• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“እርግጠኛ ሆኜ የምነግራችሁ መንግሥት ኮሮጆ አይሰርቅም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ

April 1, 2021 01:09 am by Editor 1 Comment

መንግሥት በምርጫ ዙሪያ በመቶ ሺሕ የሚቆጠር ካድሬ እስካለፈው እሑድ ድረስ ማሠልጠኑን፣ ማክሰኞ መጋቢት 21 ቀን 2013 ዓ.ም. በተካሄደው የአዲስ ወግ ውይይት ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ተናግረው፣ ዘንድሮ ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው አገራዊ ምርጫ ፓርቲያቸው ብልፅግና ከተሸነፈ ሥልጣን ለማስረከብ ዝግጁ መሆኑን አስታወቁ።

“እንደ ብልፅግና ፓርቲ ከተሸነፍን ሥልጣን ለማስረከብ ተዘጋጅተናል። ይህንን ካደረግን ደግሞ ከምርጫ በኋላ ሰላም የማይኖርበት ምክንያት አይኖርም። አሁን ሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት በመቶ ሺሕ የሚቆጠር ካድሬ እስካለፈው ቅዳሜና እሑድ ድረስ ሥልጠና ላይ ነበር። ዋናው መልዕክት ኢትዮጵያ አሸናፊ መሆን አለባት ነው” ብለዋል።

ኢትዮጵያ አሸናፊ የምትሆነው ሽንፈት ሲኖር በማመሥገንና መልካም በመመኘት ሥልጣን መስጠት ከተቻለ መሆኑን ገልጸው፣ “በታሪካችን ሆኖ ስለማያውቅ ለእኛም ጥሩ ነው አገርም ይቀጥላል። ብናሸንፍ ደግሞ ሰላማዊ ሆኖ ሰዎች ተሸንፈው ከሆነ እንኳን፣ በሒደቱ ጥርጣሬ በልቦናቸው ያላደረ ከሆነ ጠቃሚ ነው የሚል ውይይት አድርገናል” ሲሉ በካድሬዎች ውይይት ላይ የነበረውን ሐሳብ ጠቁመዋል።

ከዚህ ባለፈ እንደ ምርጫ 97 የምርጫ ኮሮጆ በመስረቅ የሚፈጠር ቀውስ እንደማይኖር፣ እንዲያውም እሳቸውን የሚያስፈራቸው ቅጥረኞች ወይም የተገዙ ሰዎች ራሳቸውን ከሕዝብ ጋር አመሳስለው በአንዳንድ ቦታዎች መራጭንና አስመራጭን በማጥቃት ጥፋት እንዳያስከትሉ እንደሆነ ተናግረዋል።

“በምርጫ 97 የገጠመንን ችግር ከአሁኑ ጋር እንዳታመሳክሩት። በምርጫ 97 ኮሮጆ የሚሰርቅ መንግሥት፣ ኮሮጆ የሚሰርቅ ፖሊስ፣ ኮሮጆ የሚሰርቅ አስፈጻሚና ድምፄ አይሰረቅብኝ የሚል ሕዝብ ነው የተጋጨው። እርግጠኛ ሆኜ የምነግራችሁ መንግሥት ኮሮጆ አይሰርቅም” ሲሉ ቃል ገብተዋል።

አሁን ችግር የሚያጋጥመው ኮሮጆ በመሰረቁ ብቻ ሳይሆን፣ ወጥቶ ለመምረጥ ዜጎች የደኅንነት ስሜት እንዳይሰማቸው ለማድረግ የሚፈልጉ፣ የተገዙ፣ በሽፍትነት የሚሠሩ፣ ዘር እየመረጡ የሚገድሉ፣ የኢትዮጵያን አንድነትና ህልውና የማይፈልጉ ኃይሎች መኖራቸው እንደሆነ ጠቁመው፣ “ነገር ግን ታጥቀውና ዩኒፎርም ለብሰው ስለማናገኛቸው፣ ተመሳስለው ስለሆነ የሚገኙት ጥፋት ሊያደርሱ ይችላሉ። እነዚህን መከላከል የምንችለው እያንዳንዱ ዜጋ ኃላፊነት ሲወስድ ብቻ ነው። እያንዳንዱ ዜጋ መረጃ ከሰጠ፣ ሁኔታዎችን ለሚመለከተው አካል ካሳወቀ ከወዲሁ እየገመትን፣ እየለየንና እያወቅን ከሄድን የጥፋት ኃይሎችና ቅጥረኞች ጥፋት እንዳያመጡ ማድረግ ይቻላል” ብለዋል።    

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምርጫውን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ ያወሱት፣ በጣም ብዙ ኃይሎች ቋምጠው የሚጠብቁት ይህንን ምርጫ እንደሆነ ነው። በዚህ ምርጫ አማካይነት ኢትዮጵያ ውስጥ ችግር መፍጠር ይቻላል በማለት ብዙ ሀብት የሚያፈሱ አገሮች እንዳሉ፣ ይህንን ችግር የሚገነዘቡና የሚያዩ ብዙ ሰዎች ምርጫው አያስፈልግም እንደሚሉ፣ ምርጫው ቅንጦት ነው የሚሉ ሰዎች ዝም ብለው ሳይሆን መከራከሪያቸው ችግሩን በማየት፣ የኢትዮጵያን ቀጣይነትና ህልውና ቅድሚያ በመስጠት ስለሆነ እንደሚጨነቁ አስረድተዋል።

ከዚህ ምርጫ ምንድነው የምናገኘው? ብዙ ተዋንያን ሊያጠፏት የሚፈልጓትን አገር በውስጥ ሳንግባባ ምርጫ ብለን ከነበረው ሁኔታ የዘቀጠ ነገር እንዳይፈጠር በማለት የሚሠጉ አሉ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ሥጋቱን አጉልተው ምርጫው ባይኖር እንደሚፈልጉ እንደሚናገሩ አስታውቀዋል። “በሌላ በኩል ደግሞ ምርጫው ባለመደረጉ ለረብሻና ለብጥብጥ እንደ ነጥብ ለመጠቀም የሚፈልጉ ኃይሎች ስላሉ፣ የመንግሥትን ቅቡልነት የሚያሳጡና ሰብሰብ ብለን ወደ ልማት ወደ ብልፅግና እንዳናተኩር የሚያደርጉ  ስላሉ ምርጫ ማድረግ አስፈላጊ የሚሆንባቸው ሁኔታዎች አሉ” ብለዋል።

ምርጫው መካሄድ አለበት ወይም የለበትም ብሎ የሚወስነው አካል ለሚመጣው ውጤት ኃላፊነት የሚወስድ መሆኑን ገልጸው፣ ‹‹ምርጫ አማራጭ መሆኑ አያጠራጥርም። አሁን በመድረኩ ወንድሞቼና እህቴ እንዳነሳችሁት እያንዳንዱ ዜጋ ሰላም የሁሉም ነገር መሠረት መሆኑን አውቆ፣ ጊዜ ስላለም ማንን እንደሚመርጥ እያሰበ ቆይቶ ከመረጠ በኋላ ድንጋይ የሚወረወር ከሆነ ግን በጋራ መቆም አለበት። በዚህ በሚጠበቀው አገራዊ ምርጫ በከተማ ውስጥ ድንጋይ የሚወረውርና ውጤቱን ባለመቀበል የሚደረግ ተቃውሞ ይኖራል ብዬ አልጠብቅም። ሥጋቱ ግን የተገዙ አካላት ቀውስ እንዳይፈጥሩ ነው፤›› ሲሉ አስረድተዋል።

“መጪው ምርጫ ዕድልና ችግሮችን ይዟል፤” በማለት ሁለቱንም ተገንዝቦ ለመምረጥ የሚነሳና የሚመርጠውን አካል ሕጋዊነት ያረጋገጠ ማኅበረሰብ እንዲፈጠር፣ ይህን መሰል ውይይቶች እንደሚያስፈልጉ አሳስበዋል።

የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ኃላፊዎችና ልሂቃን የተሳተፉበት የአዲስ ወግ ውይይት “ሰላምና ደኅንነት በምርጫ ወቅት” በሚል ርዕስ በወቅታዊ ጭብጥ የተመረጠ ሲሆን፣ በሦስት ክፍለ ጊዜያት በተለያዩ ርዕሶች የሚካሄድ ነው።

ማክሰኞ መጋቢት 21 ቀን 2013 ዓ.ም. ማለዳ የተካሄደው የመጀመርያው ክፍል የአዲስ ወግ ውይይት በሰላማዊ ምርጫ መገለጫዎችና መሥፈርቶች ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ ከቀትር በኋላ የተካሄደው ክፍል በምርጫ ወቅት ሰላምን ለማስፈን ሰላምን የሚያንፁ አገር በቀልና ዘመናዊ ተቋማት ሚና ተዳሰዋል። ባለ ሦስት ክፍሉ የአዲስ ወግ ፍፃሜ ረቡዕ መጋቢት 22 ቀን 2013 ዓ.ም. ሐሰተኛ መረጃ በሰላማዊ ምርጫ ላይ ያለውን አሉታዊ ተፅዕኖ መግታት በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ እንደሚካሄድ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያስረዳል። (ሪፖርተር)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: election 2013, election 2021

Reader Interactions

Comments

  1. ነፃ ሕዝብ says

    April 1, 2021 06:16 am at 6:16 am

    ይሄ ነፍሰ_ገዳይ ዘረኛና የግራኝ አህመድ የጥፋት ውላጅ በማላይ ንግግሮቹ አያሌ ኢትዮጵያውያንን በማጭበርበር ሕዝብ እያሳረደ ይገኛል ፥ አብይ አህመድ አሊ ከእንግዲህን ወዲያ ኢትዮጵያን መምራት ሳይሆን በዓለም ወንጀለኛ ፍ/ቤት (ICC) ቀርቦ መጠየቅ እንጂ ለዚያች ሀገር የመምራት ብቃትም ሆነ ሞራል የለውም ፥ ከእንግዲህን ወዲያ እርሱ ይኖራል ወይ እኛ ጨርሰን እናልቃለን ፡፡

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule