• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለአህመዲን ጀበል ህክምና ስጡት፣ ፍቱትም!

November 16, 2017 03:29 pm by Editor Leave a Comment

  • በግፍ አስሮም ህክምና መንፈግ ለምን?
  • ሀሳብን የደፈረው ጀግና  …!

የወንድም ኡስታዝ አህመዲን ጀበልን በእስር ላይ ህክምና መነፈጉን ከተለያዩ ምንጮች ለማረጋገጥ ችያለሁ። በእስር ላይ ያሉ ወገኖችን በህገ መንግስትና በአለም አቀፍ ህግ የተደነገገ እየተጣሰባቸው ነው። በህግ ስር ባለው ኡስታዝ አህመዲንና በብዙ ታሳሪዎች መንግስት የሰብአዊ መብት ጥሰት እየፈጸመባቸው ተደጋግሞ ተመልክተናል። ዛሬ አደባባይ በአህመዲን ያየነውም ይህንኑ ነው። በኡስታዝ አህመዲን ሰውነት ላይ የሚታየውን ጉዳትና መጎሳቆል ስመለከት የተሰማኝ ስሜት ደስ አይልም።

አሳሪው መንግስት ደጋግሞ “ኡስታዝ አህመዲንና ጓደኞቹ የታሰሩት በህግ ጥሰት ነው!”  ቢልም የታሰረበት በመፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴነቱ ብቻ እንደሆነ አምናሁ። ከታሰሩት በርካታ የመፍትሔ አፈላላጊዎች ኮሚቴ አባላት መካከል  ኡስታዝ አህመዲንን ጨምሮ ጥቂቶች ተለይተው ሲቀሩ ዋና ዋና የተባሉት ተከሳሾች በነጻ ተፈትተዋል። ዛሬ ጎልማሳው ወንድም አህመዲን እንደቀሩት ወንድሞቹ እኩል ከወህኒ እንዲወጣ ባይፈቀድለት እንኳ ህክምና የማግኘት መብቱ ሊከበርለት ይገባል እላለሁ!

በእስር ላይ ሆኖ ህክምና አለማግኘት ቀርቶ ህክምና እያገኙ ኑሮን መግፋት እጅግ የከፋ መከራ ስለመሆኑ ከ4 ዓመት በፊት በወራት የሳውዲ ወህኒ ህይዎቴ አውቀዋለሁ። “ከአረብ ሀገራት በተሻለ መልኩ የሰብአዊ መብት ይዞታ ተከብሯል”  በምትባለው ኢትዮጵያ ሀገራችን መሳሪያ ያላነሳ ታሳሪን ህክምና ነፍጎ ማሰቃየትን የመሰለ የከፋ ግፍ ሲፈጸም ደጋግመን ተመልክተናል። ይህ መራራ እውነት እጅግ በጣም ያሳዝናል! ልብን በሀዘን ይሰብራል! ኡስታዝ አህመዲን ጀበል በአስቸኳይ ህክምና ይደረግለት ዘንድ የዜጋ ድምጼን አሰማለሁ!

ሀሳብን የደፈረውን ጀግና ፍቱት …!

ወንድም ኡስታዝ አህመዲን ጀበልን ሳስታውስ ብዙ ነገሩ  ትዝ ይለኛል። ኡስታዝ አህመዲን ለቆመበት አላማ ጽኑ ነው። የህዝብ ከበሬታ ያሰጠው አስተምህሮት መሆኑንም ለመረዳት ብዙ ጊዜ አልፈጀብኝም። ኡስታዝ አህመዲን በሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ ተመርጦ በወቅቱ ለነበረው ሁከት መፍትሔ አመንጭ ከነበሩት መካከል አንዱ ነበር። ዳሩ ግን ለመፍትሔ የተወከሉት “ወንጀለኛ” ተብለው ዘብጥያ ሲወርዱ አህመዲን ክራሞቱ ወህኒ ሆነ። በእሱና በቀሩት ወንድሞች እስር አዘንን።

ኡስታዝ አህመዲን ጀበል

ኡስታዝ አህመዲን የሀገሬ ሰው ለማንሳትና በአደባባይ ለመሞገት ይፈራቸው የነበሩ የሙስሊም ጉዳዮችን በስራዎቹ እያነሳ የማይደፈር ሀሳብን የደፈረ በመሆኑ አደንቀዋለሁ። በጋዜጦችና በየአደባባዩ ሀሳብን ሲያቀርብና ሲሞግት፣ ከዚያም የታሪክ ድርሳናትን ፈታትሾ ለንበብ  ሲያቀርብ ተመልክቻለሁ። አህመዲን የማህበረሰቡ ውስጥ ይንሸራሸር የነበረውን ሀሳብ በአደባባይ ማውጣቱና መነጋገሪያ ማድረጉን አደንቃለሁ!

የኡስታዝ አህመዲንን የጻፋቸውን መጻሕፍት ደጋግሜ ካነበብኳቸው ውስጥ ቀዳሚዎቹ ናቸው። “ስለ ሙስሊሙ ጉዳት ያገባኛል” ማለቱንና ሀሳቡን በነጻነት መግለጹን አከብርለታለሁ። በመጽሐፍቱ ያሰናዳቸውን ሀሳቦችና ምልከታዎቻ ጋር ግን ብዙም አልስማማም። በሀሳብ ልዩነት አምናለሁ፣  የሀሳብ ልዩነት አለን ማለት ሰብአዊ መብቱ ሲጣስ ዝም እላለሁ ማለት አይደለም።

ጎልማሳው ኡስታዝ አህመዲን የሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባል ሆኖ እያለ ሲጀመር መንግስት ሆደ ሰፊ በመሆን መፍትሔ አብሮ እንደመፈለግ ማሰሩ ምን ጠቀመ? በግፍ አስሮም ህክምና መንፈግስ ለምን? ብየ ደጋግሜ ራሴን ጠይቄያለሁ። አጥጋቢ መልስ ግን የለኝም። በህግና ስርአት እስር ላይ ያለን ፍርደኛ ህክምና ነፍጎ ማንገላታትና እንዲህ እንዳየነው ከሰው ተራ ማውጣት ግለሰብን ብቻ ሳይሆን ዜጋን መናቅ ማለት ነው። እናም የታሳሪውን ስቃይ ስሰማ ከተናቁት ዜጎች መካከል መሆኔ ተሰምቶኛል። ለኡስታዝ አህመዲን ጀበል ህክምና ከማድረግ በላይ በህዝብ ውክል በመውሰዱ ለወህኒ የተዳረገ ወጣት ነውና በአስቸኳይ ትፈቱት ዘንድ የዜጋ ድምጼን አሰማለሁ!

ፍትህ ለኡስታዝ አህመዲንና በግፍ ለሚሰቃዩት ታሳሪዎች!

ወዳጄ ኡስታዝ አህመዲን ሆይ ምህረቱን ይላክልህ! (ፎቶዎቹ ከማህበራዊ ሚዲያ የተገኙ ናቸው)

እስኪ ቸር ያሰማን

ነቢዩ ሲራክ

ህዳር 7 ቀን 2010 ዓም


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Social Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule