• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“እርግጠኛ ሆኜ የምነግራችሁ መንግሥት ኮሮጆ አይሰርቅም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ

April 1, 2021 01:09 am by Editor 1 Comment

መንግሥት በምርጫ ዙሪያ በመቶ ሺሕ የሚቆጠር ካድሬ እስካለፈው እሑድ ድረስ ማሠልጠኑን፣ ማክሰኞ መጋቢት 21 ቀን 2013 ዓ.ም. በተካሄደው የአዲስ ወግ ውይይት ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ተናግረው፣ ዘንድሮ ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው አገራዊ ምርጫ ፓርቲያቸው ብልፅግና ከተሸነፈ ሥልጣን ለማስረከብ ዝግጁ መሆኑን አስታወቁ።

“እንደ ብልፅግና ፓርቲ ከተሸነፍን ሥልጣን ለማስረከብ ተዘጋጅተናል። ይህንን ካደረግን ደግሞ ከምርጫ በኋላ ሰላም የማይኖርበት ምክንያት አይኖርም። አሁን ሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት በመቶ ሺሕ የሚቆጠር ካድሬ እስካለፈው ቅዳሜና እሑድ ድረስ ሥልጠና ላይ ነበር። ዋናው መልዕክት ኢትዮጵያ አሸናፊ መሆን አለባት ነው” ብለዋል።

ኢትዮጵያ አሸናፊ የምትሆነው ሽንፈት ሲኖር በማመሥገንና መልካም በመመኘት ሥልጣን መስጠት ከተቻለ መሆኑን ገልጸው፣ “በታሪካችን ሆኖ ስለማያውቅ ለእኛም ጥሩ ነው አገርም ይቀጥላል። ብናሸንፍ ደግሞ ሰላማዊ ሆኖ ሰዎች ተሸንፈው ከሆነ እንኳን፣ በሒደቱ ጥርጣሬ በልቦናቸው ያላደረ ከሆነ ጠቃሚ ነው የሚል ውይይት አድርገናል” ሲሉ በካድሬዎች ውይይት ላይ የነበረውን ሐሳብ ጠቁመዋል።

ከዚህ ባለፈ እንደ ምርጫ 97 የምርጫ ኮሮጆ በመስረቅ የሚፈጠር ቀውስ እንደማይኖር፣ እንዲያውም እሳቸውን የሚያስፈራቸው ቅጥረኞች ወይም የተገዙ ሰዎች ራሳቸውን ከሕዝብ ጋር አመሳስለው በአንዳንድ ቦታዎች መራጭንና አስመራጭን በማጥቃት ጥፋት እንዳያስከትሉ እንደሆነ ተናግረዋል።

“በምርጫ 97 የገጠመንን ችግር ከአሁኑ ጋር እንዳታመሳክሩት። በምርጫ 97 ኮሮጆ የሚሰርቅ መንግሥት፣ ኮሮጆ የሚሰርቅ ፖሊስ፣ ኮሮጆ የሚሰርቅ አስፈጻሚና ድምፄ አይሰረቅብኝ የሚል ሕዝብ ነው የተጋጨው። እርግጠኛ ሆኜ የምነግራችሁ መንግሥት ኮሮጆ አይሰርቅም” ሲሉ ቃል ገብተዋል።

አሁን ችግር የሚያጋጥመው ኮሮጆ በመሰረቁ ብቻ ሳይሆን፣ ወጥቶ ለመምረጥ ዜጎች የደኅንነት ስሜት እንዳይሰማቸው ለማድረግ የሚፈልጉ፣ የተገዙ፣ በሽፍትነት የሚሠሩ፣ ዘር እየመረጡ የሚገድሉ፣ የኢትዮጵያን አንድነትና ህልውና የማይፈልጉ ኃይሎች መኖራቸው እንደሆነ ጠቁመው፣ “ነገር ግን ታጥቀውና ዩኒፎርም ለብሰው ስለማናገኛቸው፣ ተመሳስለው ስለሆነ የሚገኙት ጥፋት ሊያደርሱ ይችላሉ። እነዚህን መከላከል የምንችለው እያንዳንዱ ዜጋ ኃላፊነት ሲወስድ ብቻ ነው። እያንዳንዱ ዜጋ መረጃ ከሰጠ፣ ሁኔታዎችን ለሚመለከተው አካል ካሳወቀ ከወዲሁ እየገመትን፣ እየለየንና እያወቅን ከሄድን የጥፋት ኃይሎችና ቅጥረኞች ጥፋት እንዳያመጡ ማድረግ ይቻላል” ብለዋል።    

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምርጫውን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ ያወሱት፣ በጣም ብዙ ኃይሎች ቋምጠው የሚጠብቁት ይህንን ምርጫ እንደሆነ ነው። በዚህ ምርጫ አማካይነት ኢትዮጵያ ውስጥ ችግር መፍጠር ይቻላል በማለት ብዙ ሀብት የሚያፈሱ አገሮች እንዳሉ፣ ይህንን ችግር የሚገነዘቡና የሚያዩ ብዙ ሰዎች ምርጫው አያስፈልግም እንደሚሉ፣ ምርጫው ቅንጦት ነው የሚሉ ሰዎች ዝም ብለው ሳይሆን መከራከሪያቸው ችግሩን በማየት፣ የኢትዮጵያን ቀጣይነትና ህልውና ቅድሚያ በመስጠት ስለሆነ እንደሚጨነቁ አስረድተዋል።

ከዚህ ምርጫ ምንድነው የምናገኘው? ብዙ ተዋንያን ሊያጠፏት የሚፈልጓትን አገር በውስጥ ሳንግባባ ምርጫ ብለን ከነበረው ሁኔታ የዘቀጠ ነገር እንዳይፈጠር በማለት የሚሠጉ አሉ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ሥጋቱን አጉልተው ምርጫው ባይኖር እንደሚፈልጉ እንደሚናገሩ አስታውቀዋል። “በሌላ በኩል ደግሞ ምርጫው ባለመደረጉ ለረብሻና ለብጥብጥ እንደ ነጥብ ለመጠቀም የሚፈልጉ ኃይሎች ስላሉ፣ የመንግሥትን ቅቡልነት የሚያሳጡና ሰብሰብ ብለን ወደ ልማት ወደ ብልፅግና እንዳናተኩር የሚያደርጉ  ስላሉ ምርጫ ማድረግ አስፈላጊ የሚሆንባቸው ሁኔታዎች አሉ” ብለዋል።

ምርጫው መካሄድ አለበት ወይም የለበትም ብሎ የሚወስነው አካል ለሚመጣው ውጤት ኃላፊነት የሚወስድ መሆኑን ገልጸው፣ ‹‹ምርጫ አማራጭ መሆኑ አያጠራጥርም። አሁን በመድረኩ ወንድሞቼና እህቴ እንዳነሳችሁት እያንዳንዱ ዜጋ ሰላም የሁሉም ነገር መሠረት መሆኑን አውቆ፣ ጊዜ ስላለም ማንን እንደሚመርጥ እያሰበ ቆይቶ ከመረጠ በኋላ ድንጋይ የሚወረወር ከሆነ ግን በጋራ መቆም አለበት። በዚህ በሚጠበቀው አገራዊ ምርጫ በከተማ ውስጥ ድንጋይ የሚወረውርና ውጤቱን ባለመቀበል የሚደረግ ተቃውሞ ይኖራል ብዬ አልጠብቅም። ሥጋቱ ግን የተገዙ አካላት ቀውስ እንዳይፈጥሩ ነው፤›› ሲሉ አስረድተዋል።

“መጪው ምርጫ ዕድልና ችግሮችን ይዟል፤” በማለት ሁለቱንም ተገንዝቦ ለመምረጥ የሚነሳና የሚመርጠውን አካል ሕጋዊነት ያረጋገጠ ማኅበረሰብ እንዲፈጠር፣ ይህን መሰል ውይይቶች እንደሚያስፈልጉ አሳስበዋል።

የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ኃላፊዎችና ልሂቃን የተሳተፉበት የአዲስ ወግ ውይይት “ሰላምና ደኅንነት በምርጫ ወቅት” በሚል ርዕስ በወቅታዊ ጭብጥ የተመረጠ ሲሆን፣ በሦስት ክፍለ ጊዜያት በተለያዩ ርዕሶች የሚካሄድ ነው።

ማክሰኞ መጋቢት 21 ቀን 2013 ዓ.ም. ማለዳ የተካሄደው የመጀመርያው ክፍል የአዲስ ወግ ውይይት በሰላማዊ ምርጫ መገለጫዎችና መሥፈርቶች ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ ከቀትር በኋላ የተካሄደው ክፍል በምርጫ ወቅት ሰላምን ለማስፈን ሰላምን የሚያንፁ አገር በቀልና ዘመናዊ ተቋማት ሚና ተዳሰዋል። ባለ ሦስት ክፍሉ የአዲስ ወግ ፍፃሜ ረቡዕ መጋቢት 22 ቀን 2013 ዓ.ም. ሐሰተኛ መረጃ በሰላማዊ ምርጫ ላይ ያለውን አሉታዊ ተፅዕኖ መግታት በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ እንደሚካሄድ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያስረዳል። (ሪፖርተር)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: election 2013, election 2021

Reader Interactions

Comments

  1. ነፃ ሕዝብ says

    April 1, 2021 06:16 am at 6:16 am

    ይሄ ነፍሰ_ገዳይ ዘረኛና የግራኝ አህመድ የጥፋት ውላጅ በማላይ ንግግሮቹ አያሌ ኢትዮጵያውያንን በማጭበርበር ሕዝብ እያሳረደ ይገኛል ፥ አብይ አህመድ አሊ ከእንግዲህን ወዲያ ኢትዮጵያን መምራት ሳይሆን በዓለም ወንጀለኛ ፍ/ቤት (ICC) ቀርቦ መጠየቅ እንጂ ለዚያች ሀገር የመምራት ብቃትም ሆነ ሞራል የለውም ፥ ከእንግዲህን ወዲያ እርሱ ይኖራል ወይ እኛ ጨርሰን እናልቃለን ፡፡

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule