• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ፎቶና ታሪኩ – እስረኞች [የህወሓት ግፍ ሰለባ ስለሆኑት ወገኖቻችን ሲባል ሊነበብ የሚገባው]

January 7, 2018 04:43 pm by Editor 3 Comments

{ፈላስፋ በወህኒ ቤት በራፍ ላይ እንዲህ የሚል ፅሁፍ አነበብኩ አለ፤ ይህች ቦታ የመከራና የጭንቅ ናት፤ ያልሞቱ (በሕይወት ያሉ) ሰዎች የሚቀበሩባት መቃብርም ናት። የወዳጆች መፈተኛ፤ የጠላቶች መደሰቻ የሆነች ቦታ ናትና።} አንጋረ ፈላስፋ (የፈላስፎች አነጋገር)፤ በሊቀ መዘምራን ሞገስ ዕቁበ ጊዮርጊስ በ1953 ዓ/ም ከግዕዝ ወደ አማርኛ ተተረጎመ።
*************************************************************
በወያኔ አገዛዝ፤ በወያኔ ቀንበር
የካቴናው ስርስር የኮረንቲው ንዝር
የመቀመቅ ፍዳው የጨለማው እስር
የሰቆቃው ንረት የአውሬዎቹ ምንዝር
እንዴት እንደ ሆነ እንዴት እንደነበር
ፍትህ በሌለበት ለዳኛ ከመንገር
ጠበቃ ከማቆም ዕማኝ ከመደርደር
ይኸው የኛ ፎቶ ታሪኩን ይናገር።
ፎቶ፤ ሴፕቴምበር 14 2011 (እአአ)

የወያኔ ፀጥታ ሀይሎች አዲስ አበባ ላይ አንዱዓለም አራጌን በቁጥጥር ስር ሲያውሉ። እነሆ ከዚህ ቀን ጀምሮ ወጣቱ ትንታግ የሠላማዊ ትግል አራማጅ ፖለቲከኛ በወህኒ ቤት ይገኛል። ህግና ዳኛ ወያኔንና አገዛዙን ለመጠበቅ በቆሙባት ኢትዮጵያ ለህዝብ መብት፤ ነፃነት ፍትህና እኩልነት ተሟጋቹ አንዱዓለም አራጌ በሽብርተኝነት ህገ መንግሥቱን በሀይል ለመናድ በሚል በተመሰረተበት ክስ ዕድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበት በር ተዘግቶበታል። ዘረኞችና ዘራፊዎች ‘መንግሥት’ በሆኑባት ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊነትና ፍትህ ጠያቂነት ‘ሽብርተኝነት’ ሆኗል። ዳኞች እነሱ አቃቤ ህግ እነሱ ህጉም ለእነርሱ።

እነሆ በ2002 ዓ/ም (2010) ምርጫ ወቅት በህወሃት/ኢህአዴግ ገዢ ፓርቲ እና በተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በተካሄደው ውይይት አንዱዓለም አራጌ ‘መድረክ’ን ወክሎ እንዲህ አለ፤ “ኢህአዴግ አንድም ቀን ስሜታዊ እንጂ ምክንያታዊ ውይይት አድርጎ አያውቅም። በመሰረቱ ኢህአዴግ አምባገነናዊ መንግሥት ነው። በግልፅ መነጋገር አለብን። የአምባገነንነቱ መሰረት ደግሞ ፍርሃት ነው። በሀገራችን ‘የፈሪ ዱላው አስራ ሁለት ነው’ ይባላል። ኢህአዴግ ፈሪ ስለሆነ የተለያዩ የፍርሃት ህጎችን እያወጣ የኢትዮጵያን ህዝብ ቀይዶ፤ ጫንቃው ላይ ተጭኖ ለመግዛት እየሞከረ ነው ያለው። ለምሳሌ በደርግ ጊዜ አንድ አዋጅ ወጥቶ ነበር፤ አዋጅ 767 የሚባል። ያነበበ ያስነበበ አሽሙር የተናገረ 15 ዓመት ይፈረድበታል ይላል። ዛሬ ኢህአዴግ የሚያወጣው የፀረ ሽብር ህግ ፤ የፓርቲዎች ሥነ ምግባር አዋጅ የኢትዮጵያን ህዝብ ለጉሞ እንዳይንቀሳቀስ የሚያደርግ ህግ ነው። ኢህአዴግ ከ’97 ዓመተ ምህረት በሁዋላ የተማርኩት ነገር አለ ይላል። የተማረው አንድ ነገር ነው። በነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የኢትዮጵያ ህዝብ ኢህአዴግን እንደማይመርጠው ያውቃል። ጠንቅቆ ያውቃል። ስለዚህ ሜዳውን ሁሉ ዘጋግቶ ለብቻው መሮጥ ይፈልጋል።

[የህወሓት ግፍ ሰለባ ስለሆኑት ወገኖቻችን ሲባል ሊነበብ የሚገባው]

ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: eprdf, Ethiopia, Full Width Top, meles, Middle Column, political prisoners, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    January 10, 2018 02:48 am at 2:48 am

    በውነቱ መነጋገር ካስፈለገ: አንተማመንም እንጂ: ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ሲሸፍት ያታሰሩ የጉራጌ ብሄረ ሰብ ወጣቶች ናቸው!! ለምሳሌ ያህል እስክንድር ነጋ: ዓንዱ አለም አራጌን ይጠቅሷል!!ከውጭ ማለትም ከሰሜን አሜሪካም ተደራጅተው ሙሉ ድጋፍ እያደረጉ ልማቱን ለማደናቀፍ የሚያደርጉት እነዚሁ ቡድኖች ናቸው:: ኢህአድግን ለማሳሰብ የምንፈልገው : ሁሉንም እስረኛ ባንዴ ወይም በጅምላ ከመልቀቅ እየተጠናና እየታየ ቢለቀቁ ለቅቆ ከማሳደድ ያግደናል::

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    January 10, 2018 03:10 am at 3:10 am

    ኢህአድግ!!! ሰድዶ ማሳደድ ካማረህ: ዶሮህን በቆቅ ለውጣት!!! ደጋግሞ ይታሰብበት!!!

    Reply
  3. Tesfa says

    February 4, 2018 06:57 pm at 6:57 pm

    አቶ ሙሉጌታ – በዘር የተቃመስክ ተውሳክ በመሆነህ እይታህ ሁሉ በዘር ዙሪያ ነው። ጉራጌዎች ሃገር አይሸጡም። ጉራጌዎች ሃገራቸውን፤ ህዝባቸውን የሚወድ በሃገራችን ውስጥ ጠንካራ ሰራተኛ እንደሆኑ የሚመሰከርላቸው ናቸው። ሰርተው ነው የሚከብሩት። እንደ ወያኔ በስርቆትና በዝርፊያ አይደለም። ግን እንዳንተ ያለ ጅል ይህ ሁሉ ነገር አይገባውም። የምትተነፍሰውና የምታስበው ወያኔ በገጠመልህ ሳንባና ጭንቅላት ነው።
    ከላይ የጠቀስካቸው በወያኔ ኢ-ፍትሃዊ ግፍ ሃበሳቸውን የሚቆጥሩት ስዎች በዘርና በጎሳ ቢሰለፉ ኑሮ ወያኔ አይነካቸውም ነበር። የሃገርን አንድነት፤ የወገንን መረገጥ በአደባባይ ወያኔን ተቃውመው ድምጻቸውን በማሰማታቸው ሰቆቃ ውስጥ ወያኔ ከተታቸው። ማሳደድ አንተን የመሰሉ የህዝባችን ተባዮች ነው እንጂ ከቆቅ ጋር ጥል ያለው ወይም ደሮውን በቆቅ የሚለውጥ ጅላ ጅል የለም። ገና ወያኔ ውሸቱን ሁሉን ፈትቼ እስርቤቱን ወደ መዝናኛ ቦታና የመጎብኛ መአከል አደርጋለሁ በማለቱ ይህን አምነህ ሰው እንዳይፈታ ምቀኛ መሆንህ ምንኛ ያሳዝናል። ልማት አደናቃፊው ወያኔ እንጂ ሌላ ሃይል አይደለም። ሁሉም ነገር ወደ ትግራይ በማለት ሌላውን የሃገራችን ክፍል ራቁቱን ያስቀረ አጥፊ ድርጅት ነው። እንዲሁ በየድህረ ገጽ እየገባህ ነገር ታማታለህ። ግን ተነቅቶብሃል። ማንም አይሰማህም።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule