• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ፍቅር እስከ መቃብር” በሰሜን ዋልታ

February 9, 2015 07:07 am by Editor 1 Comment

ዶክተር ሬዶልፍ ክኑት ሞልቨር (Reidulf Knut Molvær) የ77 ዓመት ኖርዌጂያዊ አዛውንት ናቸው። ዋና ሙያቸው የሥነ ጥሑፍ፣ የቋንቋ፣ የታሪክና የማህበራዊ ሳይንስ ተመራማሪነት ነው። በአማርኛ ሥነ ጽሁፍና ቋንቋ ጥናት ከሎንዶን ዩኒቨርስቲ የዶክትሬት ድግሪያቸውን ያገኙ ሲሆኑ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ 14 ኬንያ ውስጥ ደግሞ 6 ዓመታትን ባለም አቀፍ ድርጅቶች ውስጥ በመሥራት አሳልፈዋል። የትዳር ጓደኛቸው ኬንያዊት ሲሆኑ፣ አራት ልጆችም በጋራ አፍርተዋል። ከልጆቻቸውም መካከል አንዱ የሕክምና ዶክተር፣ ሁለቱ ኢንጂነሮች ሆነዋል።

ዶ/ር ሞልቨር ለፍልስፍና ማስትሬት ድግሪያቸው መመረቂያ  አዘጋጅተውት የነበረው ጥናታቸው ቀዳሚውን እውቅና አስገኝቶላቸው የነበረ ነው። ይህን ጥናታቸውን “ልማድና ለውጥ በኢትዮጵያ – Tradition and Change in Ethiopia: Social and Cultural Life as Reflected in Amharic Fictional Literature ca. 1930-1974” በሚል አቢይ ርእስ ስር አስቀምጠው ባለ 365 ገጽ መጽሐፍ እ.አ.አ. በ1980 ዓ.ም- አሳትመው አውጥተዋል። ይህ የበኩር ሥራቸው የብዙ አንባቢያንንና ተመራማሪዎችን ቀልብ የሳበ ሆኖ እስከዛሬ ድረስ ዘልቋል። ለጥቀውም ”ማኅበራዊነትና ማኅበራዊ ቁጥጥር በኢትዮጵያ – Socialization and Social Control in Ethiopia” እ.አ.አ. በ1995 ዓ.ም. አንድ ዳጎስ ያለ መጽሐፍ ለንባብ አብቅተዋል።

ከዚህ ሥራቸው ቀጥለውም በእንግሊዝኛ ቋንቋ “Black Lions – The Creative Lives of Modern Ethiopia’s Literary Giants and Pioneers” በሚል ርእስ የመጀመሪያውን የ33 ኢትዮጵያውያን ደራስያንን ሥራና የሕይወት ታሪክ ያካተተ መጽሐፍ እ.አ.አ. በ1997 ዓ.ም. ላይነ ንባብ አብቅተዋል። ይህም ድንቅ ሥራቸው በዚህ ረገድ የነበረውን የመረጃ እጥረት ክፍተት ለመሸፈን ከፍተኛ እገዛ አድርጓል። ከብላቴን ጌታ ሕሩይ ወልደ ሥላሴ እስከ እኔ ትውልድ ያሉትን ተጠቃሽ ጸሐፍት አካተውበታል።

ሰንበት ብለውም በዚሁ መድበላቸው ውስጥ ያልተካተቱትነ የሁለት እውቅ ኢትዮጵያውያን የሕይወት ታሪኮችና ሥራዎቻቸውን ”የሰሜን ምሥራቅ አፍሪካ ጥናት- Northeast African Studies” በተሰኘ ታዋቂ  ጁርናል ላይ አቅርበው አስነብበዋል። እኒህም ሁለት እውቅ ደራስያን ሻምበል  አፈወርቅ ዮሐንስና ደራሲ ደበበ ሰይፉ ናቸው።

ቀጥለውም የተለያዩ ጥናታዊ ጽሑፎችን በኢትዮጵያ ሥነ ጥሑፍ፣ ቋንቋ፣ ታሪክና ማህበራዊ ሳይንስ ዙሪያ እያዘጋጁ በተለያዩ ጉባዔዎችና ጁርናሎች ላይ አቅርበዋል። አሁን በቅርቡ በሐምሌ ወር 2014 ዓ.ም. ደግሞ የክቡር ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁን ዝነኛውን ያገራችንን ረዥም ልቦለድ መጽሐፍ ”ፍቅር እስከ መቃብር”ን ወደ ኖርዌጂያንኛ ቋንቋ “Kjærlighet til graven” በሚል ርእስ ተርጉመው፣ ለንባብ አብቅተዋል። ይህ ወደ ኖርዌጂያን ቋንቋ የተተረጎመው ሥራቸው 607 ገጾች ያለው ሲሆን፣ በኖርዌጂያን አንባቢያን ዘንድ ትልቅ ተነባቢነትንና ተቀባይነትንአግኝቶላቸዋል።

ዶ/ር ሞልቨር ለዚህ ድንቅ ሥራቸው ክብርና ሞገስ ሊሰጣቸው የሚገባችው ታታሪ ሰው ናቸው። ”ፍቅር አስከ መቃብር” ከዚህ ቀደም ወደ ራሽያንና ወደ እንግሊዝኛ ቋንቋዎች መተርጎሙ ይታወሳል። አሁን ደግሞ ወደ ኖርዌጂያን ቋንቋ መተርጎሙ፣ በሰሜን ዋልታ የእስካንዲኔቪያን አገሮች ቋንቋዎች የመተርጎም እድሉን ከፍ ያድርገዋል። ይሄውም ወደ እስዊድንኛ፣ ዳንማርኪኛ፣ ፊንማርኪኛና ሳሚኛ ቋንቋዎች የመተርጎም እድሉ ሰፊ ነው። ዶ/ር ሞልቨርን ሳወያያቸው በቀጣይነት ስላሰቧቸው የትርጉም ሥራዎቻቸው ጠይቄያቸው ነበር። ከአማርኛ ሥነ ጽሑፎች ውስጥ የብላቴን ጌታ ማህተመ ሥላሴ ወልደ መስቀልን “እንቅልፍ ለምኔ” ፣ የአፈወርቅ ገብረ ኢየሱስን ”ጦቢያ”፣ የደጃዝማች ግርማቸው ተክለ ሐዋሪያትን ”አርአያ”፣ ከኬንያ ሥነ ጽሑፍ ደግሞ የንጉጊ ዋቲያንጎን “Grain of Wheat” ለመተርጎም ከጀመሯቸውና በእቅድ ከያዟቸው ሥራዎች መካከል እንዳሉ አጫውተውኛል። የታዋቂውን ኬንያዊ ደራሲ የንጉጊን መጽሐፍ እንዲተረጉሙ የግድ ሰበብ የሆናቸውም ለሥነ ጽሑፍ የኖቤል ሽልማት እጩ ሆኖ እንዲቀርብ ስለታሰበ፣ ከወዲሁ በኖርዌጂያን አንባቢያን ዘንድ እውቅናውን ለማጠንከርና መንገዱንም ለመጥረግ እንዲያመች እንደሁ ዶ/ር ሞልቨር አልሸሸጉኝም። እኒህ ይበልጡኑ በኢትዮጵያ ሥነ ጥሑፍ፣ ቋንቋ፣ ታሪክና ማህበራዊ ሳይንስ ዙሪያ ጥብቅ ምርምር ሲያደርጉ የኖሩ ሰው፣ ከዚህ ቀደምም አንድ በኪስዋህሊ ቋንቋ የተጻፈ የኬንያ ሥነ ጽሑፍ ወደ ኖርዌጂያን ቋንቋ መተርጎማቸውም ይታወቃል።

ከዶ/ር ሞልቨር ተጨማሪ ሥራዎች መካከል እነዚህም ይገኙባቸዋል

ዶ/ር ሞልቨር ለኢትዮጵያውያን ደራስያንና የቀለም ሰዎች ታላቅ አክብሮትና ፍቅር ያለቸው ሰው መሆናቸውም የሚሰመርበት ጉዳይ ነው። እ.አ.አ. በ2005 ዓ.ም. ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅንን ለኖርዌይ ደራስያን ማኅበር “ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ ሽልማት” እጩ ተወዳዳሪ አድርጌ ባቀረብኩበት ሰዓት ከጎኔ ከሞቆማቸውም በላይ፣ በቀጣዩ ዓመት ሎሬት ጸጋዬን ለኖቤል ሽልማት እጩ አድርጎ ለማቅረብ፤ ከእኔና ከጋሼ ኃይሉ ገብረ ዮሐንስ (ገሞራው) ጎን ለመሰለፍ ቃል ገበተውልን የነበሩ ናቸው። በሎሬት ጸጋዬ እረፍት ምክንያት ያሰብነው ሳይተገበር በውጥን ቀርቷል።

ዶ/ር ሞልቨር በጅምር የያዙዋቸውን ሥራዎች ጨርሰው ለኖርዌጂያን አንባቢያን አቅርበው ለማስነበብ እንዲያበቃቸው ምኞቴ ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. BELIYU BERHANU says

    October 13, 2017 01:01 pm at 1:01 pm

    IT IS VARY GOOD

    Reply

Leave a Reply to BELIYU BERHANU Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule