• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት

February 17, 2023 12:35 pm by Editor 2 Comments

የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳደር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በክልሉ ታጥቆ ለሚብቀሳቀሰው የኦነግ ሸኔ ቡድን የሰላም እና የእርቅ ጥሪ አቀረቡ። ጨፌ ኦሮሚያ በዛሬው እለት መደበኛ ስብሰባውን እያደረገ ይገኛል። አቶ ሽመልስ አብዲሳ መንግሥት የክልሉን ሰላም ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል።

ጨፌ ኦሮሚያ በዛሬው እለት መደበኛ ስብሰባውን ማድረግ የጀመረ ሲሆን፣ የክልሉ ርእሰ መስተዳደር አቶ ሽመልስ አብዲሳ የክልሉ መንግሥት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል።

በዚህም አቶ ሽመልስ፣ “ሰላም ለሁሉም ነገር መሰረት ነው፣ ሰላም በሌለበት ስለ ልማት ማሰብ አይቻልም” ያሉ ሲሆን፣ የኦሮሚያ ክልል መንግሥት የክልሉን ሰላም ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል።

ርእሰ መስተዳደር አቶ ሽመልስ በንግግራቸው፣ “በዚህ በተከበረው ጨፌው ፊት በክልላችን ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ አካላት ማለትም ኦነግ ሸኔ በእርቅ ወደ ሰላማዊ መንገድ ተመልሶ እንዲገባ በክብር ጥሪ አቀርባለሁ” ብለዋል።

አቶ ሽመልስ አክለውም መንግሥት ለሰላም ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ኦነግ ሸኔ እና መሰል የጥፋት ሃይሎች ትክክለኛውን መንገድ እንዲይዙ እየሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል።

በክልሉ ሰላም እንዲሰፍን እስከ ህይወት መሰዋእትነት እየከፈሉ ላሉ የጸጥታ አካላትም ምስጋናቸውን ያቀረቡት ርእሰ መስተዳደሩ፣ ለክልሉ ሰላም የሰሩት ስራ ሁሌም በታሪክ ስዘከር ይኖራል ብለዋል።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ2013 ግንቦት ወር ላይ በኦሮሚያ ክልል ታጥቆ የሚንቀሳቀሰውን “ኦነግ ሸኔ” ቡድንን በሽብርተኝትነት መፈረጁ ይታወሳል።

በተለምዶ “ሸኔ” ተብሎ የሚጠራውና በኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀሰዉ ቡድን በርካቶችን ህይወት እንዲጠፋ፣ እንዲፈናቀሉ እና ንብረት እንዲያወድም ከማደረግ በዘለለ የሀገር መከላከያ ሰራዊትን ማጥቃቱንም መንግሥት በወቅቱ ገልጸዋል።

“ሸኔ” በ2013 ዓ.ም ብቻ በኦሮሚያ ክልል ውስጥ 463 ሰዎች ላይ አደጋ ማድረሱ የሚታወስ ሲሆን፣ ይህ ጥቃት እየተባባሰ መምጣቱም ሪፖርቶች ያመለክታሉ።

ቡድኑ ባሳለፍነው ጥር ወር በምስራቅ ወለጋ በፈጸመው ጥቃት ከ50 በላይ ንጹሃን ዜጎችን መግደሉንም የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ባወጣው ሪፖርት አመላክቷል። (AlAin)

ይህ የሽመልስ አብዲሣ ጥሪ ሕገ ወጥ ብቻ ሳይሆን በሕግም የሚያስጠይቅ ነው የሚሉ ድምፆች እየተሰሙ ነው። በክልል ደረጃ በይፋ ይህንን መሰል ጥሪ ማቅረብ የፖለቲካ ዓላማ ከሌለው ወይም በሰላም ሽፋን እንዳይገለጥ የተፈለገ ምሥጢር ከሌለ በስተቀር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትን (የፓርላማውን) ሥልጣን የሚጋፋ ነውና ፓርላማው በግልጽ ጥያቄ ሊያቀርብ ይገባል። 

ሌሎች አስተያየት ሰጪዎች ትህነግም አሸባሪ ተብሎ የሰላም ስምምነት ፈርሟል በማለት ለሚያነሱት ያኛው ቢያንስ በፌዴራል ደረጃ የተከናወነና በሌሎችም አገራት ሲሠራበት የቆየ ልምድ ነው የሚል የማጣፊያ አስተያየት ሲሰጥ ይደመጣል። ወደ ሸኔ ስንመጣ ግን ኦሮሚያ እንደ አገር፤ ጨፌው እንደ ፌደራል ፓርላማ፤ ሽመልስም እንደ ርዕሰ ብሔር ካልተቆጠሩ በስተቀር በይፋ የፓርላማውን ሥልጣን አልፎ ይህንን መሰሉ ውሳኔ ማሳለፍ ክልላዊ ዕብጠት ነው።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News, Politics Tagged With: ethiopian terrorists, olf shanee, olf shine, operation dismantle tplf, shemelis abdissa, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. ይስሃቅ አበበ says

    March 4, 2023 12:51 pm at 12:51 pm

    ሸሌ ለሸኔ ያቀረበው ድራማ !

    Reply
  2. ይስሃቅ አበበ says

    March 4, 2023 12:58 pm at 12:58 pm

    ሸሌ ለሸኔ ያቀረበው አስቂኝ አሳፋሪ ቀሽም ድራማ ! የሚያበሳጭ !! በእርግጠኝነት እግዚአብሔር የንፁሃንን ደም ቁማርተኛውን…ይፋረዳቸዋል ! ሸኔ ሸሌ ሸሌ ሸኔ !!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule