• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የማናውቀው ታሪካችን

January 16, 2017 05:24 am by Editor 4 Comments

ታሪካችንን ባለማወቃችን ሁሌም ወደኋላ በመገስገስ ላይ እንገኛለን፤ ሰሞኑን አንዳንድ ዜና መዋዕሎችን ማንበብ ጀምሬ እስካሁን አራት ያህል አንብቤአለሁ፤ ከዚህ በፊት እየተንገዳገድሁ በግዕዝ አንብቤአቸዋለሁ፤ ዛሬ የሲራክ አሳታሚ ድርጅት በአማርኛ እያሳተማቸው በመሆኑ ምስጋና ይድረሰውና ሳልንገዳገድ በአማርኛ እያነበብሁ ነው፤ በዚህ ንባቤ ውስጥ አንዳንድ ያገኘኋቸው ሀሳቦች ስለራሳችን ያለን እውቀት ምን ያህል ጎደሎ መሆኑን የሚያሳዩ ናቸው፤ ለዛሬው ሁለት ሀሳቦችን ከላሊበላ ዜና መዋዕል፤ አንድ ደግሞ ከሱስንዮስ መርጫለሁ፤ እኔን እንዳስደነቁኝ ሌሎችንም ያስደንቃሉ ብዬ እገምታለሁ፡፡

አንደኛ፤ ከስምንት መቶ ዓመታት በፊት በ1160 ዓ.ም. የነገሠው ገብረ መስቀል የሚባለው የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት “በነገሠ በአሥር ዓመቱ መራ ከተባለው አጠገብ የነበረውን ቤተ መንግሥት ወደሌላ ለማዛወር አስቦ ቀይት ከተባለችው ባላባት ከሚዳቋ ገደል በላይ፣ ከመካልት በመለስ፣ ከጉሮ በታች፣ ከገጠርጌ አፋፍ በላይ ያለውን ቦታ በአርባ ጊደር ገዝቶ ቤተ መንግሥቱን መካነ ልዕልት ብሎ እሰየመው ቦታ ላይ ሠራና በዚያው አቅራቢያ ታላላቅ ቋጥኝ ደንጊያዎች መኖራቸውን ስላረጋገጠ …” የላሊበላን አሥር የድንጋይ ፍልፍል ቤተ ክርስቲያኖች አሠራ፤ እነዚህን በዓለም ተወዳዳሪ የሌላቸውን ዕጹብ-ድንቅ የሚባሉ ቤተ ክርስቲያኖች ለማሠራት ሃያ ሦስት ዓመታት ብቻ ፈጀበት፡፡

ከአጼ ምኒልክ በቀር እስከዛሬ በእንደዚህ ያለ አጭር ጊዜ ውስጥ እንዲህ ያለ ትልቅ ሥራ ያበረከተልን ንጉሠ ነገሥት ያለ አይመስለኝም፡፡

ሁለተኛ፤ “አጼ ገብረ መስቀል በተወለደ በሰባ ሰባት፣ በነገሠ በሠላሳ ሰባት ዓመቱ የአጎቱን ልጅ ነአኩቶ ለአብን በመንግሥቱ አስቀምጦ ሥርዓተ መንግሥቱን እንዲያጠና በቅርብ እየተቆጣጠረ እስከ ሦስት ዓመት ጠበቀው፤ ከሦስት ዓመት በኋላ በነገሠ በአርባ ዓመት፣ በተወለደ በሰማንያ ዓመቱ” ዐረፈ፤ ልብ በሉ፤ የአጎቱን ልጅ መርጦ አንግሦት፣ አጠገቡ ሆኖ እያስተማረው ለሦስት ዓመታት ያህል ቆይቶ ሞተ፡፡

ከዛሬ ሦስት መቶ ዓመታት በፊት ደግሞ ከአጼ ሱስንዮስ ዜና መዋዕል (1597-1625) ያገኘሁት የሕዝብን ንቃትና ቆራጥነት የሚያሳይና የሚያስደንቅ ታሪክ ነው፤

የእናርያ ሰዎች ቤነሮ የሚባል ሹማቸውን ገደሉና ለአጼ ሱስንዮስ ደብዳቤ ላኩለት፤ “እነሆ ሰዎችን ያለፍርድ ስለገደለ፣ የሰዎችን እጅና እግርም ስለቆረጠ፣ የሰዎችን ዓይንም ስላጠፋ፣ … በወጣቶችና በሽማግሌዎች፣ በሕጻናትም ላይ ስላርራራ፣ እኛ ከየቤታችን ያዋጣነውን የንጉሥ ግብርም ስለወሰደ፣ በቅሚያና በዝርፊያም የሰውን ሁሉ ገንዘብ ስለሰበሰበ፣ የሰውን ሚስት ስለቀማ፣ ስለሽርሙጥናውና ስለስስቱም፣ የወንድሙን ሚስት ስለወሰደ፣ በላያችን ላይም ግፍን ስለፈጸመ፣ ሴት ዘጠኝ ወር አርግዛ በአሥረኛው ወር ልጅን እንደምትወልድ እኛም ለዘጠኝ ዓመታት ያህል የሱን ተንኮል ሁሉ አረገዝን፤ በአሥረኛውም ዓመት ሞትን ወለድንለት፤ የእናርያ ሰዎችን ሁሉ ያጠፋ ዘንድም ስለጸናና ስለጨከነ ገደልነው፡፡”

አጼ ሱስንዮስም ለወጉ ተቆጣና ሌላ ሾመላቸው፡፡

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
ጥር 2009 (ከህንድ)

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Social Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Eunetu Yeneger says

    January 16, 2017 06:22 pm at 6:22 pm

    ፕ/ር እንደ እኔ መረዳት ለዚህ ሁሉ መከራና ችግር መነሻ ምንጩ የጠቀሱት የመልካም አስተዳደር እጦት ብቻ ሳይሆን መሪዎቻችንን እንደ ጣዖት እንድናያቸውና እንድንፈራቸው ያደረገን የመንፈሳዊ/ሃይማኖታችን ታሪካችን በዋናነት ተጠያቂ ይመስለኛልና በዚህ የሁለንተናዊ ችግሮቻችን ሁሉ ዋና ምንጭ በሆነው ጉዳይ ላይ ተነጋግረን ለዘመን ጠገቡ መከራችንና ብልሹ ታሪካችን እልባት እናብጅለት????

    አሁንም እጮሃለሁ!
    እውነቱ ይነገር

    Reply
  2. ቃሉ ኩሳ says

    January 17, 2017 06:05 pm at 6:05 pm

    አሁንም ብዚህ ጽሁፍ ውስጥ ያልገበኝ፣ መራ፣ ጎሮ፣ መካል የሚሉ ቃለቶች ትርጉማቸውና ቦታቸው የት እንደሆነ ኣልገበኝም። ቃለቶቹ ግዕዝ ናቸው ወይስ አማሪኛ? ከ800 ዓመት በፊት የነበሩ ወይስ ቅርብ ጊዜ የወጣላቸው ነው?

    Reply
  3. Lusif says

    January 18, 2017 01:44 am at 1:44 am

    It is good to know about the past through history. We may get a glimpse how the people of Ethiopia endured and secured the current political boundary. Did our parents did any remarkable progress ( socially, politically, economically ) like other advanced countries and people did? To me the was nothing, except passing there own problems to the current generation. Knowing history is good to know the misdeeds of the past. There were also undone affairs, that still haunt the current generation.
    The young generation, I believe, do not give a slightest care what had happened. It’s problem is an existential, now and here. With technological advances and easy access to knowledge and information, model countries are western democracies or countries like Japan, south Korea, or eastern democracy. It’s’ core demand is to have equal opportunity to shape and build his country – Ethiopia.
    Some conservatives from every corner, and those politicians who want cling to power my call the current young generation a copy cat or chauvinist, or narrow minded, or underdevelopment. All youth are not perfect. There could be such elements. The majority of the Ethiopian people, particularly the youth want to democratically free and equal. Only free and equal citizens can live in an enduring peace and respect. The Youth wants to rewrite the Ethiopian history anew, that is real, history of mutual peaceful coexistence, discovery, innovation, invention and exploration. Some may think it is a wishful dream. Who think so, are dead wrong. Other societies have done. We have every capability to it. We need only a democratic system and responsible government that honors equal opportunities.
    Dear Pro., I admire your effort. You tried to dig out the facts and the truth. That really shows me how much you love the integrity of country. I can guarantee you, no matter, what kind of voices you here from those empty barrels, no power on earth that can compromise our unity and Ethiopia will leave forever.

    Reply
  4. koster says

    January 18, 2017 08:43 pm at 8:43 pm

    We donot know our history properly since we were taught about Kansas, the Prairie etc. than about Dima or Washera. Those elites who managed to know more about Ethiopia will only tell us piece by piece only when it fits their interest. Before you said there is no ethnic Amara and now Ermias Tokuma is telling us there is not ethnicity at all in Ethiopia. https://www.youtube.com/watch?v=FOCbHb8LiYc

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule