• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጉ፣ የአቶ ዠ ልጅ ወይም “ጉማሬው” ዋናተኛ

August 18, 2016 12:01 pm by Editor Leave a Comment

አቶ ዠ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ከተጫነባቸው በኋላ በUN ኢትዮጵያን ወክሎ የመቀመጥ ስልጣናቸው ቀረና ወደ ሌላ ሥልጣን ተሻገሩ። እድገት ወይም ውርደት (promotion ወይም demotion) ሳንል፣ ወደ ሌላ ሥልጣን ተሻገሩ እንላለን። አቶ ዠ የሃገሪቱ የዋና ፌዴሬሽን ፕሬዚደንት ሆነው ተሾሙ። እንግዲህ “ፕሬዚደንት” የሚለው ቃል እስካለ ድረስ፣ ሹመቱ፣ ማዕረጉ ትልቅ ነው ተብሎ እንዲታሰብ የአቶ ዠ መልካም ፈቃድ ነው እንላለን። የዋና ፌዴሬሽን ፕሬዚደንት ሆነው የተሾሙበት ጊዜ ደግሞ እንዳጋጣሚ ሆኑ የኦሎምፒክ ውድድር የተቃረበበት ጊዜ ነበር። ዠ አዲሱ ቢሮአቸው ሆነው አንድ ሃሳብ ብልጭ አለላቸው። ሃገራቸውን በኦሎምፒክ መወከል። የሃገራቸውን ሰንደቅ ዓላማ በኦሎምፒክ መክፈቻ ላይ ተገኝቶ ማውለብለብ…። እንዴት ያለ ድንቅ ሃሳብ ሲሉ አሰቡ አቶ ዠ።

እንግዲህ መሰደብ፣ መዋረድ፣ መሰደድ፣ መደብደብ፣ መራብ… ወዘተርፈ… ባጨሩ ያለም ሁሉ መከራ ተሰብስበው የሃገሪቱ ህዝብ ላይ የወረዱበት ዘመን መሆኑ አይረሳም። የዚህ ሁሉ ምክንያት ደግሞ ያው “ዠ”ዎች ናቸው ተብሎ በሰፊው ይታመናል። ሙሰኝነት፣ ቅጥ ያጣ ስግብግብነት፣ ዘረኝነት፣ በሥልጣን ያለአግባብ መጠቀም… ወዘተርፈ (ላበ-ተርፈ ሊባል አይችልም። ዛሬ “ዠ”ዎች ወዛም እንጂ ላባም አይደሉምና) ያመጡት ጣጣ ነው።

ሰሞኑን የሃገሬው ህዝብ ያፈረበትና የተሰደበበት ሁኔታም በዚሁ ምክንያት ነው፣ የስግብግብነትና በሥልጣን ያለአግባብ መጠቀም ውጤት ናቸው። አባት ልጁን ከሌሎች፣ ችሎታ ካላቸው የማስቀደም – ዠ  “ጉ” ን ከሌሎች፣ ችሎታው ካላቸው የማስቀደም ውጤት ናቸው። “ዋናተኛው” ጉን ማስቀደማቸው። “ዋናተኛው” ጉ ሃገሩን ወክሎ “ዋኝቶ” ህዝቡንና ሃገሩን አሳፍሯል። የሃገሬው አትሌቶች ህዝባቸውን በማኩራትና ሃገራቸውን በበጎ በማስጠራት ነበር የሚታወቁት። ጉ፣ የአቶ ዠ ልጅ ደግሞ በበኩሉ በአለም ታይቶ የማይታወቅ ቀርፋፋነትን በማሳየት ሃገሪቷን ዳግም አስጠራ። ዳግም አዋረዳት! ጋዜጦች ጻፉ፣ “ሃገሪቷ እኮ ባህር የላትም፣ መሬት ብቻ ነች።” ሲሉ። “ጉ የሚዋኝበት፣ የሚለማመድበት የለም እኮ” እንደማለት ከጀላቸው። ሰው ዋና የሚዋኘው ባህር ውስጥ ብቻ ነው? ሃይቆችና ወንዞች የሉም እንዴ?

“ዋናተኛው” ጉ እጅግ ወደኋላ ከመቅረቱ የተነሳ ከቴሌቪዢን ካሜራ እይታ ውጪ ነበር። ሌሎቹ ዋኝተው ጨርሰው ኮፍያቸውንና መነጽራቸውን አውልቀው ሰውነታቸውን ለማደራረቅና ልብሳቸውን ለመቀየር ሲዘጋጁ “ጉማሬው” ዋናተኛ ጉ ውሃ ውስጥ ይጎማለላል። አንዳንዶች ”ምናልባት ነዳጅ እየፈለገ ይሆናል” ሲሉ አላገጡ። አንዳንዶች ደግሞ  “አሳነባሪው” ጉ ብለው አንሾካሾኩ (tweet አደረጉ)። “አሳ ነባሪ እኮ በጣም ይዋኛል። ውቅያኖስ ያቋርጣል” ሲሉ ሌሎች ተከራከሩ። በመጨረሻ “ጉማሬው” በሚለው ቅጽል ተስማሙ።

“ጉማሬው” ዋናተኛ የሃገሪቱ ምርጥ ዋናተኛ አይደለም ሲል አንድ አንድ ታዋቂ ጋዜጣ ደግሞ እንዲህ ሲል ዘገበ፣ “ጭምጭምታ ከሁነኛ ምንጮች እንደሰማነው ጉ የሃገሩ ምርጥ ዋናተኛ አይደለም። በተለየ ችሮታ ነው እንዲወዳደር የተደረገው፣ አባቱ አቶ ዠ የሃገሪቱ የዋና ፌዴሬሽን ፕሬዚደንት ናቸው።” ይለናል። አቶ ዠ ከልጃቸው ከ ጉ ጎን ሆነው የሃገራቸውን ሰንደቅ ዓላማ ይዘው የታዩበትን ፎቶ ጋዜጣው ጎልጉሎ አውጥቶ ለጥፎታል።

ከውድድሩ በኋላ“ጉማሬው” ዋናተኛ ቃለ መጠይቅ ተደርጎለት ሲመልስ፣ “በኦሎምፕክ ስወዳደር የመጀመሪያ  ጊዜዬ  ነው። ባገኘሁት ውጤት በጣም ተደስቻለሁ። በኦሎምፒክ መሳተፍ በጣም ትልቅ ክብር ነው። ስለዚህም ደስተኛ ነኝ። እኔ ሃገር ሁሉም ይሮጣል፣ ይሮጣል…እኔ ግን እንደነሱ መሮጥ አልፈለግኩም፣ በዋና ነው ሃገሬን መወከል የፈለግኩት” አለ። ጋዜጠኛው፣ “ምናልባት ብትሮጥ ኖሮ ቦርጭህ ስለሚረግፍ፣ በዋና ከዚህ የተሻለ ውጤት ልታገኝ ትችል እንደነበር ትገምታለህ” ሲል አከታትሎ ጠየቀው። ጉ አልመለሰም። አንገቱን አቀርቅሮ የዋና መነጽሩን ማሻሸት ያዘ።

የሃገሬው ህዝብ፣ “ይሄ ነገር እንዴት ነው?” ሲል ማሰላሰል ያዘ።

“የመጀመሪያዬ” የሚለው ቃል የሃገሪቱን ህዝብ አበሳጨ። “የመጀመሪያዬ”? ”ይሄ ሰው፣ ጉ ዠ ሃገራችንን ደጋግሞ ሊያሰድብ ይፈልጋል እንዴ?” ሲል የሃገሬው ህዝብ በቁጨት ጸጉሩን ነጨ። ህዝቡ “የሃገሩ ምርጥ ዋናተኛ ሳይሆን ይህ ዕድል ለሱ የተሰጠው በምን ምክንያት ነው? ሌሎች፣ ከሱ የተሻሉ ስንት አመት ሙሉ ለዚህ ዕድል፣ ለዚች ቀን፣ ለኦሎምፒክ ሲሉ ሲዘጋጁ የከረሙ እያሉ እሱ በምን ምክንያት፣ ያለችሎታው ለኦሎምፒክ በቃ? እስከመቼ ነው እንዲህ በቅጥ ያጣ ስግብግብነት፣ በዘረኝነት፣ በሥልጣን ያለአግባብ በመጠቀም በሚመጣ ውርደት ተሸማቀን የምንኖረው?” ሲል የሃገሬው ህዝብ ተቆጣ።

“ከሱ የላቀ ችሎታ ያላቸው እያሉ እሱ እንዴት ይህንን፣ ሃገራችንና እኛን እንዲወክል ተደረገ? በምንሥ ምክንያት ነው? የዚህ ሁሉ ፈላጭ ቆራጭ፣ የዋና ፌዴሬሺኑ ፕሬዚደንት፣ አቶ ዠ ተጠያቂ ይሆናሉንስ?” ሲል ህዝቡ እንደዝናብ አጉረመረመ፣ ከዚያም እንደነጎድጓድ አስጎመጎመ፣ አስጎምጉሞም አልቀረ። እንደ በልግ ዝናብ ድንገት መውረድ ጀመረ፣ እንደ ሃምሌ ወንዝ ጎዳናውን ሞላው፣ በቁጣ ሞገድ ጎዳናውን እንደ ማዕበል አናወጠ።

“መዋራድ በቃን! መሰደብ በቃን!”

“ክብራችንን ያዋረደው ዠ ተጠያቂ ይሁን!”

“ቅጥ ያጣ ስግብግብነት፣ ዘረኝነት፣ በሥልጣን ያለአግባብ መጠቀም አሁኑኑ ይቁም !”

አቶ ዠ ደግሞ ቢሮአቸው ሆነው በመስኮት ማዕበሉን ይመለከቱ ጀመር። የማዕበሉ ሞገድ እቢሮአቸው ገብቶ  ጠራርጎ እንዳይወስዳቸው ሰጉ።

ከህዝቡ፣

“ሥራና ሃላፊነት በችሎታ እንጂ በችሮታ መሆኑ ዛሬውኑ ይቁም!” የሚሉ ቃላት እንደነጎድጓድ ያስጎመጉሙ፣ እንደ መብረቅ ያብለጨልጩ ጀመር።

በዚያ ብልጭታ ህዝቡ ተስፋ ማየት ጀመረ። የእኩልነት ተሰፋ፣ የማደግ ተስፋ፣ የመኖር ተስፋ፣ በችሎታ እንጂ በችሮታ ያለመኖርን ተስፋ…

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature, Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule