• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ፍቅር እስከ መቃብር” በሰሜን ዋልታ

February 9, 2015 07:07 am by Editor 1 Comment

ዶክተር ሬዶልፍ ክኑት ሞልቨር (Reidulf Knut Molvær) የ77 ዓመት ኖርዌጂያዊ አዛውንት ናቸው። ዋና ሙያቸው የሥነ ጥሑፍ፣ የቋንቋ፣ የታሪክና የማህበራዊ ሳይንስ ተመራማሪነት ነው። በአማርኛ ሥነ ጽሁፍና ቋንቋ ጥናት ከሎንዶን ዩኒቨርስቲ የዶክትሬት ድግሪያቸውን ያገኙ ሲሆኑ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ 14 ኬንያ ውስጥ ደግሞ 6 ዓመታትን ባለም አቀፍ ድርጅቶች ውስጥ በመሥራት አሳልፈዋል። የትዳር ጓደኛቸው ኬንያዊት ሲሆኑ፣ አራት ልጆችም በጋራ አፍርተዋል። ከልጆቻቸውም መካከል አንዱ የሕክምና ዶክተር፣ ሁለቱ ኢንጂነሮች ሆነዋል።

ዶ/ር ሞልቨር ለፍልስፍና ማስትሬት ድግሪያቸው መመረቂያ  አዘጋጅተውት የነበረው ጥናታቸው ቀዳሚውን እውቅና አስገኝቶላቸው የነበረ ነው። ይህን ጥናታቸውን “ልማድና ለውጥ በኢትዮጵያ – Tradition and Change in Ethiopia: Social and Cultural Life as Reflected in Amharic Fictional Literature ca. 1930-1974” በሚል አቢይ ርእስ ስር አስቀምጠው ባለ 365 ገጽ መጽሐፍ እ.አ.አ. በ1980 ዓ.ም- አሳትመው አውጥተዋል። ይህ የበኩር ሥራቸው የብዙ አንባቢያንንና ተመራማሪዎችን ቀልብ የሳበ ሆኖ እስከዛሬ ድረስ ዘልቋል። ለጥቀውም ”ማኅበራዊነትና ማኅበራዊ ቁጥጥር በኢትዮጵያ – Socialization and Social Control in Ethiopia” እ.አ.አ. በ1995 ዓ.ም. አንድ ዳጎስ ያለ መጽሐፍ ለንባብ አብቅተዋል።

ከዚህ ሥራቸው ቀጥለውም በእንግሊዝኛ ቋንቋ “Black Lions – The Creative Lives of Modern Ethiopia’s Literary Giants and Pioneers” በሚል ርእስ የመጀመሪያውን የ33 ኢትዮጵያውያን ደራስያንን ሥራና የሕይወት ታሪክ ያካተተ መጽሐፍ እ.አ.አ. በ1997 ዓ.ም. ላይነ ንባብ አብቅተዋል። ይህም ድንቅ ሥራቸው በዚህ ረገድ የነበረውን የመረጃ እጥረት ክፍተት ለመሸፈን ከፍተኛ እገዛ አድርጓል። ከብላቴን ጌታ ሕሩይ ወልደ ሥላሴ እስከ እኔ ትውልድ ያሉትን ተጠቃሽ ጸሐፍት አካተውበታል።

ሰንበት ብለውም በዚሁ መድበላቸው ውስጥ ያልተካተቱትነ የሁለት እውቅ ኢትዮጵያውያን የሕይወት ታሪኮችና ሥራዎቻቸውን ”የሰሜን ምሥራቅ አፍሪካ ጥናት- Northeast African Studies” በተሰኘ ታዋቂ  ጁርናል ላይ አቅርበው አስነብበዋል። እኒህም ሁለት እውቅ ደራስያን ሻምበል  አፈወርቅ ዮሐንስና ደራሲ ደበበ ሰይፉ ናቸው።

ቀጥለውም የተለያዩ ጥናታዊ ጽሑፎችን በኢትዮጵያ ሥነ ጥሑፍ፣ ቋንቋ፣ ታሪክና ማህበራዊ ሳይንስ ዙሪያ እያዘጋጁ በተለያዩ ጉባዔዎችና ጁርናሎች ላይ አቅርበዋል። አሁን በቅርቡ በሐምሌ ወር 2014 ዓ.ም. ደግሞ የክቡር ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁን ዝነኛውን ያገራችንን ረዥም ልቦለድ መጽሐፍ ”ፍቅር እስከ መቃብር”ን ወደ ኖርዌጂያንኛ ቋንቋ “Kjærlighet til graven” በሚል ርእስ ተርጉመው፣ ለንባብ አብቅተዋል። ይህ ወደ ኖርዌጂያን ቋንቋ የተተረጎመው ሥራቸው 607 ገጾች ያለው ሲሆን፣ በኖርዌጂያን አንባቢያን ዘንድ ትልቅ ተነባቢነትንና ተቀባይነትንአግኝቶላቸዋል።

ዶ/ር ሞልቨር ለዚህ ድንቅ ሥራቸው ክብርና ሞገስ ሊሰጣቸው የሚገባችው ታታሪ ሰው ናቸው። ”ፍቅር አስከ መቃብር” ከዚህ ቀደም ወደ ራሽያንና ወደ እንግሊዝኛ ቋንቋዎች መተርጎሙ ይታወሳል። አሁን ደግሞ ወደ ኖርዌጂያን ቋንቋ መተርጎሙ፣ በሰሜን ዋልታ የእስካንዲኔቪያን አገሮች ቋንቋዎች የመተርጎም እድሉን ከፍ ያድርገዋል። ይሄውም ወደ እስዊድንኛ፣ ዳንማርኪኛ፣ ፊንማርኪኛና ሳሚኛ ቋንቋዎች የመተርጎም እድሉ ሰፊ ነው። ዶ/ር ሞልቨርን ሳወያያቸው በቀጣይነት ስላሰቧቸው የትርጉም ሥራዎቻቸው ጠይቄያቸው ነበር። ከአማርኛ ሥነ ጽሑፎች ውስጥ የብላቴን ጌታ ማህተመ ሥላሴ ወልደ መስቀልን “እንቅልፍ ለምኔ” ፣ የአፈወርቅ ገብረ ኢየሱስን ”ጦቢያ”፣ የደጃዝማች ግርማቸው ተክለ ሐዋሪያትን ”አርአያ”፣ ከኬንያ ሥነ ጽሑፍ ደግሞ የንጉጊ ዋቲያንጎን “Grain of Wheat” ለመተርጎም ከጀመሯቸውና በእቅድ ከያዟቸው ሥራዎች መካከል እንዳሉ አጫውተውኛል። የታዋቂውን ኬንያዊ ደራሲ የንጉጊን መጽሐፍ እንዲተረጉሙ የግድ ሰበብ የሆናቸውም ለሥነ ጽሑፍ የኖቤል ሽልማት እጩ ሆኖ እንዲቀርብ ስለታሰበ፣ ከወዲሁ በኖርዌጂያን አንባቢያን ዘንድ እውቅናውን ለማጠንከርና መንገዱንም ለመጥረግ እንዲያመች እንደሁ ዶ/ር ሞልቨር አልሸሸጉኝም። እኒህ ይበልጡኑ በኢትዮጵያ ሥነ ጥሑፍ፣ ቋንቋ፣ ታሪክና ማህበራዊ ሳይንስ ዙሪያ ጥብቅ ምርምር ሲያደርጉ የኖሩ ሰው፣ ከዚህ ቀደምም አንድ በኪስዋህሊ ቋንቋ የተጻፈ የኬንያ ሥነ ጽሑፍ ወደ ኖርዌጂያን ቋንቋ መተርጎማቸውም ይታወቃል።

ከዶ/ር ሞልቨር ተጨማሪ ሥራዎች መካከል እነዚህም ይገኙባቸዋል

ዶ/ር ሞልቨር ለኢትዮጵያውያን ደራስያንና የቀለም ሰዎች ታላቅ አክብሮትና ፍቅር ያለቸው ሰው መሆናቸውም የሚሰመርበት ጉዳይ ነው። እ.አ.አ. በ2005 ዓ.ም. ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅንን ለኖርዌይ ደራስያን ማኅበር “ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ ሽልማት” እጩ ተወዳዳሪ አድርጌ ባቀረብኩበት ሰዓት ከጎኔ ከሞቆማቸውም በላይ፣ በቀጣዩ ዓመት ሎሬት ጸጋዬን ለኖቤል ሽልማት እጩ አድርጎ ለማቅረብ፤ ከእኔና ከጋሼ ኃይሉ ገብረ ዮሐንስ (ገሞራው) ጎን ለመሰለፍ ቃል ገበተውልን የነበሩ ናቸው። በሎሬት ጸጋዬ እረፍት ምክንያት ያሰብነው ሳይተገበር በውጥን ቀርቷል።

ዶ/ር ሞልቨር በጅምር የያዙዋቸውን ሥራዎች ጨርሰው ለኖርዌጂያን አንባቢያን አቅርበው ለማስነበብ እንዲያበቃቸው ምኞቴ ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. BELIYU BERHANU says

    October 13, 2017 01:01 pm at 1:01 pm

    IT IS VARY GOOD

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule