• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ፎቶና ታሪኩ – እስረኞች [የህወሓት ግፍ ሰለባ ስለሆኑት ወገኖቻችን ሲባል ሊነበብ የሚገባው]

January 7, 2018 04:43 pm by Editor 3 Comments

{ፈላስፋ በወህኒ ቤት በራፍ ላይ እንዲህ የሚል ፅሁፍ አነበብኩ አለ፤ ይህች ቦታ የመከራና የጭንቅ ናት፤ ያልሞቱ (በሕይወት ያሉ) ሰዎች የሚቀበሩባት መቃብርም ናት። የወዳጆች መፈተኛ፤ የጠላቶች መደሰቻ የሆነች ቦታ ናትና።} አንጋረ ፈላስፋ (የፈላስፎች አነጋገር)፤ በሊቀ መዘምራን ሞገስ ዕቁበ ጊዮርጊስ በ1953 ዓ/ም ከግዕዝ ወደ አማርኛ ተተረጎመ።
*************************************************************
በወያኔ አገዛዝ፤ በወያኔ ቀንበር
የካቴናው ስርስር የኮረንቲው ንዝር
የመቀመቅ ፍዳው የጨለማው እስር
የሰቆቃው ንረት የአውሬዎቹ ምንዝር
እንዴት እንደ ሆነ እንዴት እንደነበር
ፍትህ በሌለበት ለዳኛ ከመንገር
ጠበቃ ከማቆም ዕማኝ ከመደርደር
ይኸው የኛ ፎቶ ታሪኩን ይናገር።
ፎቶ፤ ሴፕቴምበር 14 2011 (እአአ)

የወያኔ ፀጥታ ሀይሎች አዲስ አበባ ላይ አንዱዓለም አራጌን በቁጥጥር ስር ሲያውሉ። እነሆ ከዚህ ቀን ጀምሮ ወጣቱ ትንታግ የሠላማዊ ትግል አራማጅ ፖለቲከኛ በወህኒ ቤት ይገኛል። ህግና ዳኛ ወያኔንና አገዛዙን ለመጠበቅ በቆሙባት ኢትዮጵያ ለህዝብ መብት፤ ነፃነት ፍትህና እኩልነት ተሟጋቹ አንዱዓለም አራጌ በሽብርተኝነት ህገ መንግሥቱን በሀይል ለመናድ በሚል በተመሰረተበት ክስ ዕድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበት በር ተዘግቶበታል። ዘረኞችና ዘራፊዎች ‘መንግሥት’ በሆኑባት ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊነትና ፍትህ ጠያቂነት ‘ሽብርተኝነት’ ሆኗል። ዳኞች እነሱ አቃቤ ህግ እነሱ ህጉም ለእነርሱ።

እነሆ በ2002 ዓ/ም (2010) ምርጫ ወቅት በህወሃት/ኢህአዴግ ገዢ ፓርቲ እና በተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በተካሄደው ውይይት አንዱዓለም አራጌ ‘መድረክ’ን ወክሎ እንዲህ አለ፤ “ኢህአዴግ አንድም ቀን ስሜታዊ እንጂ ምክንያታዊ ውይይት አድርጎ አያውቅም። በመሰረቱ ኢህአዴግ አምባገነናዊ መንግሥት ነው። በግልፅ መነጋገር አለብን። የአምባገነንነቱ መሰረት ደግሞ ፍርሃት ነው። በሀገራችን ‘የፈሪ ዱላው አስራ ሁለት ነው’ ይባላል። ኢህአዴግ ፈሪ ስለሆነ የተለያዩ የፍርሃት ህጎችን እያወጣ የኢትዮጵያን ህዝብ ቀይዶ፤ ጫንቃው ላይ ተጭኖ ለመግዛት እየሞከረ ነው ያለው። ለምሳሌ በደርግ ጊዜ አንድ አዋጅ ወጥቶ ነበር፤ አዋጅ 767 የሚባል። ያነበበ ያስነበበ አሽሙር የተናገረ 15 ዓመት ይፈረድበታል ይላል። ዛሬ ኢህአዴግ የሚያወጣው የፀረ ሽብር ህግ ፤ የፓርቲዎች ሥነ ምግባር አዋጅ የኢትዮጵያን ህዝብ ለጉሞ እንዳይንቀሳቀስ የሚያደርግ ህግ ነው። ኢህአዴግ ከ’97 ዓመተ ምህረት በሁዋላ የተማርኩት ነገር አለ ይላል። የተማረው አንድ ነገር ነው። በነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የኢትዮጵያ ህዝብ ኢህአዴግን እንደማይመርጠው ያውቃል። ጠንቅቆ ያውቃል። ስለዚህ ሜዳውን ሁሉ ዘጋግቶ ለብቻው መሮጥ ይፈልጋል።

[የህወሓት ግፍ ሰለባ ስለሆኑት ወገኖቻችን ሲባል ሊነበብ የሚገባው]

ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: eprdf, Ethiopia, Full Width Top, meles, Middle Column, political prisoners, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    January 10, 2018 02:48 am at 2:48 am

    በውነቱ መነጋገር ካስፈለገ: አንተማመንም እንጂ: ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ሲሸፍት ያታሰሩ የጉራጌ ብሄረ ሰብ ወጣቶች ናቸው!! ለምሳሌ ያህል እስክንድር ነጋ: ዓንዱ አለም አራጌን ይጠቅሷል!!ከውጭ ማለትም ከሰሜን አሜሪካም ተደራጅተው ሙሉ ድጋፍ እያደረጉ ልማቱን ለማደናቀፍ የሚያደርጉት እነዚሁ ቡድኖች ናቸው:: ኢህአድግን ለማሳሰብ የምንፈልገው : ሁሉንም እስረኛ ባንዴ ወይም በጅምላ ከመልቀቅ እየተጠናና እየታየ ቢለቀቁ ለቅቆ ከማሳደድ ያግደናል::

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    January 10, 2018 03:10 am at 3:10 am

    ኢህአድግ!!! ሰድዶ ማሳደድ ካማረህ: ዶሮህን በቆቅ ለውጣት!!! ደጋግሞ ይታሰብበት!!!

    Reply
  3. Tesfa says

    February 4, 2018 06:57 pm at 6:57 pm

    አቶ ሙሉጌታ – በዘር የተቃመስክ ተውሳክ በመሆነህ እይታህ ሁሉ በዘር ዙሪያ ነው። ጉራጌዎች ሃገር አይሸጡም። ጉራጌዎች ሃገራቸውን፤ ህዝባቸውን የሚወድ በሃገራችን ውስጥ ጠንካራ ሰራተኛ እንደሆኑ የሚመሰከርላቸው ናቸው። ሰርተው ነው የሚከብሩት። እንደ ወያኔ በስርቆትና በዝርፊያ አይደለም። ግን እንዳንተ ያለ ጅል ይህ ሁሉ ነገር አይገባውም። የምትተነፍሰውና የምታስበው ወያኔ በገጠመልህ ሳንባና ጭንቅላት ነው።
    ከላይ የጠቀስካቸው በወያኔ ኢ-ፍትሃዊ ግፍ ሃበሳቸውን የሚቆጥሩት ስዎች በዘርና በጎሳ ቢሰለፉ ኑሮ ወያኔ አይነካቸውም ነበር። የሃገርን አንድነት፤ የወገንን መረገጥ በአደባባይ ወያኔን ተቃውመው ድምጻቸውን በማሰማታቸው ሰቆቃ ውስጥ ወያኔ ከተታቸው። ማሳደድ አንተን የመሰሉ የህዝባችን ተባዮች ነው እንጂ ከቆቅ ጋር ጥል ያለው ወይም ደሮውን በቆቅ የሚለውጥ ጅላ ጅል የለም። ገና ወያኔ ውሸቱን ሁሉን ፈትቼ እስርቤቱን ወደ መዝናኛ ቦታና የመጎብኛ መአከል አደርጋለሁ በማለቱ ይህን አምነህ ሰው እንዳይፈታ ምቀኛ መሆንህ ምንኛ ያሳዝናል። ልማት አደናቃፊው ወያኔ እንጂ ሌላ ሃይል አይደለም። ሁሉም ነገር ወደ ትግራይ በማለት ሌላውን የሃገራችን ክፍል ራቁቱን ያስቀረ አጥፊ ድርጅት ነው። እንዲሁ በየድህረ ገጽ እየገባህ ነገር ታማታለህ። ግን ተነቅቶብሃል። ማንም አይሰማህም።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule