• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ፍቅር እስከ መቃብር” በሰሜን ዋልታ

February 9, 2015 07:07 am by Editor 1 Comment

ዶክተር ሬዶልፍ ክኑት ሞልቨር (Reidulf Knut Molvær) የ77 ዓመት ኖርዌጂያዊ አዛውንት ናቸው። ዋና ሙያቸው የሥነ ጥሑፍ፣ የቋንቋ፣ የታሪክና የማህበራዊ ሳይንስ ተመራማሪነት ነው። በአማርኛ ሥነ ጽሁፍና ቋንቋ ጥናት ከሎንዶን ዩኒቨርስቲ የዶክትሬት ድግሪያቸውን ያገኙ ሲሆኑ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ 14 ኬንያ ውስጥ ደግሞ 6 ዓመታትን ባለም አቀፍ ድርጅቶች ውስጥ በመሥራት አሳልፈዋል። የትዳር ጓደኛቸው ኬንያዊት ሲሆኑ፣ አራት ልጆችም በጋራ አፍርተዋል። ከልጆቻቸውም መካከል አንዱ የሕክምና ዶክተር፣ ሁለቱ ኢንጂነሮች ሆነዋል።

ዶ/ር ሞልቨር ለፍልስፍና ማስትሬት ድግሪያቸው መመረቂያ  አዘጋጅተውት የነበረው ጥናታቸው ቀዳሚውን እውቅና አስገኝቶላቸው የነበረ ነው። ይህን ጥናታቸውን “ልማድና ለውጥ በኢትዮጵያ – Tradition and Change in Ethiopia: Social and Cultural Life as Reflected in Amharic Fictional Literature ca. 1930-1974” በሚል አቢይ ርእስ ስር አስቀምጠው ባለ 365 ገጽ መጽሐፍ እ.አ.አ. በ1980 ዓ.ም- አሳትመው አውጥተዋል። ይህ የበኩር ሥራቸው የብዙ አንባቢያንንና ተመራማሪዎችን ቀልብ የሳበ ሆኖ እስከዛሬ ድረስ ዘልቋል። ለጥቀውም ”ማኅበራዊነትና ማኅበራዊ ቁጥጥር በኢትዮጵያ – Socialization and Social Control in Ethiopia” እ.አ.አ. በ1995 ዓ.ም. አንድ ዳጎስ ያለ መጽሐፍ ለንባብ አብቅተዋል።

ከዚህ ሥራቸው ቀጥለውም በእንግሊዝኛ ቋንቋ “Black Lions – The Creative Lives of Modern Ethiopia’s Literary Giants and Pioneers” በሚል ርእስ የመጀመሪያውን የ33 ኢትዮጵያውያን ደራስያንን ሥራና የሕይወት ታሪክ ያካተተ መጽሐፍ እ.አ.አ. በ1997 ዓ.ም. ላይነ ንባብ አብቅተዋል። ይህም ድንቅ ሥራቸው በዚህ ረገድ የነበረውን የመረጃ እጥረት ክፍተት ለመሸፈን ከፍተኛ እገዛ አድርጓል። ከብላቴን ጌታ ሕሩይ ወልደ ሥላሴ እስከ እኔ ትውልድ ያሉትን ተጠቃሽ ጸሐፍት አካተውበታል።

ሰንበት ብለውም በዚሁ መድበላቸው ውስጥ ያልተካተቱትነ የሁለት እውቅ ኢትዮጵያውያን የሕይወት ታሪኮችና ሥራዎቻቸውን ”የሰሜን ምሥራቅ አፍሪካ ጥናት- Northeast African Studies” በተሰኘ ታዋቂ  ጁርናል ላይ አቅርበው አስነብበዋል። እኒህም ሁለት እውቅ ደራስያን ሻምበል  አፈወርቅ ዮሐንስና ደራሲ ደበበ ሰይፉ ናቸው።

ቀጥለውም የተለያዩ ጥናታዊ ጽሑፎችን በኢትዮጵያ ሥነ ጥሑፍ፣ ቋንቋ፣ ታሪክና ማህበራዊ ሳይንስ ዙሪያ እያዘጋጁ በተለያዩ ጉባዔዎችና ጁርናሎች ላይ አቅርበዋል። አሁን በቅርቡ በሐምሌ ወር 2014 ዓ.ም. ደግሞ የክቡር ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁን ዝነኛውን ያገራችንን ረዥም ልቦለድ መጽሐፍ ”ፍቅር እስከ መቃብር”ን ወደ ኖርዌጂያንኛ ቋንቋ “Kjærlighet til graven” በሚል ርእስ ተርጉመው፣ ለንባብ አብቅተዋል። ይህ ወደ ኖርዌጂያን ቋንቋ የተተረጎመው ሥራቸው 607 ገጾች ያለው ሲሆን፣ በኖርዌጂያን አንባቢያን ዘንድ ትልቅ ተነባቢነትንና ተቀባይነትንአግኝቶላቸዋል።

ዶ/ር ሞልቨር ለዚህ ድንቅ ሥራቸው ክብርና ሞገስ ሊሰጣቸው የሚገባችው ታታሪ ሰው ናቸው። ”ፍቅር አስከ መቃብር” ከዚህ ቀደም ወደ ራሽያንና ወደ እንግሊዝኛ ቋንቋዎች መተርጎሙ ይታወሳል። አሁን ደግሞ ወደ ኖርዌጂያን ቋንቋ መተርጎሙ፣ በሰሜን ዋልታ የእስካንዲኔቪያን አገሮች ቋንቋዎች የመተርጎም እድሉን ከፍ ያድርገዋል። ይሄውም ወደ እስዊድንኛ፣ ዳንማርኪኛ፣ ፊንማርኪኛና ሳሚኛ ቋንቋዎች የመተርጎም እድሉ ሰፊ ነው። ዶ/ር ሞልቨርን ሳወያያቸው በቀጣይነት ስላሰቧቸው የትርጉም ሥራዎቻቸው ጠይቄያቸው ነበር። ከአማርኛ ሥነ ጽሑፎች ውስጥ የብላቴን ጌታ ማህተመ ሥላሴ ወልደ መስቀልን “እንቅልፍ ለምኔ” ፣ የአፈወርቅ ገብረ ኢየሱስን ”ጦቢያ”፣ የደጃዝማች ግርማቸው ተክለ ሐዋሪያትን ”አርአያ”፣ ከኬንያ ሥነ ጽሑፍ ደግሞ የንጉጊ ዋቲያንጎን “Grain of Wheat” ለመተርጎም ከጀመሯቸውና በእቅድ ከያዟቸው ሥራዎች መካከል እንዳሉ አጫውተውኛል። የታዋቂውን ኬንያዊ ደራሲ የንጉጊን መጽሐፍ እንዲተረጉሙ የግድ ሰበብ የሆናቸውም ለሥነ ጽሑፍ የኖቤል ሽልማት እጩ ሆኖ እንዲቀርብ ስለታሰበ፣ ከወዲሁ በኖርዌጂያን አንባቢያን ዘንድ እውቅናውን ለማጠንከርና መንገዱንም ለመጥረግ እንዲያመች እንደሁ ዶ/ር ሞልቨር አልሸሸጉኝም። እኒህ ይበልጡኑ በኢትዮጵያ ሥነ ጥሑፍ፣ ቋንቋ፣ ታሪክና ማህበራዊ ሳይንስ ዙሪያ ጥብቅ ምርምር ሲያደርጉ የኖሩ ሰው፣ ከዚህ ቀደምም አንድ በኪስዋህሊ ቋንቋ የተጻፈ የኬንያ ሥነ ጽሑፍ ወደ ኖርዌጂያን ቋንቋ መተርጎማቸውም ይታወቃል።

ከዶ/ር ሞልቨር ተጨማሪ ሥራዎች መካከል እነዚህም ይገኙባቸዋል

ዶ/ር ሞልቨር ለኢትዮጵያውያን ደራስያንና የቀለም ሰዎች ታላቅ አክብሮትና ፍቅር ያለቸው ሰው መሆናቸውም የሚሰመርበት ጉዳይ ነው። እ.አ.አ. በ2005 ዓ.ም. ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅንን ለኖርዌይ ደራስያን ማኅበር “ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ ሽልማት” እጩ ተወዳዳሪ አድርጌ ባቀረብኩበት ሰዓት ከጎኔ ከሞቆማቸውም በላይ፣ በቀጣዩ ዓመት ሎሬት ጸጋዬን ለኖቤል ሽልማት እጩ አድርጎ ለማቅረብ፤ ከእኔና ከጋሼ ኃይሉ ገብረ ዮሐንስ (ገሞራው) ጎን ለመሰለፍ ቃል ገበተውልን የነበሩ ናቸው። በሎሬት ጸጋዬ እረፍት ምክንያት ያሰብነው ሳይተገበር በውጥን ቀርቷል።

ዶ/ር ሞልቨር በጅምር የያዙዋቸውን ሥራዎች ጨርሰው ለኖርዌጂያን አንባቢያን አቅርበው ለማስነበብ እንዲያበቃቸው ምኞቴ ነው።

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. BELIYU BERHANU says

    October 13, 2017 01:01 pm at 1:01 pm

    IT IS VARY GOOD

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
Copyright © 2026 · Goolgule