• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“እርግጠኛ ሆኜ የምነግራችሁ መንግሥት ኮሮጆ አይሰርቅም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ

April 1, 2021 01:09 am by Editor 1 Comment

መንግሥት በምርጫ ዙሪያ በመቶ ሺሕ የሚቆጠር ካድሬ እስካለፈው እሑድ ድረስ ማሠልጠኑን፣ ማክሰኞ መጋቢት 21 ቀን 2013 ዓ.ም. በተካሄደው የአዲስ ወግ ውይይት ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ተናግረው፣ ዘንድሮ ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው አገራዊ ምርጫ ፓርቲያቸው ብልፅግና ከተሸነፈ ሥልጣን ለማስረከብ ዝግጁ መሆኑን አስታወቁ።

“እንደ ብልፅግና ፓርቲ ከተሸነፍን ሥልጣን ለማስረከብ ተዘጋጅተናል። ይህንን ካደረግን ደግሞ ከምርጫ በኋላ ሰላም የማይኖርበት ምክንያት አይኖርም። አሁን ሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት በመቶ ሺሕ የሚቆጠር ካድሬ እስካለፈው ቅዳሜና እሑድ ድረስ ሥልጠና ላይ ነበር። ዋናው መልዕክት ኢትዮጵያ አሸናፊ መሆን አለባት ነው” ብለዋል።

ኢትዮጵያ አሸናፊ የምትሆነው ሽንፈት ሲኖር በማመሥገንና መልካም በመመኘት ሥልጣን መስጠት ከተቻለ መሆኑን ገልጸው፣ “በታሪካችን ሆኖ ስለማያውቅ ለእኛም ጥሩ ነው አገርም ይቀጥላል። ብናሸንፍ ደግሞ ሰላማዊ ሆኖ ሰዎች ተሸንፈው ከሆነ እንኳን፣ በሒደቱ ጥርጣሬ በልቦናቸው ያላደረ ከሆነ ጠቃሚ ነው የሚል ውይይት አድርገናል” ሲሉ በካድሬዎች ውይይት ላይ የነበረውን ሐሳብ ጠቁመዋል።

ከዚህ ባለፈ እንደ ምርጫ 97 የምርጫ ኮሮጆ በመስረቅ የሚፈጠር ቀውስ እንደማይኖር፣ እንዲያውም እሳቸውን የሚያስፈራቸው ቅጥረኞች ወይም የተገዙ ሰዎች ራሳቸውን ከሕዝብ ጋር አመሳስለው በአንዳንድ ቦታዎች መራጭንና አስመራጭን በማጥቃት ጥፋት እንዳያስከትሉ እንደሆነ ተናግረዋል።

“በምርጫ 97 የገጠመንን ችግር ከአሁኑ ጋር እንዳታመሳክሩት። በምርጫ 97 ኮሮጆ የሚሰርቅ መንግሥት፣ ኮሮጆ የሚሰርቅ ፖሊስ፣ ኮሮጆ የሚሰርቅ አስፈጻሚና ድምፄ አይሰረቅብኝ የሚል ሕዝብ ነው የተጋጨው። እርግጠኛ ሆኜ የምነግራችሁ መንግሥት ኮሮጆ አይሰርቅም” ሲሉ ቃል ገብተዋል።

አሁን ችግር የሚያጋጥመው ኮሮጆ በመሰረቁ ብቻ ሳይሆን፣ ወጥቶ ለመምረጥ ዜጎች የደኅንነት ስሜት እንዳይሰማቸው ለማድረግ የሚፈልጉ፣ የተገዙ፣ በሽፍትነት የሚሠሩ፣ ዘር እየመረጡ የሚገድሉ፣ የኢትዮጵያን አንድነትና ህልውና የማይፈልጉ ኃይሎች መኖራቸው እንደሆነ ጠቁመው፣ “ነገር ግን ታጥቀውና ዩኒፎርም ለብሰው ስለማናገኛቸው፣ ተመሳስለው ስለሆነ የሚገኙት ጥፋት ሊያደርሱ ይችላሉ። እነዚህን መከላከል የምንችለው እያንዳንዱ ዜጋ ኃላፊነት ሲወስድ ብቻ ነው። እያንዳንዱ ዜጋ መረጃ ከሰጠ፣ ሁኔታዎችን ለሚመለከተው አካል ካሳወቀ ከወዲሁ እየገመትን፣ እየለየንና እያወቅን ከሄድን የጥፋት ኃይሎችና ቅጥረኞች ጥፋት እንዳያመጡ ማድረግ ይቻላል” ብለዋል።    

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምርጫውን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ ያወሱት፣ በጣም ብዙ ኃይሎች ቋምጠው የሚጠብቁት ይህንን ምርጫ እንደሆነ ነው። በዚህ ምርጫ አማካይነት ኢትዮጵያ ውስጥ ችግር መፍጠር ይቻላል በማለት ብዙ ሀብት የሚያፈሱ አገሮች እንዳሉ፣ ይህንን ችግር የሚገነዘቡና የሚያዩ ብዙ ሰዎች ምርጫው አያስፈልግም እንደሚሉ፣ ምርጫው ቅንጦት ነው የሚሉ ሰዎች ዝም ብለው ሳይሆን መከራከሪያቸው ችግሩን በማየት፣ የኢትዮጵያን ቀጣይነትና ህልውና ቅድሚያ በመስጠት ስለሆነ እንደሚጨነቁ አስረድተዋል።

ከዚህ ምርጫ ምንድነው የምናገኘው? ብዙ ተዋንያን ሊያጠፏት የሚፈልጓትን አገር በውስጥ ሳንግባባ ምርጫ ብለን ከነበረው ሁኔታ የዘቀጠ ነገር እንዳይፈጠር በማለት የሚሠጉ አሉ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ሥጋቱን አጉልተው ምርጫው ባይኖር እንደሚፈልጉ እንደሚናገሩ አስታውቀዋል። “በሌላ በኩል ደግሞ ምርጫው ባለመደረጉ ለረብሻና ለብጥብጥ እንደ ነጥብ ለመጠቀም የሚፈልጉ ኃይሎች ስላሉ፣ የመንግሥትን ቅቡልነት የሚያሳጡና ሰብሰብ ብለን ወደ ልማት ወደ ብልፅግና እንዳናተኩር የሚያደርጉ  ስላሉ ምርጫ ማድረግ አስፈላጊ የሚሆንባቸው ሁኔታዎች አሉ” ብለዋል።

ምርጫው መካሄድ አለበት ወይም የለበትም ብሎ የሚወስነው አካል ለሚመጣው ውጤት ኃላፊነት የሚወስድ መሆኑን ገልጸው፣ ‹‹ምርጫ አማራጭ መሆኑ አያጠራጥርም። አሁን በመድረኩ ወንድሞቼና እህቴ እንዳነሳችሁት እያንዳንዱ ዜጋ ሰላም የሁሉም ነገር መሠረት መሆኑን አውቆ፣ ጊዜ ስላለም ማንን እንደሚመርጥ እያሰበ ቆይቶ ከመረጠ በኋላ ድንጋይ የሚወረወር ከሆነ ግን በጋራ መቆም አለበት። በዚህ በሚጠበቀው አገራዊ ምርጫ በከተማ ውስጥ ድንጋይ የሚወረውርና ውጤቱን ባለመቀበል የሚደረግ ተቃውሞ ይኖራል ብዬ አልጠብቅም። ሥጋቱ ግን የተገዙ አካላት ቀውስ እንዳይፈጥሩ ነው፤›› ሲሉ አስረድተዋል።

“መጪው ምርጫ ዕድልና ችግሮችን ይዟል፤” በማለት ሁለቱንም ተገንዝቦ ለመምረጥ የሚነሳና የሚመርጠውን አካል ሕጋዊነት ያረጋገጠ ማኅበረሰብ እንዲፈጠር፣ ይህን መሰል ውይይቶች እንደሚያስፈልጉ አሳስበዋል።

የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ኃላፊዎችና ልሂቃን የተሳተፉበት የአዲስ ወግ ውይይት “ሰላምና ደኅንነት በምርጫ ወቅት” በሚል ርዕስ በወቅታዊ ጭብጥ የተመረጠ ሲሆን፣ በሦስት ክፍለ ጊዜያት በተለያዩ ርዕሶች የሚካሄድ ነው።

ማክሰኞ መጋቢት 21 ቀን 2013 ዓ.ም. ማለዳ የተካሄደው የመጀመርያው ክፍል የአዲስ ወግ ውይይት በሰላማዊ ምርጫ መገለጫዎችና መሥፈርቶች ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ ከቀትር በኋላ የተካሄደው ክፍል በምርጫ ወቅት ሰላምን ለማስፈን ሰላምን የሚያንፁ አገር በቀልና ዘመናዊ ተቋማት ሚና ተዳሰዋል። ባለ ሦስት ክፍሉ የአዲስ ወግ ፍፃሜ ረቡዕ መጋቢት 22 ቀን 2013 ዓ.ም. ሐሰተኛ መረጃ በሰላማዊ ምርጫ ላይ ያለውን አሉታዊ ተፅዕኖ መግታት በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ እንደሚካሄድ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያስረዳል። (ሪፖርተር)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: election 2013, election 2021

Reader Interactions

Comments

  1. ነፃ ሕዝብ says

    April 1, 2021 06:16 am at 6:16 am

    ይሄ ነፍሰ_ገዳይ ዘረኛና የግራኝ አህመድ የጥፋት ውላጅ በማላይ ንግግሮቹ አያሌ ኢትዮጵያውያንን በማጭበርበር ሕዝብ እያሳረደ ይገኛል ፥ አብይ አህመድ አሊ ከእንግዲህን ወዲያ ኢትዮጵያን መምራት ሳይሆን በዓለም ወንጀለኛ ፍ/ቤት (ICC) ቀርቦ መጠየቅ እንጂ ለዚያች ሀገር የመምራት ብቃትም ሆነ ሞራል የለውም ፥ ከእንግዲህን ወዲያ እርሱ ይኖራል ወይ እኛ ጨርሰን እናልቃለን ፡፡

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule