• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለአህመዲን ጀበል ህክምና ስጡት፣ ፍቱትም!

November 16, 2017 03:29 pm by Editor Leave a Comment

  • በግፍ አስሮም ህክምና መንፈግ ለምን?
  • ሀሳብን የደፈረው ጀግና  …!

የወንድም ኡስታዝ አህመዲን ጀበልን በእስር ላይ ህክምና መነፈጉን ከተለያዩ ምንጮች ለማረጋገጥ ችያለሁ። በእስር ላይ ያሉ ወገኖችን በህገ መንግስትና በአለም አቀፍ ህግ የተደነገገ እየተጣሰባቸው ነው። በህግ ስር ባለው ኡስታዝ አህመዲንና በብዙ ታሳሪዎች መንግስት የሰብአዊ መብት ጥሰት እየፈጸመባቸው ተደጋግሞ ተመልክተናል። ዛሬ አደባባይ በአህመዲን ያየነውም ይህንኑ ነው። በኡስታዝ አህመዲን ሰውነት ላይ የሚታየውን ጉዳትና መጎሳቆል ስመለከት የተሰማኝ ስሜት ደስ አይልም።

አሳሪው መንግስት ደጋግሞ “ኡስታዝ አህመዲንና ጓደኞቹ የታሰሩት በህግ ጥሰት ነው!”  ቢልም የታሰረበት በመፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴነቱ ብቻ እንደሆነ አምናሁ። ከታሰሩት በርካታ የመፍትሔ አፈላላጊዎች ኮሚቴ አባላት መካከል  ኡስታዝ አህመዲንን ጨምሮ ጥቂቶች ተለይተው ሲቀሩ ዋና ዋና የተባሉት ተከሳሾች በነጻ ተፈትተዋል። ዛሬ ጎልማሳው ወንድም አህመዲን እንደቀሩት ወንድሞቹ እኩል ከወህኒ እንዲወጣ ባይፈቀድለት እንኳ ህክምና የማግኘት መብቱ ሊከበርለት ይገባል እላለሁ!

በእስር ላይ ሆኖ ህክምና አለማግኘት ቀርቶ ህክምና እያገኙ ኑሮን መግፋት እጅግ የከፋ መከራ ስለመሆኑ ከ4 ዓመት በፊት በወራት የሳውዲ ወህኒ ህይዎቴ አውቀዋለሁ። “ከአረብ ሀገራት በተሻለ መልኩ የሰብአዊ መብት ይዞታ ተከብሯል”  በምትባለው ኢትዮጵያ ሀገራችን መሳሪያ ያላነሳ ታሳሪን ህክምና ነፍጎ ማሰቃየትን የመሰለ የከፋ ግፍ ሲፈጸም ደጋግመን ተመልክተናል። ይህ መራራ እውነት እጅግ በጣም ያሳዝናል! ልብን በሀዘን ይሰብራል! ኡስታዝ አህመዲን ጀበል በአስቸኳይ ህክምና ይደረግለት ዘንድ የዜጋ ድምጼን አሰማለሁ!

ሀሳብን የደፈረውን ጀግና ፍቱት …!

ወንድም ኡስታዝ አህመዲን ጀበልን ሳስታውስ ብዙ ነገሩ  ትዝ ይለኛል። ኡስታዝ አህመዲን ለቆመበት አላማ ጽኑ ነው። የህዝብ ከበሬታ ያሰጠው አስተምህሮት መሆኑንም ለመረዳት ብዙ ጊዜ አልፈጀብኝም። ኡስታዝ አህመዲን በሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ ተመርጦ በወቅቱ ለነበረው ሁከት መፍትሔ አመንጭ ከነበሩት መካከል አንዱ ነበር። ዳሩ ግን ለመፍትሔ የተወከሉት “ወንጀለኛ” ተብለው ዘብጥያ ሲወርዱ አህመዲን ክራሞቱ ወህኒ ሆነ። በእሱና በቀሩት ወንድሞች እስር አዘንን።

ኡስታዝ አህመዲን ጀበል

ኡስታዝ አህመዲን የሀገሬ ሰው ለማንሳትና በአደባባይ ለመሞገት ይፈራቸው የነበሩ የሙስሊም ጉዳዮችን በስራዎቹ እያነሳ የማይደፈር ሀሳብን የደፈረ በመሆኑ አደንቀዋለሁ። በጋዜጦችና በየአደባባዩ ሀሳብን ሲያቀርብና ሲሞግት፣ ከዚያም የታሪክ ድርሳናትን ፈታትሾ ለንበብ  ሲያቀርብ ተመልክቻለሁ። አህመዲን የማህበረሰቡ ውስጥ ይንሸራሸር የነበረውን ሀሳብ በአደባባይ ማውጣቱና መነጋገሪያ ማድረጉን አደንቃለሁ!

የኡስታዝ አህመዲንን የጻፋቸውን መጻሕፍት ደጋግሜ ካነበብኳቸው ውስጥ ቀዳሚዎቹ ናቸው። “ስለ ሙስሊሙ ጉዳት ያገባኛል” ማለቱንና ሀሳቡን በነጻነት መግለጹን አከብርለታለሁ። በመጽሐፍቱ ያሰናዳቸውን ሀሳቦችና ምልከታዎቻ ጋር ግን ብዙም አልስማማም። በሀሳብ ልዩነት አምናለሁ፣  የሀሳብ ልዩነት አለን ማለት ሰብአዊ መብቱ ሲጣስ ዝም እላለሁ ማለት አይደለም።

ጎልማሳው ኡስታዝ አህመዲን የሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባል ሆኖ እያለ ሲጀመር መንግስት ሆደ ሰፊ በመሆን መፍትሔ አብሮ እንደመፈለግ ማሰሩ ምን ጠቀመ? በግፍ አስሮም ህክምና መንፈግስ ለምን? ብየ ደጋግሜ ራሴን ጠይቄያለሁ። አጥጋቢ መልስ ግን የለኝም። በህግና ስርአት እስር ላይ ያለን ፍርደኛ ህክምና ነፍጎ ማንገላታትና እንዲህ እንዳየነው ከሰው ተራ ማውጣት ግለሰብን ብቻ ሳይሆን ዜጋን መናቅ ማለት ነው። እናም የታሳሪውን ስቃይ ስሰማ ከተናቁት ዜጎች መካከል መሆኔ ተሰምቶኛል። ለኡስታዝ አህመዲን ጀበል ህክምና ከማድረግ በላይ በህዝብ ውክል በመውሰዱ ለወህኒ የተዳረገ ወጣት ነውና በአስቸኳይ ትፈቱት ዘንድ የዜጋ ድምጼን አሰማለሁ!

ፍትህ ለኡስታዝ አህመዲንና በግፍ ለሚሰቃዩት ታሳሪዎች!

ወዳጄ ኡስታዝ አህመዲን ሆይ ምህረቱን ይላክልህ! (ፎቶዎቹ ከማህበራዊ ሚዲያ የተገኙ ናቸው)

እስኪ ቸር ያሰማን

ነቢዩ ሲራክ

ህዳር 7 ቀን 2010 ዓም


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Social Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule