• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የማናውቀው ታሪካችን

January 16, 2017 05:24 am by Editor 4 Comments

ታሪካችንን ባለማወቃችን ሁሌም ወደኋላ በመገስገስ ላይ እንገኛለን፤ ሰሞኑን አንዳንድ ዜና መዋዕሎችን ማንበብ ጀምሬ እስካሁን አራት ያህል አንብቤአለሁ፤ ከዚህ በፊት እየተንገዳገድሁ በግዕዝ አንብቤአቸዋለሁ፤ ዛሬ የሲራክ አሳታሚ ድርጅት በአማርኛ እያሳተማቸው በመሆኑ ምስጋና ይድረሰውና ሳልንገዳገድ በአማርኛ እያነበብሁ ነው፤ በዚህ ንባቤ ውስጥ አንዳንድ ያገኘኋቸው ሀሳቦች ስለራሳችን ያለን እውቀት ምን ያህል ጎደሎ መሆኑን የሚያሳዩ ናቸው፤ ለዛሬው ሁለት ሀሳቦችን ከላሊበላ ዜና መዋዕል፤ አንድ ደግሞ ከሱስንዮስ መርጫለሁ፤ እኔን እንዳስደነቁኝ ሌሎችንም ያስደንቃሉ ብዬ እገምታለሁ፡፡

አንደኛ፤ ከስምንት መቶ ዓመታት በፊት በ1160 ዓ.ም. የነገሠው ገብረ መስቀል የሚባለው የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት “በነገሠ በአሥር ዓመቱ መራ ከተባለው አጠገብ የነበረውን ቤተ መንግሥት ወደሌላ ለማዛወር አስቦ ቀይት ከተባለችው ባላባት ከሚዳቋ ገደል በላይ፣ ከመካልት በመለስ፣ ከጉሮ በታች፣ ከገጠርጌ አፋፍ በላይ ያለውን ቦታ በአርባ ጊደር ገዝቶ ቤተ መንግሥቱን መካነ ልዕልት ብሎ እሰየመው ቦታ ላይ ሠራና በዚያው አቅራቢያ ታላላቅ ቋጥኝ ደንጊያዎች መኖራቸውን ስላረጋገጠ …” የላሊበላን አሥር የድንጋይ ፍልፍል ቤተ ክርስቲያኖች አሠራ፤ እነዚህን በዓለም ተወዳዳሪ የሌላቸውን ዕጹብ-ድንቅ የሚባሉ ቤተ ክርስቲያኖች ለማሠራት ሃያ ሦስት ዓመታት ብቻ ፈጀበት፡፡

ከአጼ ምኒልክ በቀር እስከዛሬ በእንደዚህ ያለ አጭር ጊዜ ውስጥ እንዲህ ያለ ትልቅ ሥራ ያበረከተልን ንጉሠ ነገሥት ያለ አይመስለኝም፡፡

ሁለተኛ፤ “አጼ ገብረ መስቀል በተወለደ በሰባ ሰባት፣ በነገሠ በሠላሳ ሰባት ዓመቱ የአጎቱን ልጅ ነአኩቶ ለአብን በመንግሥቱ አስቀምጦ ሥርዓተ መንግሥቱን እንዲያጠና በቅርብ እየተቆጣጠረ እስከ ሦስት ዓመት ጠበቀው፤ ከሦስት ዓመት በኋላ በነገሠ በአርባ ዓመት፣ በተወለደ በሰማንያ ዓመቱ” ዐረፈ፤ ልብ በሉ፤ የአጎቱን ልጅ መርጦ አንግሦት፣ አጠገቡ ሆኖ እያስተማረው ለሦስት ዓመታት ያህል ቆይቶ ሞተ፡፡

ከዛሬ ሦስት መቶ ዓመታት በፊት ደግሞ ከአጼ ሱስንዮስ ዜና መዋዕል (1597-1625) ያገኘሁት የሕዝብን ንቃትና ቆራጥነት የሚያሳይና የሚያስደንቅ ታሪክ ነው፤

የእናርያ ሰዎች ቤነሮ የሚባል ሹማቸውን ገደሉና ለአጼ ሱስንዮስ ደብዳቤ ላኩለት፤ “እነሆ ሰዎችን ያለፍርድ ስለገደለ፣ የሰዎችን እጅና እግርም ስለቆረጠ፣ የሰዎችን ዓይንም ስላጠፋ፣ … በወጣቶችና በሽማግሌዎች፣ በሕጻናትም ላይ ስላርራራ፣ እኛ ከየቤታችን ያዋጣነውን የንጉሥ ግብርም ስለወሰደ፣ በቅሚያና በዝርፊያም የሰውን ሁሉ ገንዘብ ስለሰበሰበ፣ የሰውን ሚስት ስለቀማ፣ ስለሽርሙጥናውና ስለስስቱም፣ የወንድሙን ሚስት ስለወሰደ፣ በላያችን ላይም ግፍን ስለፈጸመ፣ ሴት ዘጠኝ ወር አርግዛ በአሥረኛው ወር ልጅን እንደምትወልድ እኛም ለዘጠኝ ዓመታት ያህል የሱን ተንኮል ሁሉ አረገዝን፤ በአሥረኛውም ዓመት ሞትን ወለድንለት፤ የእናርያ ሰዎችን ሁሉ ያጠፋ ዘንድም ስለጸናና ስለጨከነ ገደልነው፡፡”

አጼ ሱስንዮስም ለወጉ ተቆጣና ሌላ ሾመላቸው፡፡

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
ጥር 2009 (ከህንድ)

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Social Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Eunetu Yeneger says

    January 16, 2017 06:22 pm at 6:22 pm

    ፕ/ር እንደ እኔ መረዳት ለዚህ ሁሉ መከራና ችግር መነሻ ምንጩ የጠቀሱት የመልካም አስተዳደር እጦት ብቻ ሳይሆን መሪዎቻችንን እንደ ጣዖት እንድናያቸውና እንድንፈራቸው ያደረገን የመንፈሳዊ/ሃይማኖታችን ታሪካችን በዋናነት ተጠያቂ ይመስለኛልና በዚህ የሁለንተናዊ ችግሮቻችን ሁሉ ዋና ምንጭ በሆነው ጉዳይ ላይ ተነጋግረን ለዘመን ጠገቡ መከራችንና ብልሹ ታሪካችን እልባት እናብጅለት????

    አሁንም እጮሃለሁ!
    እውነቱ ይነገር

    Reply
  2. ቃሉ ኩሳ says

    January 17, 2017 06:05 pm at 6:05 pm

    አሁንም ብዚህ ጽሁፍ ውስጥ ያልገበኝ፣ መራ፣ ጎሮ፣ መካል የሚሉ ቃለቶች ትርጉማቸውና ቦታቸው የት እንደሆነ ኣልገበኝም። ቃለቶቹ ግዕዝ ናቸው ወይስ አማሪኛ? ከ800 ዓመት በፊት የነበሩ ወይስ ቅርብ ጊዜ የወጣላቸው ነው?

    Reply
  3. Lusif says

    January 18, 2017 01:44 am at 1:44 am

    It is good to know about the past through history. We may get a glimpse how the people of Ethiopia endured and secured the current political boundary. Did our parents did any remarkable progress ( socially, politically, economically ) like other advanced countries and people did? To me the was nothing, except passing there own problems to the current generation. Knowing history is good to know the misdeeds of the past. There were also undone affairs, that still haunt the current generation.
    The young generation, I believe, do not give a slightest care what had happened. It’s problem is an existential, now and here. With technological advances and easy access to knowledge and information, model countries are western democracies or countries like Japan, south Korea, or eastern democracy. It’s’ core demand is to have equal opportunity to shape and build his country – Ethiopia.
    Some conservatives from every corner, and those politicians who want cling to power my call the current young generation a copy cat or chauvinist, or narrow minded, or underdevelopment. All youth are not perfect. There could be such elements. The majority of the Ethiopian people, particularly the youth want to democratically free and equal. Only free and equal citizens can live in an enduring peace and respect. The Youth wants to rewrite the Ethiopian history anew, that is real, history of mutual peaceful coexistence, discovery, innovation, invention and exploration. Some may think it is a wishful dream. Who think so, are dead wrong. Other societies have done. We have every capability to it. We need only a democratic system and responsible government that honors equal opportunities.
    Dear Pro., I admire your effort. You tried to dig out the facts and the truth. That really shows me how much you love the integrity of country. I can guarantee you, no matter, what kind of voices you here from those empty barrels, no power on earth that can compromise our unity and Ethiopia will leave forever.

    Reply
  4. koster says

    January 18, 2017 08:43 pm at 8:43 pm

    We donot know our history properly since we were taught about Kansas, the Prairie etc. than about Dima or Washera. Those elites who managed to know more about Ethiopia will only tell us piece by piece only when it fits their interest. Before you said there is no ethnic Amara and now Ermias Tokuma is telling us there is not ethnicity at all in Ethiopia. https://www.youtube.com/watch?v=FOCbHb8LiYc

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule