉ እና ንብረት እንዲያወድም ከማደረግ በዘለለ የሀገር መከላከያ ሰራዊትን ማጥቃቱንም መንግሥት በወቅቱ ገልጸዋል።

“ሸኔ” በ2013 ዓ.ም ብቻ በኦሮሚያ ክልል ውስጥ 463 ሰዎች ላይ አደጋ ማድረሱ የሚታወስ ሲሆን፣ ይህ ጥቃት እየተባባሰ መምጣቱም ሪፖርቶች ያመለክታሉ።

ቡድኑ ባሳለፍነው ጥር ወር በምስራቅ ወለጋ በፈጸመው ጥቃት ከ50 በላይ ንጹሃን ዜጎችን መግደሉንም የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ባወጣው ሪፖርት አመላክቷል። (AlAin)

ይህ የሽመልስ አብዲሣ ጥሪ ሕገ ወጥ ብቻ ሳይሆን በሕግም የሚያስጠይቅ ነው የሚሉ ድምፆች እየተሰሙ ነው። በክልል ደረጃ በይፋ ይህንን መሰል ጥሪ ማቅረብ የፖለቲካ ዓላማ ከሌለው ወይም በሰላም ሽፋን እንዳይገለጥ የተፈለገ ምሥጢር ከሌለ በስተቀር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትን (የፓርላማውን) ሥልጣን የሚጋፋ ነውና ፓርላማው በግልጽ ጥያቄ ሊያቀርብ ይገባል። 

ሌሎች አስተያየት ሰጪዎች ትህነግም አሸባሪ ተብሎ የሰላም ስምምነት ፈርሟል በማለት ለሚያነሱት ያኛው ቢያንስ በፌዴራል ደረጃ የተከናወነና በሌሎችም አገራት ሲሠራበት የቆየ ልምድ ነው የሚል የማጣፊያ አስተያየት ሲሰጥ ይደመጣል። ወደ ሸኔ ስንመጣ ግን ኦሮሚያ እንደ አገር፤ ጨፌው እንደ ፌደራል ፓርላማ፤ ሽመልስም እንደ ርዕሰ ብሔር ካልተቆጠሩ በስተቀር በይፋ የፓርላማውን ሥልጣን አልፎ ይህንን መሰሉ ውሳኔ ማሳለፍ ክልላዊ ዕብጠት ነው።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News, Politics Tagged With: ethiopian terrorists, olf shanee, olf shine, operation dismantle tplf, shemelis abdissa, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. ይስሃቅ አበበ says

    March 4, 2023 12:51 pm at 12:51 pm

    ሸሌ ለሸኔ ያቀረበው ድራማ !

    Reply
  2. ይስሃቅ አበበ says

    March 4, 2023 12:58 pm at 12:58 pm

    ሸሌ ለሸኔ ያቀረበው አስቂኝ አሳፋሪ ቀሽም ድራማ ! የሚያበሳጭ !! በእርግጠኝነት እግዚአብሔር የንፁሃንን ደም ቁማርተኛውን…ይፋረዳቸዋል ! ሸኔ ሸሌ ሸሌ ሸኔ !!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm
  • “ሙሽራው እስኪመጣ የምትቆይ ቤተክርስቲያን እናድርጋት” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ February 15, 2023 03:13 pm
  • በመዝገበ ቃላት የችጋር መጠሪያ የነበረችው ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ስንዴ ወደ ውጭ ላከች February 13, 2023 03:28 am
  • ውዝግቡን በሐዋሪያት መንገድ ለመፍታት ስምምነት ላይ ተደርሷል February 10, 2023 09:06 am
  • የሚከተልህ ሁሉ ወዳጅህ አይደለም – መልዕክት “ለመንፈሳዊው ቄሮ” መሪ ዘመድኩን በቀለ! February 10, 2023 12:48 am
  • በሰማዕትነት ጥሪ ቤተመንግሥቱን ባቋራጭ መቆጣጠር February 9, 2023 01:25 pm
  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule