• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ፎቶና ታሪኩ

November 16, 2017 08:30 pm by Editor Leave a Comment

በወያኔ ዘመን በህወሃት ቀንበር
ያሳለፍነው ህይወት የጠጣነው አረር
እንዴት እንደሆነ እንዴት እንደነበር
ጠበቃ ከማቆም እማኝ ከመደርደር
ይኸው የኛ ፎቶ ታሪኩን ይናገር።

*የተከበርክ አንባቢ ሆይ! ቀጣዮቹን ፎቶዎች በፅሞና እና በማስተዋል ተመልከታቸው፤ መልዕክቶቹንም ረጋ ብለህ ወደ
ነፍስህም ቀርበህ አንብብ። ምናልባት ለመፍትሄውም ሆነ ለችግሩ አንተ ትቀርብ ይሆናልና።

የድህነት ጠባሳዎቸ ከሚታዩባቸው የጎንደር መንገዶች አንዱ (ፎቶ: James Jeffrey/IPS)

በጎንደር ከተማ የሚታየው ዘግናኝ የቁልቁለት ‘እድገት’። በህወሃት በይፋ ጠላትነት ተፈርጆ የቁም ስቅሉን እያየ በሚገኘው የአማራ ህዝብ ላይ ሆን ተብሎ በመካሄድ ላይ ያለው የኢኮኖሚ ተዐቅቦ ያስከተለው መከራና ድህነት እጅግ ዘግናኝ ሲሆን በቅርቡ በወጣ ጥናታዊ ዘገባም የአማራ ህፃናት ከዚህ በፊት ታይቶ በማያውቅ ሁኔታ (በርግጠኝነትም በሌሎች ክልሎች በዚህ ስፋትና መልክ ያልተከሰተ) ያለ ዕድሜያቸው እየቀነጨሩ በመሆኑ ክልሉ ሰፊ የሆነውን የነገውን የሥራና የአስተዳደር ተረካቢ የሆነውን ወጣት ሀይል የማጣት እድሉ ከፍተኛ እንደሆን ተጠቁሟል። ጎንደርና ባህር ዳር ሲጨልም መቀሌና አክሱም በብርሃን ያንፀባርቃሉ። በአማራው ክልል ባለፈው የህወሃት ሩብ ምዕተ ዓመት አገዛዝ የጤና ጣቢያዎች ሆስፒታሎች መንገዶች ት/ቤቶች የመብራትና የውሃ መስመሮች ሆን ተብለው እንዳይገነቡ የነበሩትም እንዲወላልቁና እንዲፈራርሱ የተደረገበት የክፉ ሰዎች በቀለኝነት በህዝብ ሰቆቃና ህይወት መጠነ ሰፊ ጥፋት ያደረሰና እያደረሰም ያለ የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር ዘር የማጥፋት ተልዕኮ ውጤት ነው።

በአማራው ክልል በሩብ ምዕተ ዓመት የተገነቡት ከባድ ኢንዱስትሪዎችም ሆኑ መጠነኛ ስንት ናቸው? የአማራው ክልል ካለው የቆዳ ስፋትና በውስጡም ከሚኖረው ህዝብ ብዛት አንፃር በትግራይ ክልል የተገነቡት ከባድ ኢንዱስትሪዎችና መጠነኞችስ ስንት ናቸው? ንፅፅሩስ ተገቢና ፍትሃዊ አይሆንምን? ብአዴን ይህንን አያውቅም? ብአዴን እመራዋለሁ የሚለው ህዝብ ፍትሃዊ ባልሆነ ብቻ ሳይሆን ጭፍን በቀለኛ በሆነው ህወሃት ቀጥተኛ ብቀላ ሲፈፀምበት መሬቱን ሲገፈፍ ንብረቱን ሲቀማ የመኖር ህልውናው በየአቅጣጫው በእሾህ ተከቦ ሲደማ፤ በትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር የአጥፍቶ ጠፊ ሰላዮችና በተባባሪዎቹ የዘር ድርጅቶችና አስፈፃሚ ታጣቂዎች በመላው ሀገሪቱ ደሙ ደመ ከልብ ሲሆንና ‘የድረሱልኝ’ ጣዕር ሲያሰማ እንዴት ሆኖ ነው ብአዴን ከአማራው አብራክ የወጣ ነው ማለት የሚቻለው? ብአዴን ሆይ! ሁለት ሞት የለምና አንዱንና ሰማዕታዊውን ሞት መርጠህ ለህዝብህና ሰው ስለመሆን ስትል ዘር አጥፊውን ህወሃት ተጋፍጠህ ብትሞት እንኳን ሞትክ አይባልምና አደባባይ ወጥተህ ህዝብህን ምራ! ወይም ለሀገራቸው ኢትዮጵያና ለሚወክሉትም ህዝባቸው ለመሞት ለተነሱ ትንታጎች የአማራ ውልድ ወጣት የኢትዮጵያ ልጆች አስረክብ!! ብአዴን ሆይ ስማ፤ ሁለት እግር አለኝ ብሎ ሁለት ዛፍ በተመሳሳይ ጊዜ መውጣት አይቻልም። ወይ የህወሃት ናዚስቶችን ወይ ህዝብህን ሀገርህን ኢትዮጵያንና ፍትህን ምረጥ፤ ይኸው ነው!

በፌዴራል መንግሥት ልዩ ልዩ በጀትና ወጪ በከፍተኛ ፍጥነትና ዕድገት በመገንባት ላይ ያለችው መቀሌ ከተማ (Wikimedia Commons)

ባለፈው ሩብ ምዕተ ዓመት በትግራይ ክልል የተካሄደው ልማትና ያስከተለው ለውጥ በመላ የኢትዮጵያ ግዛቶች ተካሂዷል ከተባለው ልማት ግንባታና እድገት በእጥፍ ድርብ የሚበልጥ ነው። ዘመናዊ የህዝብ ማመላለሻ አውሮፕላኖች የካርጎና የጦር ጄቶች ማሳረፊያ ጣቢያዎች እጅግ የተራቀቁ ሆስፒታሎችና በአቅርቦት የተደራጁ አያሌ ጤና ጣቢያዎች መንገዶች የተሟላ የመብራት አገልግሎት ፋብሪካዎችና ኢንዱስትሪዎች የንፁህ ውሃ መስመሮች የተደራጁና የተሟሉ ትምህርት ቤቶች ኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎች እና ወዘተርፈዎች ሁሉ ከተከዜ በታች ባለው ግብር ከፋይ የኢትዮጵያ ህዝብና በሀገሪቱ አንጡራ ሀብት ኪሳራ በአንዲት ክፍለሀገር ላይ ተገንብተውና በመገንባትም ላይ የሚገኙ ሲሆን ይህ ሁሉ አደሏዊነትና ግፍ የሚፈፀመው ደግሞ ‘ትግራይ እስክትለማ ሌላው ይድማ” በሚለው የዘረኛው ህወሃት በቀለኛ መርህና በተባባሪዎቹ የሥልጣን አጎብዳጅነትና አሽከርነት ነው። ከተከዜ በታች የሚኖረው ኢትዮጵያዊና አዲስ ትውልድ አፍ መፍቻው ‘መብራት የለም፤ ውሃ የለም፤ ስኳር የለም፤ ሥራ የለም…’ ሲሆን በትግራይ ክልል በሚኖሩ ትግራውያን እኒህ አፍ መፍቻና የእለት ተእለት መግባቢያ ቃላት አይታወቁም። ወደ ሶስት አሥርታት እየተጠጋ የሚገኘው የህወሃት ፌዴራሊዝም ውጤት የኢፌዲሪ እኩልነት። ድንቄም እኩልነት!

መስፍን ማሞ ተሰማ

(ቀሪዎቹን ፎቶዎችና ታሪካቸውን ለማንበብ እዚሀ ላይ ይጫኑ)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule